22/08/2026
🎭 ለበዓል ልዩ ድግስ፡ «ዝክረ አዲስ ዓመት» በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር እና በኤን.ቢ.ሲ (NBC) ኢትዮጵያ! 🌟
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ከኤን.ቢ.ሲ (NBC) ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጀው «ዝክረ አዲስ ዓመት» ልዩ የኪነ-ጥበብ ድግስ፣ የ2019 አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለሕዝብ ዕይታ ለመብቃት በከፍተኛ ጥበባዊና ቴክኒካዊ ዝግጅት ላይ ይገኛል።
የዝግጅቱን የልምምድ ሂደት ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከኤን.ቢ.ሲ (NBC) ኢትዮጵያ በመጡ ከፍተኛ አመራሮችና የቴክኒክ ባለሙያዎች ተገመግሟል።
በግምገማው ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ዋና ዳይሬክተር አቶ ባረክ ታደሰ ዝግጅቱ የቴአትር ቤቱን ታሪካዊና ባህላዊ ግርማ ሞገስ በሚመጥን ደረጃ እንዲቀርብ አቅጣጫ ያስቀመጡ ሲሆን፣ በባህላዊ ዜማዎችና ውዝዋዜዎች ጥራት፣ በመድረክ ምጥጥን (Stage Balance) እና በብርሃን አደረጃጀት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ይገኛል።
በተጨማሪም ከኤን.ቢ.ሲ (NBC) ኢትዮጵያ የመጡ የቴክኒክ ባለሙያዎች የአዘጋጆቹን የፈጠራ ክህሎት በመደነቅ፣ የማህበራዊ ሚዲያ የቅጅ መብት (Copyright) ህግጋትን እና የመልቲሚዲያ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን የተመለከቱ ጠቃሚ የሙያ አስተያየቶችን አቅርበዋል። በአሁኑ ወቅት ዝግጅቱ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ ተጠናቆ ለበዓል እንዲበቃ የቀሩት የልምምድ ጊዜያት በከፍተኛ ትጋት እየተከናወኑ ይገኛሉ።
📌 የጥበብ አፍቃሪያን እንዳያመልጥዎ! ይህን አስደሳችና ብሩህ የአዲስ ዓመት ስጦታ የመጀመሪያ ተከታታይ ለመሆን አሁኑኑ፡
• 🔔 የፌስቡክ ገጻችንን ማሳወቂያዎች (Notifications) «ON» ያድርጉ!
•
• ልዩ ዝግጅቱ እንዳያመልጥዎ ገጻችንን Like እና Follow በማድረግ የቤተሰባችን አባል ይሁኑ!
•
ስለዝግጅቱ የሚወጡ ተጨማሪ መረጃዎችን፣ ከቴሌቪዥን መስኮትና ከማህበራዊ ሚዲያ የቀጥታ ስርጭቶች ጋር ቀድመው ይከታተሉ።
#ኢትዮጵያብሔራዊቴአትር #ዝክረአዲስዓመት #ኪነጥበብ #አዲስዓመት2019