Addis Ababa City Bus Service Enterprise አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Addis Ababa City Bus Service Enterprise አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት

Addis Ababa City Bus Service Enterprise አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የአዲስ አበባ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት አዋጅ ቁጥር74/2014 እንዲሁም በደንብ ቁጥር 144/2015 የተቋቋመ የልማት ድርጅት ነው። Our company gives different types of public transport service.

These are:-
1. Regular scheduled service
It is a service given by the enterprise to the commuters based on time table with 124 fixed routes.
2.Premium Service
It is a service given by the enterprise to government or non government organizations, schools and other institutions. It is based on distance covered and agreed with the user ahead of time.
3.Special service
It is a service given when speci

al occasion occurs like mourning, meeting and festivity based on kilometer and duration of service.
4.Vehicle Inspection
5.Maintenance Service
The maintenance is basis.
5.1. Preventive maintenance
5.2.Corrective Maintenance
6.External Technical Service
7. Technical Training & Certification
8.Advertisement
Anbessa City Bus Service Enerprise has attractive, modern, and wide coverage transit advertising solution which allows to cut advertising costs and offers you an efficient media that can pick the attention of everybody in Addis Ababa and neighboring cities
9.Training & Certification
stay with us!!!

ለአሽከርካሪዎች የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ፣(ሲቲ ባስ፤ ነሃሴ 29/ 2018 ዓ.ም) አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የቴክኒክ ስልጠና ዳይሬክቶሬት  ለኮንትራት  ሰራተኞች እና ለ...
04/09/2026

ለአሽከርካሪዎች የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ፣

(ሲቲ ባስ፤ ነሃሴ 29/ 2018 ዓ.ም) አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የቴክኒክ ስልጠና ዳይሬክቶሬት ለኮንትራት ሰራተኞች እና ለዜሮ ዓመት ስራ ልምድ ላላቸዉ ባስ ካፒቴኖች ዉጤታማ አገልግሎት መስጠት ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ስልጠና መስጠት ጀመረ።

ስልጠናውን በንግግር ያስጀመሩት የዕለቱ የክብር እንግዳ የድርጅቱ የቴክኒክ አገልግሎትና ስልጠና ዘርፍ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢ/ር አዳነ አብደታ በቀጣይ ኢትዮጵያ ለምታስተናግደዉ ኮፕ 32 ጉባኤ ዝግጅት ደረጃዉን የጠበቀ ትራንስፖርት አገልግሎት ለዕንግዶች እና ለተገልጋዩ ማህበረሰብ ለመስጠት ጨዋና ምስጉን አሽከርካሪ ማብቃት የአዲስ አበባ ከተማ አዉቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ቀዳሚ ተግባሩ በመሆኑ ነዉ ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ኃላፊዉ አክለዉም ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (ኮፕ 32) በቀጣይ የምታስተናግድ በመሆኑ ምንግዜም ተግባራዊ ሊደረጉ የሚገባቸዉ እንደ ተቋምና ሃገር አሽከርካሪዎች አደጋን ተከላክሎ ማሽከርከር እና የትራፊክ አደጋን በመቀነስ የተቋምና የሃገር ንብረትን ከዉድመት መከላከል እንደሚገባ፤ በስነ ምግባሩ የታነጸ እና በጥንቃቄ የማሽከርከር ስነ ባህሪን ጠብቆ አገልግሎትን በመስጠት የተቋም ስም ከፍ እንዲል በመስራት አገልግሎት አሰጣጥን ሁሉን ያማከለ ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል ሲሉ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል፡፡

