Ethiopian Football Federation

Ethiopian Football Federation ይህ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ይፋዊ የፌስቡክ ገፅ ነው። ይህን ገፅ ላይክ በማድረግ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን መረጃዎችን ይከታተሉ። It organizes the national football leagues and the national team.

The Ethiopian Football Federation ( EFF ) is the governing body of football in Ethiopia. It was founded in 1943 and became affiliated with FIFA in 1952 and with CAF in 1957.

የ2026 የፊፋ የ"ያንግ ታለንት" የወጣት ዳኞች ስልጠና ተጠናቀቀየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፊፋ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፊፋ "ያንግ ታለንት" የወጣት የጨዋታ አመራሮች ስልጠና ላለፉ...
06/09/2026

የ2026 የፊፋ የ"ያንግ ታለንት" የወጣት ዳኞች ስልጠና ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፊፋ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፊፋ "ያንግ ታለንት" የወጣት የጨዋታ አመራሮች ስልጠና ላለፉት አምስት ተከታታይ ቀናት በተግባር እና ንድፈ ሐሳብ ሲሰጥ ቆይቶ ዛሬ በአዜማን ሆቴል በይፋ ተጠናቋል።

በፊፋ ቴክኒክ ኢንስትራክተር ሊ ቾንግ፣ በፊፋ የአካል ብቃት ኢንስትራክተር ማርክ ምዜንጎ እንዲሁም በሀገር ውስጥ ኢንስትራክተሮች አማካኝነት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ማጠናቀቂያ ላይ ኢንስትራክተር ጌራወርቅ ከተማ ባደረጉት ንግግር ስልጠናው ምንም እንኳን አጭር ቆይታ ቢሆንም ሰልጣኞች ከፍተኛ እውቀት ያገኙበት እንደነበር ገልጸዋል። አክለውም ሰልጣኞች ወደየመጡበት ሲመለሱ ያገኙትን እውቀት መተግበር እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የፊፋ ቴክኒክ ኢንስትራክተር ሚስተር ሊ ቾንግ በበኩላቸው ፌዴሬሽኑ ለወጣት ዳኞች ትኩረት ሰጥቶ ይህንን መርሐ ግብር በአንድ ሆቴል በማሰባሰብ ስላዘጋጀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በስልጠናው ወቅት በዘመናዊ የመግባቢያ ቴክኖሎጂዎች እና በቪዲዮ የተደገፉ አዳዲስ የዳኝነት ፅንሰ-ሀሳቦችን ማስተዋወቅ መቻሉን የገለጹት ሚስተር ሊ "ይህ አሰራር አርአያነት ያለው ሞዴል በመሆኑ ሌሎች ሀገራትም እንደሚተገብሩት አልጠራጠርም" ብለዋል። በተጨማሪም ቀደም ሲል ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማን በወጣትነቱ ተመልከተው አቅሙን እንደተረዱ በማስታወስ የወጣት ዳኞች አቅም በስልጠና እና በተግባር ማደግ እንደሚችልና በቀጣይም ከእነዚህ ሰልጣኞች መካከል በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራቸውን የሚያስጠሩ ዳኞች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

የፊፋ የአካል ብቃት ኢንስትራክተር ሚስተር ማርክ ምዜንጎ በስልጠናው የተሳተፉት ወጣት ዳኞች ከኤሊት ዳኞች ጋር ያላቸው የአቅም ልዩነት በጣም አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው "አካል ብቃት ለዳኝነት እንደ ቪዛ ነው፤ ያለ ቪዛ ትኬት ቢኖራችሁ እንኳ መጓዝ እንደማትችሉ ሁሉ ያለ አካል ብቃትም ወደ ላቀ ደረጃ መሸጋገር አይቻልም" በማለት ሰልጣኞች ጠንክረው እንዲሰሩ መክረዋል።

የኢ/እ/ፌ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባሕሩ ጥላሁን በበኩላቸው ፌዴሬሽኑ አዳዲስ አሰራሮችንና ስትራቴጂዎችን በመቅረፅ ወጣት ዳኞችን ለማፍራት እያደረገ ያለውን ጥረት አብራርተዋል። እንደ ባምላክ ተሰማ እና ሊድያ ታፈሰ ያሉ አንጋፋ ዳኞች ከዳኝነት መገለላቸውን ተከተሎ የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት የትውልድ ቅብብሎሹ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። አዳዲስ አሰራሮች ሲዘረጉ ከውስጥም ከውጭም ተቃውሞዎች ማጋጠማቸው አልቀሬ ቢሆንም ፌዴሬሽኑ ወጣት ዳኞች ላይ ኢንቨስት ማድረጉን እንደሚቀጥልና ለሰልጣኞች ማደሪያና ስልጠና ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።

አቶ ባሕሩ የኢትዮጵያ ዳኞች በታማኝነት እና በቅንነት ሥራቸውን በማከናወን በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ መልካም ስም ያላቸው መሆኑን ገልጸው አዲሶቹ ወጣት ዳኞችም ይህንን ታማኝነት እና ሙያዊ ብቃት አስጠብቀው እንዲቀጥሉ አደራ ብለዋል።

ለመገናኛ ብዙሃን !የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የህክምና አጋሩ ከሆነው ከውዳሴ ዳያግኖስቲክ ማዕከል ጋር በመተባበር የጳጉሜ የበጎ አድራጎት ወርን በማስመልከት ነገ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ...
06/09/2026

ለመገናኛ ብዙሃን !

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የህክምና አጋሩ ከሆነው ከውዳሴ ዳያግኖስቲክ ማዕከል ጋር በመተባበር የጳጉሜ የበጎ አድራጎት ወርን በማስመልከት ነገ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. በተስፋ አዲስ ፓረንትስ የህፃናት ካንሰር ማዕከል ጉብኝት ያደርጋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች እና የአሰልጣኝ ቡድን አባላት ተሳታፊ በሚሆኑበት በዚህ መርሐ ግብር ብሔራዊ ቡድናችን በተስፋ አዲስ ፓረንትስ የህፃናት ካንሰር ማዕከል በመገኘት ህሙማንን የሚጠይቅ እና ለተቋሙም ድጋፍ የሚያደርግ ይሆናል።

የመገናኛ ብዙሃን አካላት ነገ ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ አራት ኪሎ ከናዝሬት ስኩል ወረድ ብሎ የአርሜኒያ ትምህርት ቤት አጠገብ በሚገኘው የተስፋ አዲስ ፓረንትስ የህፃናት ካንሰር ህሙማን መኖሪያ ግቢ በመገኘት ለዚህ የበጎ አድራጎት ስራ ሽፋን መስጠት የምትችሉ መሆኑን በማክበር እንገልፃለን።

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የሴካፋ ውድድር ዝግጅቱን ቀጥሎ በዛሬው ዕለት ከሀዋሳ ከተማ ጋር የአቋም መፈተሻ አከናውኗል። ጨዋታውንም ያለ ግብ በአቻ ውጤት አጠናቋል።
05/09/2026

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የሴካፋ ውድድር ዝግጅቱን ቀጥሎ በዛሬው ዕለት ከሀዋሳ ከተማ ጋር የአቋም መፈተሻ አከናውኗል። ጨዋታውንም ያለ ግብ በአቻ ውጤት አጠናቋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፊፋ ጋር በመተባበር እየተካሄደ የሚገኘው የፊፋ ያንግ ታለንት የጨዋታ አመራሮች ስልጠና በንድፈ ሐሳብ እና በተግባር እየተሰጠ አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን በ...
05/09/2026

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከፊፋ ጋር በመተባበር እየተካሄደ የሚገኘው የፊፋ ያንግ ታለንት የጨዋታ አመራሮች ስልጠና በንድፈ ሐሳብ እና በተግባር እየተሰጠ አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን በነገው ዕለት ፍጻሜውን ያገኛል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ዝግጅቱን ቀጥሎ 21ኛ ቀኑን አስቆጥሯል። በዛሬው ዕለትም በቢሾፍቱ ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የአቋም...
05/09/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ዝግጅቱን ቀጥሎ 21ኛ ቀኑን አስቆጥሯል። በዛሬው ዕለትም በቢሾፍቱ ክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ አከናውኖ አንድ አቻ ተለያይቷል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከካፍ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የካፍ ሲ ላይሰንስ የመጨረሻ ሞጁል ስልጠና በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ከተማ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ፍጻሜውን ...
05/09/2026

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከካፍ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የካፍ ሲ ላይሰንስ የመጨረሻ ሞጁል ስልጠና በዛሬው ዕለት በባህር ዳር ከተማ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ፍጻሜውን አግኝቷል። ስልጠናው ላለፉት ሁለት ወራት ከአስራ አምስት ቀናት በተግባር እና በንድፈ ሃሳብ ሲሰጥ ቆይቷል።

በስልጠናው መዝጊያ ስነስርዓት ላይ የኢ/እ/ፌ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳኛቸው ንግሩ የመዝጊያ ንግግር እና የሥራ መመሪያ በመስጠት ተጠናቋል።

ለስልጠናው መሳካት የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትልቅ አስተዎፅኦ አበርክቷል።

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የሴካፋ ውድድር ዝግጅቱን በሀዋሳ ማከናወን ቀጥሎ የ6ኛ ቀን ልምምዱን በሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ አከናውኗል።
04/09/2026

የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የሴካፋ ውድድር ዝግጅቱን በሀዋሳ ማከናወን ቀጥሎ የ6ኛ ቀን ልምምዱን በሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ አከናውኗል።

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፀደቁ ውሎችየኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግዓርብ ነሐሴ 29/2018
04/09/2026

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፀደቁ ውሎች

የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ

ዓርብ ነሐሴ 29/2018

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፀደቁ ውሎችየኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪምየር ሊግዓርብ ነሐሴ 29/2018
04/09/2026

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የፀደቁ ውሎች

የኢትዮጵያ ወንዶች ፕሪምየር ሊግ

ዓርብ ነሐሴ 29/2018

Address

Https://maps. App. Goo. Gl/xEZrZeUbcRzWernFA
Addis Ababa
1080

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Football Federation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Football Federation:

Shortcuts

Share