Demba Gofa Woreda Government Communication Affairs Office

Demba Gofa Woreda Government Communication Affairs Office በጎፋ ዞን ደምባ ጎፋ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽንጉዳዮች ጽ/ቤት

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእመርታ ቀን መልዕክት ***************************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 1 ቀን የእመርታ ቀንን በማስመል...
06/09/2026

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእመርታ ቀን መልዕክት
***************************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጳጉሜን 1 ቀን የእመርታ ቀንን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል ብለዋል።

ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንደምንገኝ አስታውሰዋል።

ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን።

እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የህዝብ ተሳትፎ  ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመፍታት በመሎ ኮዛ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ የልማት ስራዎች ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው  -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን...
05/09/2026

የህዝብ ተሳትፎ ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመፍታት በመሎ ኮዛ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ የልማት ስራዎች ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ናቸው -ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ የመንግስትና የፓርቲ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት፤ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በራስ አቅም በመፍታት የአካባቢውን ዕድገትና ልማት ለማፋጠን በወረዳው አስተዳደርና ሕዝብ የጋራ ትብብር ከ344 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ 11 ማሽነሪዎች እና የእርሻ ትራክተሮች ምረቃና ቀጣይ የልማት ትብብር መርሃ ግብር በላሃ ከተማ ተካሂዷል ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በመርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በኢንቨስትመንት በቱሪዝም በርካታ ፀጋ የታደለው መሎኮዛ ወረዳ በመሰረተ ልማት ችግር ምክንያት ባለው ፀጋ ልክ መልማት አለመቻሉን ገልፀው ይህንን ችግር ለመቅረፍ ወረዳው ህብረተሰቡን በማስተባበር በራስ አቅም ችግሩን ለመሻገር የመንገድ ማሺነሪዎችን በመግዛት ያሳየው ትጋት የሚደነቅ ነው ብለዋል።

የወረዳው አስተዳደር የህዝቡን የዘመናት የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄ፤ በህዝብ ግንባር ቀደም ተሳትፎ በራስ አቅም በብቃት በመመለስ ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ፤ "ዶሮ ሸጠን ዶዘር እንገዘላን"! በሚል መሪ ሃሳብ ባካሄደው ውጤታማ ንቅናቄ የመንገድ ልማት ማሽነሪዎችን ጨምሮ ለመካናይዝድ ግብርና ልማት የእርሻ ትራክተሮች መግዛት በመቻሉ በክልሉ መንግስት ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በክልሉ በየአካባቢው አዳጊ የልማት ጥያቄዎች ብቻ ሳይሆን በርካታ ፀጋዎችና የመልማት አቅሞች አሉ ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ፀጋዎችን በአግባቡ ገልጦ ወደ ሀብት መቀየር እና ህዝቡን የልማቱ ባለቤት ባደረገ መልኩ በመስራት በራስ አቅም በርካታ የልማት ጥያቄዎችን በብቃት መመለስ እንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ረገድ የመሎ ኮዛ ወረዳ እና የላሃ ከተማ አስተዳደር በጋራ ህዝብ በማስተባበር ቁልፍ የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በራስ አቅም በብቃት መመለስ የሚያስችሉ 11 ማሽነሪዎች መግዛት መቻላቸው ዕውቅና የሚሰጠው፤ ሌሎች መዋቅሮች ምሳሌ የሚሆንና ተሞክሮ ልወስድበት የሚገባ ውጤታማ የልማት ተግባር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የመንገድ መሠረተ ልማት በተለይ የኢኮኖሚ ዕድገት የደምስር ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ በወረዳው ከፍተኛ ሃብት በማሰባሰብ የተገዙ ማሽነሪዎችን በአግባቡ ጥቅም ላይ በማዋል የህዝቡን የዘመናት የመንገድ ጥያቄዎች በተጨባጭ በመመለስ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

በአካባቢው በራስ አቅም የሚከናወነው የመንገድ መሠረተ ልማት ዝርጋታ፤ የአርሶ አደሩን ምርታማነት በማሳደግ ከምርቱ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን በማሳለጥ የወረዳውን ዕድገትና ልማት የሚያፋጥን መሆኑንም ገልፀዋል፡፡