አያይዘዉም አደጋ እድሜ፣ ጾታ፣ ዘር፤ ቀለም፤ሀብታም ወይም ድሃ ብሎ ስለማይመርጥ ሁልጊዜም እንቅስቃሴያችን ከአደጋ የፀዳ እንዲሆን የትራፊክ ህግን ማክበርና ተጠንቅቆ ማሽከርከር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ስልጠናዉን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ አዉቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የቴክኒክ ስልጠና ዘርፍ የአሽከርካሪ አሰልጣኝ ባለሙያ የሆኑት አቶ ተስፋዬ ክብረት ሲሆኑ ተሸከርካሪንና አሽከርካሪን ተቆጣጥሮ ማሽከርከር ላይ ትኩረት ያደረገ፣ አሽከርካሪ ማድረግ ስላለበት ጥንቃቄ ፣ ተሸከርካሪን ለአደጋ የሚያጋልጡ ተፈጥሯዊ እና ሰዉ ሰራሽ አምክንያቶችን ለይቶ ማወቅ ላይ ፣ የመንገድ አጠቃቀምና ሙያዊ ስነ ባህሪን አሟልቶ የተሸከርካሪን ደህንነት አረጋግጦ በመንቀሳቀስ ቀጣዩን 2019 በጀት ዓመት በስኬት ማሽከርከር ላይ ያተኮረ የስልጠናዉ አላማ መሆኑን በስልጠናዉ አብራርተዋል፡፡

በመጨረሻም ሰልጣኞች የስልጠናዉን አስፈላጊነትና ጠቀሜታ በመረዳት ላነሱት ሃሳብ አስተያት አሰልጣኙ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ስልጠናዉ በመግባባት ተጠናቋል፡፡
https://www.facebook.com/citybus2015
ቴሌግራም:https://t.me/citbus
ዩቱብ:https://youtube.com/-f2t.
ኢሜል: [email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected]

ሸጎሌ ቅርንጫፍ የ2019 እቅድን  ከባለ ድርሻ  አካለት ጋር የጋራ አደረገ ፡፡ (የከተማ አዉቶቡስ፤ነሃሴ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የሸጎሌ ቅርንጫ...
03/09/2026

ሸጎሌ ቅርንጫፍ የ2019 እቅድን ከባለ ድርሻ አካለት ጋር የጋራ አደረገ ፡፡

(የከተማ አዉቶቡስ፤ነሃሴ 28/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት የሸጎሌ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት እቅዱን የስራ ሃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የቅርንጫፍ ሰራተኞች በተገኙበት የጋራ አደረገ።

በእቅድ ዉይይቱ ላይ የሸጎሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስፈጻሚ ፤የጉለሌ ክ/ከተማ ትራንስፖርት ጽ/ቤት፤ቡራዩ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ጽ/ቤት ፤የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ጽ/ቤት እንዲሁም የቅርንጫፍ የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሁነዋል፡፡

ሪፖርቱን ያቀረቡት የቅርንጫፉ እቅድና በጀት ቡድን መሪ አቶ አቅናዉ ዘለቀ በ2018 የነበረን ዕቅድ አፈጻጸም መነሻ በማድረግ ለ2019 በጀት ዓመት ስራ አፈጻጸም ጥንካሬና ድክመትን የለየ እንዲሁም የባለ ድርሻ አከላትን አስፈላጊነትና ጥቅም የአፈጻጸም ክፍተትን የሚሞላ ሲሆን በቀጣይ በቅርንጫፍ ደረጃ ተጽዕኖ መፍጠር የሚያስችል እቅድና የባለ ድርሻ አካላትን ጥንካሬና ክፍተት በማመላከት የቀጣይ ይትኩረት ስራዎችን አመላካች ሰነድ አቅርበዋል፡፡

መርኃ -ግብሩን በይፋ የከፈቱት የሸጎሌ ቅርንጫፍ ም/ስራ አስፈጻሚ አቶ ሳሙኤል ተስፋዬ እንደገለጹት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከ84 በላይ መስመሮችን ተደራሽ በመሆን በከተማ እና አጎራባች የሸገር ከተሞችን ማህበረሰብ በስፋት የሚያገለግል በመሆኑ እንደ ቅርንጫፍ ያሉትን ሃብቶች በኔነት ስሜት በመንከባከብ አገልግሎቱን ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቅንጀት እየሰራን ለዉጥ ማምጣት ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል ፡፡

