Prosperity Party - ብልፅግና

Prosperity Party - ብልፅግና Prosperity Party is the ruling political party in Ethiopia established in December 2019

Prosperity Party is the ruling political party in Ethiopia established in December 2019 as a successor to EPRDF. Having an overall objective of making Ethiopia a prosperous country, its values are dignity of the people, justice, and multi-national unity.

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣...
02/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!

የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች ይከበራል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናትና በፈጠራ በመሻገር፣ በአሁን ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ዘይቤ ውስጥ ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ወረቶች የሚደመሩበት እንዲሁም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር በመሆሃ በሳቢ ኹነቶችና የንቅናቄ መንገዶች የሚመራ ይሆናል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ እንደሚሆንም የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አመላክቷል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት፤ ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል።

02/09/2026

ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲን የለውጥ ሥራ አደነቀ።በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ነብዩ ስሑል የተመራ...
01/09/2026

የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የብልፅግና ፓርቲን የለውጥ ሥራ አደነቀ።

በብልፅግና ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ የውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ነብዩ ስሑል የተመራ የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ልዑክ በቻይና ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።

ልዑኩ በቤጂንግ ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የአፍሪካ ጉዳዮች ኮሚቴ ጋር የፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነትን በተመለከተ ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ ላይ አቶ ነብዩ ስሑል፣ ብልፅግና ፓርቲ የሚመራበት የመደመር እሳቤና የፓርቲው ፕሮግራሞች በኢትዮጵያ ለሚታዩት ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ለውጦች ዋነኛ መሠረት መሆናቸውን ገልጸዋል።

የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤታማነት፣ የከተማና የገጠር ልማትን በተቀናጀ መልኩ ማከናወን፣ ሕዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚከናወኑ የልማት ሥራዎች እና የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የፓርቲውን የእሳቤ ጥራትና የማስፈጸም አቅም የሚያሳዩ ዋነኛ ተግባራት መሆናቸውንም አቶ ነብዩ ጠቁመዋል።

የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከሀገር ውስጥ የልማት ሥራ ባሻገር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ አቅም እያጠናከረ ያለ ተግባር መሆኑንም ገልጸዋል።

በፖለቲካው መስክ እየተመዘገቡ ያሉ አበረታች ለውጦችን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ በ2026 የአፍሪካ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጉባኤን በአዲስ አበባ ለማስተናገድ መመረጧንና ለጉባኤው ዝግጅት እያደረገች መሆኗን አስረድተዋል።

በሌላ በኩል፣ ልዑኩን የተቀበሉት የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል ወ/ሮ ሪኦ ዩሃ ብልፅግና ፓርቲ “ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግሥት፤ ጠንካራ መንግሥት ለጠንካራ ሀገር” በሚል እሳቤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እያስመዘገበ ያለውን ለውጥ ፓርቲያቸውና መንግሥታቸው በከፍተኛ አድናቆት እንደሚከታተሉ ገልጸዋል።

ወ/ሮ ሪኦ ዩሃ አክለውም፣ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲና ብልፅግና ፓርቲ በፓርቲ ለፓርቲ ግንኙነት የሚያደርጉትን ትብብር እና የጋራ ጥቅሞችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ቅንጅት በቀጣይ ለማጠናከር ፓርቲያቸው ጠንካራ አቋም እንዳለው አረጋግጠዋል።

የብልፅግና ፓርቲ ልዑክ በቤጂንግ በነበረው የመጀመሪያ ቀን ውሎ፣ ከሁለትዮሽ ውይይቱ በተጨማሪ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲን ታሪክ፣ ልምድ፣ ድሎችና ተግዳሮቶች የሚያሳየውን የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ሙዚየም ጎብኝቷል።

ጉብኝቱ የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ካለፈው ታሪኩ በመማር የአሁኑን ስኬቶች እንዴት እያጠናከረ እንደሚገኝና የወደፊት ራዕዩን ለማሳካት እያከናወነ የሚገኘውን እንቅስቃሴዎች ለመመልከት ጠቃሚ የመማማሪያ ልምድ ሆኗል።

በቀጣዮቹ ቀናት የሁለቱ ፓርቲዎች አመራሮች የጋራ ልምድ የሚጋሩበትና እርስ በእርስ የሚማማሩበት መርሃ ግብር ይከናወናል።

01/09/2026

እንደ ሀገር አበክረን ልንሰራበት የሚገባን ታዳጊ ህጻናት ትምህርት ቤት መሄድ ሲገባቸው በዳቦ ምክንያት ከትምህርት እንዳይሰተጓጎሉ ማድረግ ነው ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

"የአማራ ክልል ፈተና የማይበግረው እና ጽናት ያለው መሪ እየፈጠረ ነው" በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኀላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል...
01/09/2026

"የአማራ ክልል ፈተና የማይበግረው እና ጽናት ያለው መሪ እየፈጠረ ነው"

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኀላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ ላይ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ

01/09/2026
01/09/2026

የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎቻችን ብዙ ችግሮች የሚፈቱበት ነው ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

31/08/2026

የክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎቻችን ከበጀትና ፣ከልማት በላይ ናቸው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

31/08/2026

Weekly Message

The Renewed Public Mandate and Upcoming Key Priorities

The renewed democratic mandate conferred upon the Prosperity Party by the sovereign people of Ethiopia in the 7th General Election represents a historic vote of confidence. It is a solemn political trust that obligates us to advance our transformative national agenda. As a party, this multifaceted victory is not a reason for complacency, but a reminder of our responsibility to work diligently by prioritizing actions that tangibly transform our citizens' daily lives and fulfill their aspirations for development and better living conditions.

During the tenure of the new administration taking office this coming September, priority and concentrated effort will be given to major initiatives designed to improve livelihoods and accelerate national growth. Key focal areas center on ensuring food sovereignty and modernizing agriculture through cluster farming and technological inputs, alongside strengthening industrial foundations by enhancing renewable energy capacity, natural gas, and nuclear power projects. Furthermore, the party will focus on scaling the encouraging urban infrastructure and corridor development practices established in Addis Ababa to all regional cities, leveraging digital technologies broadly to curb corruption while delivering efficient public services, and establishing lasting political and social stability supported by the successful National Dialogue process.

These operational pillars constitute the foundational agenda for the incoming government administration. This strategic framework directly reflects the core resolutions codified in the official declaration of our Party's 2nd Regular Congress held January 31 – February 2, 2025: "Achieving our economic prosperity goals by enhancing national capacity, fostering new sectors, and building a creative economy." Through disciplined ex*****on, the decision to fortify national capacity will be translated into measurable, transformative outcomes for every citizen.

The guiding philosophy of this era remains Medemer; the ideological compass driving collective progress. Translating these strategic imperatives into reality demands active participation in national wealth creation, sustained political maturity, and unwavering civic dedication from all Ethiopians. On the international stage, regional bodies, strategic global partners, and international institutions increasingly recognize the institutional maturity, ideological clarity, and policy efficacy of the Prosperity Party. The success of our integrated developmental and diplomatic initiatives has positioned Ethiopia as an influential force in global governance.

Our destination remains resolute; establishing Ethiopia as an African Beacon of Prosperity by 2030. Grounded in popular sovereignty and guided by the principles of Medemer, the incoming administration will execute this vision with absolute fidelity. The Prosperity Party remains steadfast in heeding the public will, overcoming structural challenges, and delivering Ethiopia’s comprehensive resurgence.

Prosperity Party
August 31, 2026
Addis Ababa

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prosperity Party - ብልፅግና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Prosperity Party - ብልፅግና:

Shortcuts

Share