በመሎ ኮዛ ወረዳ በተግባር እንደታየው ለለውጥ በሚተጋ ቁርጠኛ አመራር፤ ህዝብ አስተባብሮ የውስጥ አቅምን በማጎልበት ከተሰራ ባጭር ጊዜ ውስጥ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል መገንዘብ ይገባል ሲሉ አስምረዋል፡፡

ለዚህ በየአካባቢው ያሉ ፀጋዎችን ለይቶ ወደ ሀብት ምንጭነት በመቀየር የውስጥ አቅምን ማጎልበት እንዲሁም የግሉን ዘርፍ፤ የህብረተሰቡን እና የሌሎች አጋር አካላት ተሳትፎን ማረጋገጥ እና እንደ መሎ ኮዛ ወረዳ ያሉ መልካም ተሞክሮዎች በመቀመር መስራት ለውጤታማነት ቁልፍ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የክልሉ መንግስት ባለፉ ጊዜያት ለኢኮኖሚያዊና ለማህበራዊ ብልፅግና ትልም ስኬት መሰረት ለሆነው የመንገድ መሠረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት፤ ፍትሃዊ ተደራሽነቱን ለማሳደግ በተሰራው ስራ ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱንም ገልፀው፤ በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

ችግሮችን መፍታት የምንችለው አንድ ስንሆን ነው መሎዎች አንድ በመሆኑ ስኬት አስመዝግበዋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ያለንን ጉልበት፤ ዕውቀት እና ሃብት አቀናጅተን በራስ አቅም ችግሮቻችንን ለመፍታት ከተባበርን እና በኅብረት ለጋራ ልማት ከተጋን፤ ሁለንተናዊ ልማትና ብልፅግናችንን ባጭር ጊዜ ውስጥ በእጃችን ማረጋገጥ እንችላለን በማለት ሃሳባቸውን አጠቃለዋል፡፡

ክቡር ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በመሎ ኮዛ ወረዳ ላሃ ከተማ በተዘጋጀው  የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመፍታት በነበራቸው አስተዋፅኦ ላበረከቱት ድጋፍ እውቅና ተሰጣቸ...
05/09/2026

ክቡር ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በመሎ ኮዛ ወረዳ ላሃ ከተማ በተዘጋጀው የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በራስ አቅም ለመፍታት በነበራቸው አስተዋፅኦ ላበረከቱት ድጋፍ እውቅና ተሰጣቸው

በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በራስ አቅም በመፍታት የአካባቢውን ዕድገትና ልማት ለማፋጠን በወረዳው አስተዳደርና ሕዝብ የጋራ ትብብር ከ344 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ ማሽነሪዎች እና የእርሻ ትራክተሮች ምረቃና ቀጣይ የልማት ትብብር መርሃ ግብር በላሃ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

የክልሉ መንግስት በህብረተሰብ ተሳትፎ በተገዛው ማሽነሪ ድጋፍ 25 ሚሊዬን ብር ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም የግዢ ሂደቱ እንዲፋጠን በማድረግ እገዛ አድርጓል።

ክቡር ርዕሰ መስተዳድር በመሎ ኮዛ ወረዳ ላሃ ከተማ በተዘጋጀው የምረቃ መርሃ ግብር ለነበራቸው አስተዋፅኦ ላበረከቱት ድጋፍ እውቅና ሰጥቷቸዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ ፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የላሃ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ  አገልግሎት የማዘመን ስራ ተጠናቆ  በይፋ  አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ርዕሰ መስተዳድ...
05/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የክልሉ ፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የላሃ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የማዘመን ስራ ተጠናቆ በይፋ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና የክልሉፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት፤ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ በላሃ ከተማ አስተዳደር፤ የላሃ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በይፋ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፥ የክልሉ መንግስት ከተሞችን በህብረተሰቡ ተሳትፎ ፅዱና ለኑሮ ምቹ ከማድረግ ባሻገር ወደ ብልፅግና የሚደረግ ጉዞን የሚያሳልጡ የኢኮኖሚያዊ ዕድገትና የማህበራዊ ሽግግር ማዕከላት እንዲሆኑ ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በመሎ ኮዛ ወረዳም ሆነ በላሃ ከተማ በርካታ ፀጋዎች ያሉ መሆኑንም ጠቅሰው፥ ፀጋዎችን ወደ ሀብት በመቀየር ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ ለማድረግ የተጀመሩ አበረታች ስራዎች ተጠናክረው ልቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በተቀላጠፈ አሰራርና አገልግሎት አሰጣጥ የከተሞች ዕድገትን ማሳለጥ በከተሞች ኢንቨስትመንትን ከመሳብ ባሻገር የክልሉን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያፋጥን ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ አመራሩ ተገቢውን የመሪነት ሚና በመወጣት በከተማው የአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት በይፋ ማስጀመር በመቻሉ አመስግነዋል፡፡