አቶ ሳሙኤል አያይዘዉም የቀረበዉ እቅድ የተሻለ መሆኑን ጠቅሰዉ 2019ን የተሻለ እቅድ በማቀድ ለተፈጻሚነቱ ፍላጎትና አቅርቦትን ያማከለ እቅድ በማቀድ አሰራርና መመሪያን ተከትሎ በመስራት የአዲስ አበባ ከተማ አዉቶቡስ ድርጅት በከተማና በማህበረሰቡ ተመራጭና ታማኝ አገልጋይ መሆኑን በማስመስከር በአገልግሎት አሰጣጡ ተመራጭ በማድረግ ለዉጤት መብቃት አስፈላጊ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በመጨረሻም ከሰራተኛዉ የተነሱ የተቋምንም የባለድርሻ አካላትን ያማከለ አስተያየትና ቢስተካከሉ ላሉት አሰራሮች ባለ ድርሻ አካለቶችና አመራሮቹ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ለቀጣይ 2019 እቅድ አፈጻጸም የሚያጠናክር የጋራ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመዉ የዕለቱ መርኃ ግብር ተጠናቋል፡


https://www.facebook.com/citybus2015
ቴሌግራም:https://t.me/citbus
ዩቱብ:https://youtube.com/-f2t.
ኢሜል: [email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected]

ሲቲ ባስ ለአጠቃላይ የቴክኒክ ዘርፍ ሰራተኞች በአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም በአገልግሎት ስነ ባህሪ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 19/2018 ዓ.ም...
25/08/2026

ሲቲ ባስ ለአጠቃላይ የቴክኒክ ዘርፍ ሰራተኞች በአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር እንዲሁም በአገልግሎት ስነ ባህሪ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡
(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 19/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የቴክኒክ ስልጠና ዘርፍ አገልግሎት ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ፤የአሽከርካሪ ስልጠና ዳይሬክቶሬት ፤የማዕከልና የቅርንጫፍ የዘርፍ ዳይሬክተሮችና ቡድን መሪዎች እንዲሁም የ5 ቱም ቅርንጫፍ አጠቃላይ የቴክኒክ ዘርፍ አንጋፋ ባለሙያዎች በዋናዉ መስሪያ ቤት 22 እየሩስ ህንጻ የስብሰባ አዳራሽ የግንዘቤ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የስልጠናዉን ሰነድ ያቀረቡት በስልጠና ዳይሬክቶሬቱ አሰልጣኝ ባለሙያ የሆኑት አቶ ኤርማያስ በየነ ሲሆኑ የስልጠናዉ ዋና ዋና ይዘቶች የአገልግሎት ምንነት፤አገልግሎት አሰጣጥ ማለት ምን ማለት ነዉ፤ከቴክኒክ አንጻር የአገልግሎት ምንነት ፤ጥሩ የቴክኒክ አገልግሎት ምልክቶች ፤በቴክኒክና ስልጠና ዘርፍ የሚሰጡ አገልግሎቶች ፤የመልካም አገልጋይ ባህሪያት፤እንዲሁም የተቋም ተልዕኮ፤ራዕይና እሴቶችን ጠብቆ በተቋምና በስራ መስክ ሁሉም ሰራተኛ እሴት መጨመር እንደሚገባ ሰፋ ያለ ገለጻና ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

ዉይይቱን የመሩት የቴክኒክና ስልጠና ዘርፍ ም/ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዳነ አብደታ እንደገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ አዉቶቡስ አገልግሎት ድርጅት በቀን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች በተመጣጣኝ ታሪፍ የሚያገለግልና ማህበራዊ ኃላፊነቱን የሚወጣ በመሆኑ ተቋሙ የሰራተኞችን ክህሎት ማዕከል ያደረገ የአቅም ግንባታ ስራ ለወደፊቱም በስፋት ይሰጣል ያሉ ሲሆን ይህም ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የቴክኒክ ጥገና ስራዎችን በብቃት ለመፈጸም እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት እንደሚረዳ ተመላክቷል፡፡

