Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር /

Ministry of  Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር / The Ministry of Revenues is the body responsible for collecting revenue from domestic taxes.

ኢትዮጵያ በዓለም ፊት የመሪነት ሚናዋን ለማሳየት የምትችልበት እድል ላይ ትገኛለች ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚደርሱ ተፈጥሮአዊ ...
03/08/2026

ኢትዮጵያ በዓለም ፊት የመሪነት ሚናዋን ለማሳየት የምትችልበት እድል ላይ ትገኛለች

ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚደርሱ ተፈጥሮአዊ አደጋዎችን ለመከላከል፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት "የአረንጓዴ አሻራ" ኢኒሼቲቭን ይፋ ማድረጓ ይታወቃል። ላለፉት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ እና በአካባቢ ጥበቃ ላደረገችው ተከታታይ ጥረት ከዓለም መንግሥታት ትልቅ እውቅና በማግኘት፣ ታላቁን እና 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ የ"ኮፕ" (COP) 2027 ን ጉባዔ እንድታዘጋጅ ተመርጣለች።

ዘንድሮም "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር በሚካሄድበት ወቅት በልዩ ሁኔታ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማዘጋጀት መመረጧን ተከትሎ የአገሪቱን የአረንጓዴ ዐሻራ ተነሳሽነት፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ተግባራት ለዓለም ለማሳየት በሚያስችል መልኩ ከICT ፓርክ እስከ ቢሾፍቱ ደቡብ መውጫ ባለው 45 ኪሎ ሜትር የመንገድ ኮሪደር ውስጥ የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ እና ሚንስትር ዴኤታዎች፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ደ/ር)፣ የጉምሩክ ምክትል ኮሚሽነሮች እና ሌሎችም የተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ሁሉም የሚኒስቴር መስሪያቤቶች አሻራቸውን አሳርፈዋል።

በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ ገርጂ ማርያም በሚባል ቦታ የሁለቱም ተቋማት አመራሮች እና ሰራተኞች ችግኞችን ተክለዋል።

በየጊዜው ሁለቱ ተቋማት የሚተክሏቸውን ችግኞች የመንከባከብ ስራም ተንከባካቢ ሰራተኞችን ጭምር በመቅጠር እያከናወኑ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በአዳነ ውበት
ፎቶ:- የትናየት እንዳያፍሩ

"ተስፋን እንትከል"ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)"ተስፋን እንትከል" የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞች ይተከላሉ። የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉም...
03/08/2026

"ተስፋን እንትከል"

ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

"ተስፋን እንትከል" የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞች ይተከላሉ።

የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽንም የችግኝ ተከላ ፕሮግራም እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡

2️⃣ቀናት ቀሩት!የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል  #አረንጓዴዐሻር2️⃣ DAYS LEFT!One Day National Tree pl...
01/08/2026

2️⃣ቀናት ቀሩት!
የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር
📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም

#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር

2️⃣ DAYS LEFT!
One Day National Tree planting campaign program
📅 August 3, 2026

 ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
31/07/2026



ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ከ704 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉሐምሌ 24/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)የጉምሩክ ኮሚሽን ከሀምሌ 16 እስከ ሀምሌ 22 ቀን 201...
31/07/2026

ከ704 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የጉምሩክ ኮሚሽን ከሀምሌ 16 እስከ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው ክትትል 661.1 ሚሊዮን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች እና 43.3 ሚሊዮን ብር የወጭ፤ በድምሩ 704.4 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ተይዘዋል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አዳዲስ እና ልባሽ ጨርቆች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ የግንባታ እቃዎች፣ ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የቁም እንስሳት ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ መድኃኒት፣ ማዕድናት እና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡

በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የገቢ እና የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዋሽ፣ አዲስ አበባ ኤርፖርት እና ጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዙ በቅደም ተከተላቸውም 261 ሚሊዮን፣ 111 ሚሊዮን እና 90 ሚሊዮን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ችለዋል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በጥቆማ እና በበረራ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ 34 ተጠርጣሪዎች እና 14 ተሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች እና አመራሮች፣ የክልልና የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ህዝባችን ምስጋናውን ያደርሳል፡፡

የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን ያቀርባል፡፡

፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 በፋና ቴሌቪዥን ቻናል 2 ሰኞ ምሽት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

3 ቀናት ቀሩት ! በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪ...
31/07/2026

3 ቀናት ቀሩት !

በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካዊው ሀገራዊ ዘመቻ በጋራ በመሰብሰብ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን ይተክላሉ።

የገቢዎች ሚኒስቴርም በየዓመቱ በሚካሄደውና በዚሁ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከፍተኛ ለውጥ ላይ ደረሰው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ ሲሳተፍ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

አምና የተከልነው አድጎ ለምልሟል፤ ዘንድሮም ለአረንጓዴዋ ኢትዮጵያ አሻራችንን ማኖራችንን እንቀጥላለን።

ዘንድሮም በከተማችን አዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ 20,000 ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡

የተፈጥሮ አካባቢያችንን አረንጓዴ እንደምናለብሰው ሁሉ፣ የሀገራችንን ኢኮኖሚ እድገት በዘመነ እና ፍትሀዊ ታክስ አስተዳደር እውን እናደርጋለን!