ዘመናዊ የተሳለጠ የአንድ ማዕከል ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የከተሞች ተወዳዳሪነት እና ተመራጭነትን በማሳደግ ቀጣይነት ላለው ልማት ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡

የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ በዲጂታላይዜሽን የታገዘ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ዘርፈ ብዙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መቅረፍ የሚያስችል ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

ከተሞችን ለማሳደግና ለመቀየር ወሳኙ የከተማ ነዋሪው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ ለከተሞች ቀጣይነት ያለው ልማት ግንባር ቀደም የህብረተሰብ ተሳትፎ እና ጠንካራ የማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ መሠረታዊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

መሠረተ ልማት የተሟላላቸው፤ የለሙና ለኑሮ ምቹ የሆኑ ስማርት ከተሞችን ለመፍጠር የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅትና ርብርብ አስፈላጊ መሆኑንም በአጽንኦት ገልፀዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የተማሏ የዲጂታላይዜሽን አገልግሎት በመዘርጋት ስማርት ከተሞችን ለመገንባት ለተያዘው ውጥን የተጀመሩ ስራዎች ተስፋ ሰጪ መሆናቸውንም ጠቅሰው፤ በቀጣይም ወደ ሌሎች ከተሞች በማስፋትና በማዘመን ከተሞች የብልፅግና ማዕከላት እንዲሆኑ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ይፋዊ የስራ ቆይታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለይፋዊ የስራ ጉዳይ ወደ ጎፋ ዞን በማቅናት፤ በዞኑ መሎ ኮ...
05/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ይፋዊ የስራ ቆይታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለይፋዊ የስራ ጉዳይ ወደ ጎፋ ዞን በማቅናት፤ በዞኑ መሎ ኮዛ ወረዳ በላሃ ከተማ ይፋዊ የስራ ቆይታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡

ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ ለይፋዊ የስራ ቆይታው፤ በመሎ ኮዛ ወረዳ ሲደርሱ እና በወረዳው ከፍተኛ አመራሮች፤ በሀገር ሽማግሌዎች እና በአካባቢው ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ በወረዳው በሚኖራቸው ቆይታ የተለያዩ የልማት ስራዎች የሚጎበኙ ሲሆን፤ በተለይ የግብርና ልማትና የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ተግባራትን ጨምሮ የላሃ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ የአንድ ማዕከል አገልግሎትንና ሌሎች የጎላ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸው የልማት ፕሮጀክቶች መርቀው በይፋ አገልግሎት ያስጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

በጎፋ ዞን በመሎኮዛ ወረዳ እና በላሃ ከተማ በማህበረሰብ ተሳትፎ የተገዙ ማሽነሪዎችን ለማስመረቅ ለመጡት ለርዕሰ መስተዳደሩ ደማቅ አቀባበል ተደረገሣውላ፦ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮ...
05/09/2026

በጎፋ ዞን በመሎኮዛ ወረዳ እና በላሃ ከተማ በማህበረሰብ ተሳትፎ የተገዙ ማሽነሪዎችን ለማስመረቅ ለመጡት ለርዕሰ መስተዳደሩ ደማቅ አቀባበል ተደረገ

