05/09/2026
የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ከተቋሙ ሰራተኞቸ ጋር ውይይት ተካሄደ
ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ሠራተኞች የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ውይይት አካሂደዋል።
በመድረኩ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ ኪኒሶ በሰጡት መልዕክት፣ ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አበረታች አፈጻጸም ማስመዝገቡን ጠቅሰው፣ የተመዘገበው ውጤት ለ2019 በጀት ዓመት ስኬታማ አፈጻጸም ጠንካራ መሠረት እንደሚሆን ገልጸዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ለተቋሙ ስኬታማ አፈጻጸም የሠራተኞች አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን በመጥቀስ፣ ሠራተኞችን አመስግነዋል።በውይይቱም የሰነድ ማረጋገጥና ምዝገባ፣ የሕግ ጉዳዮች፣ የሰነድ አስተዳደር እና የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የሥራ ክፍሎች በ2018 በጀት ዓመት ያከናወኗቸውን ተግባራትና ያስመዘገቧቸውን ውጤቶች አቅርበዋል።
በተጨማሪም፣ ሀሰተኛ ሰነዶችን በመከላከል ተአማኒነቱ የተጠበቀ ሰነድ ማረጋገጥና መመዝገብ፣ በተለያዩ ስልጠናዎች የሠራተኞችን አቅም ማጎልበት እንዲሁም በመሶብ የአንድ አገልግሎት ማዕከላት የሚሠሩ ሠራተኞች የተቋሙን መልካም ስምና ገጽታ በመጠበቅ የተቋሙ አምባሳደሮች ሆነው መስራት እንዳለባቸው ተገልጿል።
ተሳታፊዎችም በበኩላቸው በ2018 በጀት ዓመት የተመዘገበውን ስኬት በማስቀጠል፣ በ2019 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ደረጃን የበለጠ ለማሻሻል በተሰማሩበት የሥራ መስክ በትጋትና በኃላፊነት እንደሚያገለግሉ ገልጸዋል።
የአገልግሎቱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጆችና የማኔጅመንት አባላትም በድሬዳዋ ከተማ በ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትና በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል።