Educational Assessment and Examinations Service-EAES

Educational Assessment and Examinations Service-EAES Educational Assessment and Examinations Service
(275)

23/08/2026

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር መሻሻል አሳይቷል - ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 16/2018 (ኢዜአ)፦ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ቁጥር መሻሻል ማሳየቱን የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።

የትምህርት ሚኒስቴር በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎችን ውጤት አስመልክቶ ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት፣ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን ለፈተና ከተመዘገቡት 563 ሺህ 960 ተማሪዎች መካከል 550 ሺህ 210 የሚሆኑት ፈተናውን ወስደዋል።

ከእነዚህም ውስጥ 70 ሺህ 544 ወይም 12.8 በመቶ የሚሆኑት ከ50 በመቶ በላይ በማምጣት ማለፍ ችለዋል።

በ2017 ዓ.ም ያለፉ ተማሪዎች ምጣኔ 8 ነጥብ 9 በመቶ ነበር።

እንደ ሚኒስትሩ ማብራሪያ፣ የማለፊያ ምጣኔው በትምህርት ዘርፎች ሲታይ በተፈጥሮ ሳይንስ 16.6 በመቶ፣ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል።

በከፍተኛ ውጤት ደረጃ በተፈጥሮ ሳይንስ በወንዶች በኦሮሚያ ክልል የአዳማ ኦዳ ስፔሻል ቦርዲንግ ትምህርት ቤት ተማሪ 591.6 ነጥብ በማምጣት ከፍተኛውን ውጤት ሲያስመዘግብ፣ በሴቶች ደግሞ ከአማራ ክልል እንጅባራ አገው ምድር ትምህርት ቤት ተማሪ 583 ነጥብ በማምጣት ከፍተኛውን ውጤት ይዛለች።

በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ በወንዶች ከፍተኛው ውጤት 576 እንዲሁም በሴቶች 569 ሆኖ ተመዝግቧል።

88 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ በአንጻሩ 565 ትምህርት ቤቶች ደግሞ አንድም ተማሪ ማሳለፍ ሳይችሉ ቀርተዋል።

ሚኒስትሩ አክለው እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ከባለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ቁጥር ያለው ተማሪ የማለፊያ ነጥብ በማስመዝገቡ ምክንያት ወደ ማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር ይቀንሳል።

ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ እና የማካካሻ ፕሮግራም ትክክለኛ የመቁረጫ ነጥብ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

23/08/2026

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 12 ነጥብ 8 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል

👉 በተፈጥሮ ሳይንስ (ከ600) - በወንድ 591.64 ፤ በሴት 583.03 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ ተመዝግቧል

👉 በማኅበራዊ ሳይንስ (ከ600) - በወንድ 576.25፤ በሴት 569.17 ከፍተኛ ሆኖ ተመዝግቧል
++++++++++++++

- የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 12 ነጥብ 8 በመቶ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤቶችን ይፋ ተደርገዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ለፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች 50 በመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ የቻሉት 12 ነጥብ 8 በመቶ ወይም 70 ሺህ 544 ተማሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው ዓመት በተሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 8 ነጥብ 9 በመቶ ተማሪዎች ማለፋቸውን ያስታወሱት ሚኒስትሩ፤ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ20 ሺህ በላይ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

በዘንድሮው የፈተና ከ50 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎች ስብጥር በተፈጥሮ ሳይንስ 16 ነጥብ 58 በመቶ፣ በማኅበራዊ ሳይንስ 8 ነጥብ 33 በመቶ መሆኑንም ገልጸዋል።

ለፈተና ከተመዘገቡ 563 ሺህ 960 ተማሪዎች ውስጥ 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸው ተጠቅሷል።

በትምህርት ዘርፉ እየተተገበሩ ባሉ የሪፎርም እርምጃዎች የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱን የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ግልጽ ማሳያ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል ።

#ኢትዮጵያ

23/08/2026
23/08/2026

70 ሺህ 544 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል - ትምህርት ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 544 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል አለ የትምህርት ሚኒስቴር፡፡

የትምህረት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በዘንድሮ ዓመት የተሻሻለ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺህ 544 ተማሪዎች ብቻ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡

ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12 ነጥብ 8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን አብራርተዋል፡፡

በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺህ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺህ 210 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ ቀዳሚ ነው ብለዋል።

በዓመቱ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 62 በመቶ የሚሆኑት በኦንላይን መፈተናቸውን አስረድተዋል፡፡

በ2018 የትምህርት ዘመን አጠቃላይ 563 ሺህ 501 ተማሪዎች በ607 የፈተና ማዕከላት ውስጥ የተፈተኑ ሲሆን ፈተናው በ6 ዙሮች መሰጠቱን አስታውሰዋል።

88 ት/ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ያሳለፉ ሲሆን 565 ት/ቤቶች ደግሞ ምንም ተማሪ ማሳለፍ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡

ካለፉት ተማሪዎች መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16 ነጥብ 5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8 ነጥብ 33 በመቶ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡

በጀማል አህመድ

22/08/2026
CEOs of Assessment Bodies of Nigeria, Uganda, Ethiopia and Malawi- left to rightDealing with regional and continental ed...
17/08/2026

CEOs of Assessment Bodies of Nigeria, Uganda, Ethiopia and Malawi- left to right

Dealing with regional and continental educational Assessment issues in 42nd AEAA Annual conference, in Arusha, Tanzania.

Theme: Rethinking Educational Assessment in the age of AI

17/08/2026

Address

2QP7+M6F, King George VI Street
Addis Ababa
30747

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Educational Assessment and Examinations Service-EAES posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Educational Assessment and Examinations Service-EAES:

Shortcuts

Share