ሣውላ፦ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን በመሎ ኮዛ ወረዳና በላሃ ከተማ አስተዳደር በማህበረሰብ ተሳትፎ የተገዙ የልማት ማሽነሪዎችን ለመመረቅ ወደ ዞኑ ባደረጉት ጉዞ በበልጣ ቀበሌ ደማቅና ልዩ አቀባበል ተደረገላቸው።

በአቀባበሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊና የሶዶ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ተፈሪ አባተን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር ዳግማዊ አየለ፣ የዞኑ አስተባባሪ አካላትና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳደሩና የተመራው የልዑካን ቡድን በጎፋ ዞን በሚያደርጉት የሥራ ጉብኝት በመሎ ኮዛ ወረዳ ቶባ ቀበሌ የሚመረተውን የኮሬሪማ ምርት ይጎበኛሉ።

በተጨማሪም በአካባቢው የቱሪዝም እምቅ አቅምን ለማልማት በመስህብነት እየተገነቡ ያሉትን የቱሪሚ ዋሻና የመንቲያ ፏፏቴ ይጎበኛሉ።

ጉብኝቱ ከዚህም ባሻገር ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለሚደረገው ሽግግር መሠረት የሚጥሉ የልማት ሥራዎችን ያካትታል። በዚህም የምርት መሰብሰቢያ መካዝን ግንባታ ሥራዎችን በቦታው በመጎብኘት የአፈጻጸም ምልከታ ያደርጋሉ።

በላሃ ከተማ ደግሞ ለሕዝቡ ዘመናዊና ተቀራራቢ አገልግሎት ለመስጠት የተገነባውን ዘመናዊ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በይፋ መርቀው እንደሚከፍቱም ይጠበቃል።

የጉዞው ዋና መርሃ ግብር ደግሞ በመሎ ኮዛ ወረዳና በላሃ ከተማ አስተዳደር በማህበረሰብ ሰፊ ተሳትፎና በተባበረ ክንድ የተገዙ ማሽነሪዎችን በይፋ የመመረቅ ሥነ-ሥርዓት ነው።
የማሽነሪዎቹ ግዥ በማህበረሰቡ የጋራ ተሳትፎ መፈጸሙ፣ ህዝቡ ለአካባቢው ልማትና ለጋራ ችግሮች መፍትሔ በመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።

በመሆኑም ርዕሰ መስተዳደሩ ከህዝቡ ጋር በመሆን የዚህ ታላቅ የልማት ሥራ የደስታ ተካፋይ ሆነው ማሽነሪዎቹን በይፋ ይመርቃሉ። ይህም በጎፋ ዞን የመሎኮዛ እና የላሃ ከተማ አስተዳደር የህዝብ ተሳትፎን መሠረት ያደረገ የልማት እንቅስቃሴ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳይ አበረታች ተሞክሮ እንደሚሆን ይጠበቃል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ምክር ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠበርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ሰብሳቢነት የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት በተለያ...
04/09/2026

የክልሉ አደጋ ስጋት ምክር ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ

በርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ሰብሳቢነት የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመምከር ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

ምክር ቤቱ በመደበኛ የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ስራዎች ሁኔታ፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ከማስጠበቅ አኳያ በአደጋ ስጋት ስራ አመራ የተሰሩ ስራዎች አፈጻጸም፣ ለአደጋ በተጋለጡ አካባቢዎች የተከናወኑ የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ፣ በተሻሻለው የአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ አፈፃፀም በተመለከቱ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቷል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በውይይቱ የበልግ ዝናብ በመጠንም በስፋትም እየቀነሰ መምጣት እና የመህር ዝናብ መዘግየት የውሃ አመራጮች ላይ ችግር እየፈጠረ እንደሚገኝ እና የሰውና የእንስሳት ጤና ላይ ችግር ሊያስከትል የሚችልበት ሁኔታ ስላለ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ አሳውቀዋል።

የአደጋ ስጋት ምክር ቤቱ አባላንት ጨምሮ ሌሎች ከክልሉ የተወጣጣ ቴክኒኮ ኮሚቴ ተቋቋሞ እቅድ በማዘጋጀት ከኢሊኖ ክሰተት ጋር ተያይዞ በሰውና በእንስሳት ጤና ላይ ልያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመከላከልና ለመቀነስ የሚያስችል የልየታ እና የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።

በተለይ ህፃናት እና እናቶችን በምግብ እጥረት እንዳይጎዱ የስረዓቱ ምግብ ኒውትርሽን ስራ በልዩ ትኩረት መመራት እንዳለባት ገልፀው ከእንሳስትን ጤናም አኳያ ልዩ ክትትል ማድረግ፤ የመኖ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ በሰጡት ሀሳብ ፡- ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነት በመሸጋገር በክልሉ በሁሉም መዋቅሮች በመከናወን ላይ ባሉ ተግባራት አፈጻጸም መሻሻሎች መኖራቸውን ገልፀዋል።

አስቸኳይ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ነገሮችን የማሰባሰብ እና የማከማቸት ፣ ተማሪዎች በምግብ እጥረት ምክንያት ከትምህርታቸው እንዳይስተጓጎሉ የተማሪዎች ምገባን ፣ ተፈናቃይ የማቋቋም ስራዎችን ማጠቃለል ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል።

በራስ አቅም የሰብዓዊ ድጋፍ መሸፈን የሚያስችል አቅም ለመገንባት በመደረግ ላይ ያለው ርብርብ የሚያግዝ የተሻሻለ የአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ ወደ ተግባር ለመቀየር በክልል ደረጃ የተጀመሩ የህብረተሰብ ውይይቶችን በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች ተደራሽ በማድረግ፤ ለታለመው የአደጋ ጊዜ የመጠባበቂ ፈንድ የሚውል ገንዘብ በአፋጣኝ ከዚህ ወር ጀምሮ የማሰባሰብ ስራውን መጀመር እንደሚገባ አስውቀዋል።

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

“ሣውላን እንደገና እንሰራለን!” በሚል መሪ ቃል ለተጀመረው የከተማዋ ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር  ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ 12,000 ...
04/09/2026

“ሣውላን እንደገና እንሰራለን!” በሚል መሪ ቃል ለተጀመረው የከተማዋ ኮሪደር ልማት ማስጀመሪያ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ 12,000 (አሥራ ሁለት ሺህ) ብር ድጋፍ አድርገዋል።

እርስዎም የዚህ ታሪካዊ የከተማ ልማት አካል ለመሆን፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000787967829 ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

በጎፋ ዞን አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ መርሐ ግብሮች በድምቀት ይከበራሉ:-የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት!ሣውላ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ምወደ አዲስ ዓመት የምንሸጋገርበት የጳጉሜ...
04/09/2026

በጎፋ ዞን አምስቱ የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ መርሐ ግብሮች በድምቀት ይከበራሉ:-የዞኑ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት!

ሣውላ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም

ወደ አዲስ ዓመት የምንሸጋገርበት የጳጉሜን ወር፣ ያለፈውን ዓመት ስኬት የምንገመግምበት፣ ያጋጠሙንን ክፍተቶች የምንለይበትና ለነገው የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋና ብርታት የምንሰንቅበት ልዩ የዘመን መሸጋገሪያ ወቅት ነው።

በዚሁ መነሻ፣ በጎፋ ዞን የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን አምስቱ ቀናት በተለያዩ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ልማታዊ፣ የሰላም፣ የኅብረትና የቴክኖሎጂ መርሐ ግብሮች በንቅናቄና በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ።

የጎፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ የትምጌታ ተስፋዬ የጳጉሜን ቀናትን አከባበር አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶችን በፅናት በመሻገር በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚያዊ መስኮች ጉልህ ድሎችን እያስመዘገበች ወደ ከፍታ የማንሠራራት ምዕራፍ መሸጋገሯን ገልጸዋል።