#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻራ


፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 በፋና ቴሌቪዥን ቻናል 2 ሰኞ ምሽት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

3️⃣ቀናት ቀሩት!የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም #ተስፋንእንትከል  #አረንጓዴዐሻር3️⃣ DAYS LEFT!One Day National Tree pl...
31/07/2026

3️⃣ቀናት ቀሩት!
የአንድ ጀንበር ሀገራዊ ችግኝ ተከላ መርሃግብር
📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻር
3️⃣ DAYS LEFT!
One Day National Tree planting campaign program
📅 August 3, 2026


፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 በፋና ቴሌቪዥን ቻናል 2 ሰኞ ምሽት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

4 ቀናት ቀሩት ! በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪ...
30/07/2026

4 ቀናት ቀሩት !

በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካዊው ሀገራዊ ዘመቻ በጋራ በመሰብሰብ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን ይተክላሉ።

የገቢዎች ሚኒስቴርም በየዓመቱ በሚካሄደውና በዚሁ በህብረተሰብ ተሳትፎ ከፍተኛ ለውጥ ላይ ደረሰው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ ሲሳተፍ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

አምና የተከልነው አድጎ ለምልሟል፤ ዘንድሮም ለአረንጓዴዋ ኢትዮጵያ አሻራችንን ማኖራችንን እንቀጥላለን።

ዘንድሮም በከተማችን አዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ 20,000 ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡

የተፈጥሮ አካባቢያችንን አረንጓዴ እንደምናለብሰው ሁሉ፣ የሀገራችንን ኢኮኖሚ እድገት በዘመነ እና ፍትሀዊ ታክስ አስተዳደር እውን እናደርጋለን!

#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻራ


፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 በፋና ቴሌቪዥን ቻናል 2 ሰኞ ምሽት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

4️⃣ቀናት ቀሩት!በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካ...
30/07/2026

4️⃣ቀናት ቀሩት!

በሁሉም የሀገሪቱ ማዕዘናት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለጸናች ኢትዮጵያ ያላቸውን ጠንካራ አንድነት እና የጋራ ኃላፊነት በሚያንጸባርቀው፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ሥር ለታሪካዊው ሀገራዊ ዘመቻ በጋራ በመሰብሰብ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን ይተክላሉ።

📅 ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም
የዚህ ታሪካዊ ንቅናቄ አካል ይሁኑ!

#ተስፋንእንትከል #አረንጓዴዐሻራ



፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 በፋና ቴሌቪዥን ቻናል 2 ሰኞ ምሽት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

የትውልድ ግንባታና ገቢ  መሰብሰብ የማይነጣጠሉ ተልዕኮዎች መሆናቸው ተገለጸሐምሌ 22/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ገቢን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ...
29/07/2026

የትውልድ ግንባታና ገቢ መሰብሰብ የማይነጣጠሉ ተልዕኮዎች መሆናቸው ተገለጸ

ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ገቢን ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት የሚያከናውናቸውን ስራዎች አጠናክረው ቀጥለዋል።

በዛሬው እለትም የተቋማቱ የእቅድ አፈጻጸም እና እቅድ ግምገማ መድረክ መጠናቀቅን ተከትሎ በተከናወነው ፕሮግራም የኢትዮጽያ ጉምሩክ ኮሚሽን በቢሾፍቱ ከተማ ጨለለቅ ክ/ከተማ የሚገነባው የደምቢ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓት ተካሂዷል።

በዚሁ ፕሮግራም ላይ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ ባስተላለፉት መልእክት ተቋማቱ በየጊዜው የማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ እንደሚገኙ እና የህንኑ ተግባር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የትውልድ ግንባታና ገቢ መሰብሰብ የማይነጣጠሉ ተልዕኮዎች መሆናቸው የገለጹት ሚኒስትሯ ለህብረተሰብ ማህበራዊ ችግሮች ስንደርስ እንደተቋም ኃላፊነታችንን ከመወጣት ባለፈ ተቋሙ ገቢን በሚፈለገው ልክ ለመሰብሰብ የሚያደርገውን ጥረት በእኔነት መንፈስ እንዲያግዙ ያደርጋል ብለዋል።

አያይዘውም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በገቢው ዘርፍ ያሉ የታክስ ማጭበርበር እና ስወራ እንዲሁም ኮንትሮባንድን የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራን አጠናክረው መደገፍ እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የጉምሩክ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) በበኩላቸው ባለፋት 8 ዓመታት ከ8.5 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት መሰብሰቡን ገልጸው፣ ይህም በትምህርት ቤቶችና በአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤቶች ግንባታ፣ በጤና ተቋማት ድጋፍ፣ በንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች፣ የተፈጥሮ እድግ ለደረሰባቸው ዜጎች በተደረጉ የሰብአዊ ድጋፍ ፕሮግራሞች እንዲሁም በሌሎች ማህበራዊ ልማት ተግባራት ላይ መዋሉን ገልጸዋል።

የቢሾፍቱ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ገዛኸኝ ደጀኔ ሁለቱ ተቋማት በየጊዜው በከተማዋ እየተካሄዱ ያሉ የልማት ስራዎችን ስለሚደግፉ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበው ድጋፉ ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በእለቱ ከት/ት በቱ ግንባታ ማስጀመሪያ ጎን ለጎን የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ተከናውኗል።

በዝግጅቱ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሮች፣ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች፣ የቢሾፍቱ ከተማ አመራሮች፣ አባገዳዎችና ሀደሲንቄዎች እንዲሁም የጨለለቅ ክ/ከተማ የደንቢ አካባቢ ማህብረሰብ ተሳትፈዋል።

፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 በፋና ቴሌቪዥን ቻናል 2 ሰኞ ምሽት ከ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ፣
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

Address

Megenagna, 24 Area
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 18:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር / posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር /:

Shortcuts

Share