ኃላፊዉ አያይዘዉ ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደ ሲቲ ባስ አገልግሎት ሰጭ ተቋም ውጤታማነት ወሳኝ ነዉ ያሉ ሲሆን ስልጠናው በዋነኝነት ያተኮረው የሚከተሉትን ሶስት መሠረታዊ ዘርፎችን ለማጠናከር መሆኑን ጠቅሰዉ ፡-
1.የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል፡- ለተገልጋዮች ፈጣን፣ ቀልጣፋ እና ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችሉ አሰራሮችን ተግባራዊ ለማድረግ፤
2.የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን መተግበር፡- ግልጽነት፣ ተጠያቂነት፣ ህገወጥነት እና ሁሉን አቀፋዊነት በስራ ሂደት ውስጥ ማስፈን።
3.የአገልግሎት ስነ-ምግባርን ማጎልበት፡- በሙያዊ ባህሪ፣ ለደንበኞች አክብሮት እና ኃላፊነት በመወጣት ረገድ ያለውን ክፍተት መሙላት እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡

ወ/ሮ ሙሌ ደሳለኝ የተቋሙ የስልጠና ዳይሬክቶሬት እንዳሉት ቴክኒክ ባለሙያዎች ጥራት ያላቸው ሥራዎንችን ከተቋሙ ራዕይ ጋር ተናቦ መሥራት ውጤት ያስገኛል በማለት አንድ ቴክኒክ ባለሙያ የሥራ ሂደቶችን ለማቀላጠፍ፣ ጉድለቶችን ለመቀነስ እና የአገልግሎት ጊዜን ለማሳጠር ተናቦና ተግባቦትን ጨምሮ መስራት ለተቋም አጠቃላይ ስኬት አስተዋጽኦ ያደርጋል ብለዋል።

በመጨረሻም ተሳታፊዎቹ ተቋሙ በበርካታ ዘርፎች መዘመኑን ጠቅሰዉ ስልጠናዉ አመርቂና አነቃቂ በመሆኑ የቀረበዉን የስልጠና ሰነድ በተግባር ለማዋልና አገልግሎቱን የተሻለ ለማድረግ የተቋምን ስምና ተግባር ከፍ እንዲል እንደሚሰሩ የገለጹ ሲሆን የስራ ኃላፊዎቹ ለተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪ የሰጡ ሲሆን በመልዕክታቸዉ በቀጣይ የተቋምን ስም ከፍ የሚያደርጉ ጥቃቅን ስራዎችን በመስራት መኪኖችን ለስምሪት አገልግሎት እንዲዉሉ በማድረግ ለተገልጋዮች ምላሽ የመስጠት ተግባርን አጠናክሮ በመቀጠል እንደነዚህ ያሉ ስልጠናዎች የሰራተኞችን የሙያ ብቃት ከማሳደጉም በላ

22/08/2026
የነዳጅ አስተዳደርን የበለጠ ግልጽ፣ ተጠያቂ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ስልጠና ተሰጠ፡፡(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የፋይናን...
22/08/2026

የነዳጅ አስተዳደርን የበለጠ ግልጽ፣ ተጠያቂ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ስልጠና ተሰጠ፡፡

(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዘርፍ ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ፤የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ፤ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ፤እና የቅርንጫፍ የነዳጅ ስርጭት ባለሙያዎች በዋናዉ መስሪያ ቤት የማኔጅመንት አዳራሽ ዉይይት አካሄዱ፡፡

አቶ ይበልጣል ታምሬ የአዲስ አበባ ከተማ አዉቶቡስ አገልግሎት ድርጅት ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ ለባለሙያዎቹ ባደረጉት ገለጻ የቴሌ ብር ነዳጅ አከፋፈል ፤አመዘጋገብ እንዲሁም አጠቃላይ አሰራሮቹን በሲስተም ለመጠቀም ታሳቢ ያደረገ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የተሰጠው ስልጠና ከሁሉም ቅርንጫፍ ለተዉጣጡ ባለሙያዎች ከወረቀት ኩፖን ወደ ሲስተም ክፍያ ለመሸጋገር በተደረገው አሰራር ሲሆን ይህ ለውጥ ግልጽነትን ለማሳደግ እና የነዳጅ አስተዳደርን ውጤታማነት ለማሻሻል ያለመ ነው።

የስልጠናው ዋና ዓላማ ሰራተኞች አዲሱን የቴሌ ብር ስርዓት በብቃት እንዲጠቀሙ ማዘጋጀት ሲሆን ስልጠናዉ ከስርዓቱ ጋር በቀጥታ ለሚገናኙ የተለያዩ ባለሙያዎች የነዳጅ አስተዳደርን የበለጠ ግልጽ፣ ተጠያቂ እና ቀልጣፋ ለማድረግ እና በአሰራሩ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ በመሆኑ ተመላክቷል ፡፡
በመጨረሻም ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች የስራ ሃላፊዎቹ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

https://www.facebook.com/citybus2015
ቴሌግራም:https://t.me/citbus
ዩቱብ:https://youtube.com/-f2t.
ኢሜል: [email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected]

ሙስና ስጋት የማይሆንባትን ሀገር እንፈጥራለንየአዲስ አበባ ከተማ የስነ ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን በ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ግማሽ በጀት አመት አፈጻጸም ምዘና ከሐምሌ 14 ቀን 22018 ዐም...
21/08/2026

ሙስና ስጋት የማይሆንባትን ሀገር እንፈጥራለን

የአዲስ አበባ ከተማ የስነ ምግባርና ጸረ-ሙስና ኮሚሽን በ2018 ዓ.ም የሁለተኛ ግማሽ በጀት አመት አፈጻጸም ምዘና ከሐምሌ 14 ቀን 22018 ዐም ጀምሮ ሲያካሂድ የቆየ ሲሆን በዚሁ መሰረት ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በተቋማችን ሥር ካሉ ምዘና የተደረገላቸው ቅርንጫፎችን በማወዳደር ከ1-3 ለወጡት ዕውቅና ሰጥቷል፡፡
የተሰጣቸውን ተግባራና ሃላፊነት በመወጣትና በእቅዳቸው መሰረት ተግባራዊ በማድረግ በአፈጻጸማቸው የተሻለ የሆኑና በምዘናውም የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ቅርንጫፎች የተሸለሙ ሲሆን በቅደም ተከተላቸው እንደሚከተለው የምዘና ውጤት አግኝተው እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡

1. ቃሊቲ ቅርንጫፍ የሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል 1ኛ ወጥቷል፣
2. ሸጎሌ ቅርንጫፍ የሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል 2ኛ ወጥቷል፣
3. የካ ቅርንጫፍ የሥነ ምግባር መከታተያ ክፍል 3ኛ ወጥቷል፣
ለበለጠ መረጀ ነጻ ስ.ቁ 8981
https://www.facebook.com/citybus2015
https://www.tiktok.com/.bus7
[email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected]

21/08/2026
በሲቲ ባስ  ለሰራተኞች የቅድመ መከላከል የህክምና ምርመራ ተካሄደ፡፡(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 14/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የህክመና አገልግሎት ዳይ...
21/08/2026

በሲቲ ባስ ለሰራተኞች የቅድመ መከላከል የህክምና ምርመራ ተካሄደ፡፡

(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 14/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የህክመና አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከአለርት አጠቃላይ ሆስፒታል (ALERT Comprehensive Specialized Hospital) ጋር ለሰራተኞቹ የህክምና ቅድመ ምርመራ በዛሬዉ ዕለት አካሄደ ።

የአዲስ አበባ ከተማ አዉቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የህክምና አገልግሎት ዳይሬክተር ተወካይ የሆኑት ሲ/ር የሺ ጸጋዬ እንደገለጹት በአብዛኞቹ የስራ ቦታዎች መደበኛ የጤና ምርመራ ማድረግ የተለመደ እንዳልሆነ እና ብዙ ሰራተኞች የህመም ምልክት ከታየ በኋላ እንጂ ለመከላከል ሲባል ምርመራ አያደርጉም፣ ይህም በኋላ ላይ ወደ ከፍተኛ የህክምና እና ወጪ ያደርሳል። በዚህም የህክምና ዳይሬክቶሬቱ የሰራተኞችን ጤና እና ደህንነት ለመጠበቅ በቅድመ መካላከልና አክሞ በማዳን ላይ አቅዶ የሚሰራ ሲሆን በዚህም ሁሉም ሰራተኛ ተጠቃሚ የሚሆንበትና ሳይንገላታ በተቋሙ ቅጥር ግቢ ቅድመ ምርመራ አድርጎ እራሱን የሚያዉቅበት እንዲሁም በሽታዎችን ቀድመው ለይቶ ለማወቅ እና ለማከም ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሲ/ር የሺ ማንኛዉም ሰራተኛ የህክምና ምርመራ ማድረግ ግዴታዉ መሆኑን ጠቅሰዉ በዕለቱ ምርመራ የሚደረግባቸዉ የህክምና ዘርፎች የቆዳ ምርመራ፤ የአይን ምርመራ፤ የዉስጥ ደዌ እና የስነ አይምሮ ሲሆኑ በዚህም በህክምና ቡድኑ ከ1000 በላይ ሰራተኞች የዕድሉ ተካፋይ መሆን ችለዋል ብለዋል፡፡

በአለርት ሆስፒታል የቤተሰብ ህክምናና የማህበረሰብ ጤና ዲፓርትመንት ኃላፊና የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች አስተባባሪ ዶ/ር ቢያድግልኝ አጥናፉ እንዳሉት በመንግስት ደረጃ ጤና ሚንስትር ባወረደዉ አቅጣጫ መሰረት እንደ አለርት ሆስፒታል በተቋማትና ብዙኃን ማህበረሰብ መገኛ በሆኑ አደባባዮች ላይ በመገኘት ባጠቃላይ ከ 120ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቅድመ ምርመራ ለማድረግ እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡

ዶ/ር ቢያድግልኝ አያይዘዉም 30 አባላትን ያካተተ በ4 ቡድን ተከፋፍሎ ማለትም በዉስጥ ደዌ ፤በአይን ምርመራ ፤በስነ አይምሮ እንዲሁም በቆዳ ምርመራ ላይ ምርመራዉ የሚደረግ ሲሆን ይህ ተግባር ከክረምት ዕቅዳቸዉ አንዱ ሲቲ ባስ መሆኑን በመጥቀስ የተቋሙ ሰራተኛ ሳይንገላታ ባለበት ቦታ በመገኘት ጊዜዉን ፤ጉልበቱን እንዲሁም ስራዉን ሳይበድል ጤናዉን እንዲያዉቅ ለማድረግ ያለመ ነዉ ሲሉ አብራርተዋል፡፡

በመጨረሻም ዶ/ር ቢያድግልኝ በመልዕክታቸዉ ይህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በየዓመቱ የሚከናወን መሆኑን በመጥቀስ ማንኛዉም ሰዉ የጤናዉን ደረጃ ለማወቅ በየ6 ወሩ ምርመራ ማድረግ እንዳለበት በመግለጽ ማንኛዉም ተቋም ጥያቄ በማቅረብ ባለበት ተጠቃሚ ቢሆኑ ሲሉ ገልጸዋል፡፡

https://www.facebook.com/citybus2015
ቴሌግራም:https://t.me/citbus
ዩቱብ:https://youtube.com/-f2t.
ኢሜል: [email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected]

ለኦፕሬሽን ሰራተኞች   የአገልግሎት አሰጣጥና አተገባበር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል። (የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገል...
17/08/2026

ለኦፕሬሽን ሰራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥና አተገባበር ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