የጎፋ ዞንም የሀገራችን የለውጥና የማንሠራራት ጉዞ አካል በመሆን፣ ባለፉት ዓመታት በልማት፣ በግብርና፣ በመሠረተ ልማት፣ በማኅበራዊ አገልግሎቶችና በሕዝብ ተሳትፎ ዘርፎች ሁለንተናዊ ለውጦችን በማስመዝገብ የከፍታው ጉዞ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ ሆኖ መቀጠሉን አመልክተዋል።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ውስጥ ያለፈውን ዓመት በስኬት የምናጠቃልልበትና ወደ አዲሱ ዓመት በአዲስ ራዕይ የምንሻገርበት የተስፋ ድልድይ መሆኑን አቶ የትምጌታ ጠቅሰው፤ የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት አንኳር ስኬቶች በማስታወስና የቀሩ ተግባራትን በማረም ለቀጣዩ ዓመት የተሻለ አፈጻጸም መሠረት የሚጣልበት ወቅት መሆኑን አብራርተዋል።

የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበርም ለሀገራችን ልዩ ታሪካዊ ወቅት ላይ በመዋሉ ልዩ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ይሁንታ የተመረጠው ፓርቲ መንግሥት በሚመሠርትበትና የሕዝብን አደራ ለመወጣት ዝግጅት በሚደረግበት እንዲሁም የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ውጤቶችን ወደ ተግባር ለመለወጥ ጠንካራ ዝግጅት በሚደረግበት ወቅት መከበሩ በዓሉን ይበልጥ ታሪካዊና ትርጉም ያለው እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።

የጳጉሜን ቀናትን በዞኑ በተቀናጀና በተደራጀ መንገድ ለማክበርም በዞን ደረጃ ዐቢይና ንዑሳን ኮሚቴዎች ተደራጅተው ወደ ሙሉ የተግባር ምዕራፍ መግባቱን አቶ የትምጌታ ገልጸዋል። ኮሚቴዎቹም ከዞን እስከ ወረዳና ከተማ መዋቅር ድረስ በተዋረድ በመደራጀት በዕቅድ የተያዙ መርሐ ግብሮች በአንድነትና በተቀናጀ መልኩ እንዲፈጸሙ እየሠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ጳጉሜን 1 – “የእምርታ ቀን”

የጳጉሜን የመጀመሪያ ቀን “የእምርታ ቀን” በሚል መሪ መልእክት ይከበራል።

በዚህ ዕለት በሀገርና በዞን ደረጃ የተመዘገቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬቶች፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተገኙ ውጤቶች እንዲሁም በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ የተመዘገቡ ስኬቶች በትኩረት ይጎላሉ።

ከተረጂነት ወደ አምራችነት፣ ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከጥገኝነት ወደ ራስ በራስ መቻል የሚደረገውን የመዋቅር ሽግግር የሚያሳዩ ተግባራት በተለይ ትኩረት ያገኛሉ። የጎፋ ዞን የልማት አቅሞችን በማስፋትና ምርታማነትን በማሳደግ ለሕዝቡ የተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለመፍጠር እያደረገው ያለው ጥረትም ይቀርባል።

ጳጉሜን 2 – “የማንሠራራት ቀን”

ሁለተኛው የጳጉሜን ቀን “የማንሠራራት ቀን” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራል።

በዚህ ዕለት በየደረጃው የተመዘገቡ የልማትና የመሠረተ ልማት ውጤቶች በዜጎች ዕለታዊ ሕይወት ላይ ያመጡት ተጨባጭ ለውጥ በልዩ ልዩ ይዘቶችና ሁነቶች ይቀርባል።

የልማት ሥራዎች የመንገድ፣ የውሃ፣ የትምህርት፣ የጤናና የሌሎች መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት በሕዝቡ ሕይወት ላይ ያሳረፉትን አዎንታዊ አሻራ በማሳየት፣ የበለጠ ከፍታ ለማምጣት የሚጠይቁ ቀጣይ ተግባራትም ይታወሳሉ።

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

“የጽናት ቀን” የሆነው ጳጉሜን 3 የሀገርና የሕዝብ ሰላም፣ የሀገረ-መንግሥት ቀጣይነትና የሕዝብ ደኅንነት የሚጎላበት ቀን ይሆናል።

