05/08/2026
አገልግሎቱ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አሻራና ለአቅመ ደካማ ወገኖች የበጎአድራጎት ስራዎች አከናወነ።
ሃምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም
የሰነዶችማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ካውንስል አባላት በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በመገኘት የችግኝ ተከላ እና የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ለተማሪዎች አድርገዋል።
የአረንጓዴ አሻራና ለሶስት መቶ አቅመደካማ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ በተደረገበት በዚህ መርሀግብር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ ኪኒሶ ባስተላለፋት መልእክት የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች ዜጋ ተኮር የሆነ የልማት ተግባራት ላይ ሲሳተፉ የቆዩ መሆኑን ገልጸው በተለይ በድሬዳዋ ከተማ የተቋሙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሚገኝበት እና በድሬ መሶብ የአንድ አገልግሎት ማእከል ውስጥ በተደራጀ ሁኔታ አገልግሎቱን ተደራሽ እያደረገ በመሆኑ የአረንጓዴ አሻራና በጎ አድራጎት ተግባራትን በማከናወን ትብብርና አብሮነትን እየገለጸ ይገኛል ብለዋል።
አቶ ሀሚድ አያይዘውም ለተተኪ ሀገር ተረካቢ ተማሪዎች የተደረገው ድጋፍም ትውልድን የሚያንጽ እና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባ ተግባር ነው ብለዋል።
የሠነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አመራር እና ሰራተኞች በአንድ ጀምበር አረንጓዴ አሻራ ተግባር ላይ ሰፊ ተሳተፎ ያደረጉ ሲሆን በጎንደር ከተማ በመገኘት የአምስት አረጋውያንን ቤት ግንባታ የሶስት መቶ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍና የአረንጓዴ አሻራ ተግባራትን ማከናወናቸው ይታወቃል።