(የከተማ አዉቶቡስ ፤ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት የማዕከል አመራሮች፤ የ5ቱም ቅርንጫፍ ስራ አስፈጻሚዎች ፤ የዘርፍ ዳይሬክተሮች፤ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ያሳተፈ ዉይይት አካሄደ።

ስልጠናዎቹ በአገልግሎት አሰጣጥ እና ስነ ባህርይ ዙሪያ ለድርጅቱ ለኦፕሬሽን አገልግሎት ሰጭ ሰራተኞች የተዘጋጀ ቀጣይነት ያለው ግንኙነትና ንቃተ-ህሊና በመፍጠር የአሽከርካሪዎችን ፤የአገልግሎት ክፍያ ተቀባዮች፤ በስምሪትና ቁጥጥር ሰራተኞች ላይ ባህሪ ለውጥ ለማምጣት ያለመ ስልጠና ነዉ ።

ስልጠናዉ የተሰጠዉ በተቋሙ ዉስጥ ረዘም ላለ ጊዜ ሲያገለግሉ የነበሩ ልምድና እዉቀትን ያጣመሩ አሰልጣኞች ሲሆኑ ስልጠናዎችም የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ከመቀነስ ባለፈ የተቋሙን ወጪ በመቀነስ፣ የአገልግሎቱን እንቅስቃሴ ማሳለጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እና የህብረተሰቡን የትራንስፖርት እርካታ ለመጨመር ጉልህ አስተዋጽኦ ያላቸዉ ናቸዉ።

በስልጠናዉ የተላለፋ መረጃዎች ትኩረት ካደረጉባቸዉ ነጥቦች አገልግሎት ማለት ምን ማለት ነዉ፤የአገልግሎት አሰጣጥ ምንነት፤ የአገልግሎት መሰረታዊ ባህሪያቶች፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ወቅት መሟላት ያለባቸዉ ቅድመ ሁኔታዎች፤ የዉጤታማ አገልግሎት ደረጃዎች፤ የተገልጋ አይነቶች በመረዳት በማወቅ የተቋምን ራዕይ፤ተልዕኮና እሴት ማወቅና ማሳወቅ ላይ ያለመ መሆኑ በዉይይቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ይህ ስልጠና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት እና ግልጽ የአሠራር ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ መሆኑ፤ስልጠናዉ የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል በሚሰጡ ስልጠናዎች ላይ ያተኮረ መረጃ የተላላፈበት፤ በሥነ-ምግባር እና የባህሪ ለዉጥ ሥርዓት ላይ ያተኮረ፤ ተቋሙ ሠራተኞች በሥነ-ምግባራዊ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ከአርብ ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ተጠናቀቀ። የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ ሠራተኞች ለተገልጋዩ ህብረተሰብ በተሻለ ሥነ-ምግባር ደህንነቱ የተጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ነው።

በአጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል የተለያዩ የስልጠና ፕሮግራሞችን እያካሄደ ሲሆን የአሁኑም ስልጠና ስኬታማና ለዉጥ ማምጣት የሚያስችል መሆኑ የተገጸ ሲሆን ከሰራተኞቹ ለተነሱ ሰፋ ያለ ጥያቄና አስተያየት የስራ ኃላፊዎቹ ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት መርሃ ተጠናቋል ።

https://www.facebook.com/citybus2015
ቴሌግራም:https://t.me/citbus
ዩቱብ:https://youtube.com/-f2t.
ኢሜል: [email protected]" rel="ugc" target="_blank">[email protected]

Address

Bole Sub City
Addis Ababa
22MAZOREA/EPUATORALGUINEASTREET(ADJIACENTTOMEKELITBUILDING)ADDISABABA,

Opening Hours

Monday 02:30 - 22:00
Tuesday 02:30 - 22:00
Wednesday 02:30 - 22:00
Thursday 02:30 - 22:00
Friday 02:30 - 22:00
Saturday 02:30 - 18:30

Telephone

+251986894700

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa City Bus Service Enterprise አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis Ababa City Bus Service Enterprise አዲስ አበባ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት:

Shortcuts

Share