በዚህ ዕለት የፀጥታ መዋቅሮች ዘመናዊ ቁመና፣ በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ የተገነባው አቅም እንዲሁም ለሀገር ሰላምና ለሕዝብ ደኅንነት በመስዋዕትነት ያገለገሉ ጀግኖች በክብር ይዘከራሉ።

ሰላም የልማት መሠረት፣ ጽናት የድል ምንጭ መሆኑን በማስገንዘብ፣ መላው ሕዝብ የሰላም ግንባታ ላይ ያለውን ሚና በማጠናከር ቀኑ ይከበራል።

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

አራተኛው የጳጉሜን ቀን “የኅብር ቀን” በሚል መሪ መልእክት ይከበራል።

በዚህ ዕለት በለውጡ ዓመታት በተደረጉ ሪፎርሞች የተገኙ የብዙኃን አካታችነት ውጤቶች፣ ሀገር በቀል እሴቶች፣ የወል ትርክት ግንባታ ሂደቶች እና በጎፋ ዞን የሚገኘው የሕዝቦች አብሮነትና መተባበር በልዩ ትኩረት ይቀርባሉ።

የባህል እሴቶችን ማጎልበት፣ የአብሮነት መንፈስን ማጠናከር፣ የመረዳዳትና የበጎ አድራጎት ባህልን ማስፋፋት የዕለቱ ዋና መልእክቶች ይሆናሉ።

ጳጉሜን 5 – “የነገው ቀን”

የጳጉሜን የመጨረሻው ቀን “የነገው ቀን” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራል።

ቀኑ የኢትዮጵያን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ፣ የሳይበር ሉዓላዊነትን እና በ“5 ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ” መርሐ ግብር የተገኙ ውጤቶችን በማጉላት ይከበራል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ የዛሬን ሥራ ቀላል ከማድረግ ባሻገር የነገዋን ኢኮኖሚ፣ የትምህርት ሥርዓት፣ የሥራ ዕድልና የሀገር ተወዳዳሪነት የሚወስን ቁልፍ አቅም መሆኑ በተለያዩ የንቃተ ህሊና መርሐ ግብሮች ይገለጻል። በተለይ ወጣቱ ትውልድ በቴክኖሎጂ፣ በፈጠራና በዲጂታል ክህሎት ራሱን አብቅቶ የነገዋን ኢትዮጵያ በእውቀትና በፈጠራ የሚገነባበት ራዕይ ይጎላል።

በመሆኑም መላው የጎፋ ዞን ሕዝብ፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፀጥታ አካላት፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ማኅበረሰብ አደረጃጀቶችና ሁሉም የዞኑ ነዋሪዎች በጳጉሜን ቀናት አከባበር በንቃት እንዲሳተፉ አቶ የትምጌታ ተስፋዬ ጥሪ አቅርበዋል።

የጳጉሜን ቀናት ያለፉትን ድሎች በማስታወስ ብቻ የሚገደቡ ሳይሆኑ፣ ከስኬቶቻችን ብርታትን በመውሰድ፣ ከክፍተቶቻችን በመማርና ለቀጣዩ ዓመት በአንድ ራዕይ በመሰለፍ የበለጠ ከፍታ የምንቀይስበት የኅብረትና የተስፋ ቀናት መሆናቸው ተጠቅሷል።

“ያለፈውን በስኬት እንዘክር፤ ክፍተቶቻችንን በቁርጠኝነት እናርም፤ ለነገው ከፍታ በአንድነት እንቁም!”

በዚህም መላው የጎፋ ዞን ሕዝብ የተቀደሱ እሴቶቻችንን በማጎልበት፣ አብሮነታችንን በማጠናከር፣ ሰላምን በመጠበቅና ለነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ በጋራ በመቆም የጳጉሜን አምስቱን ቀናት በደማቅ ሁኔታ እንዲያከብር ጥሪ ተላልፏል።

መልካም የጳጉሜን ቀናት!
መልካም የአዲሱ ዓመት የመሸጋገር ወቅት!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Demba Gofa Woreda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share