Gullele Sub City Small Tax Payers Branch Office

Gullele Sub City Small Tax Payers Branch Office Revenue Collection

06/06/2026

ይህ ቻናል በገቢዎች ሚኒስቴር የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁ.2 ቅ/ጽ/ቤት የከፈተው ኦፊሴላዊ የዩቲዩብ ቻናል...

03/06/2026

ኢ-ክሊራንስ በጉለሌ ገቢዎች የመረጃ ቴክኖሎጂ ባለሙያ የተዘጋጀ

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ገጽ ለገጽ ተሰጠ
03/06/2026

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ገጽ ለገጽ ተሰጠ

03/06/2026

የውጭ ሀገር ገንዘብ ምንዛሪ ጥቅም እና ኪሣራ
**********************

ማንኛውም ግብር ከፋይ በንግድ ሥራ ሂደት ውስጥ ከውጭ ሀገር ገንዘብ ምንዛሪ ተመን መዋዠቅ የሚያገኘው ጥቅም ወይም ትርፍ እንደ ማንኛውም መደበኛ የንግድ ሥራ ገቢ ተቆጥሮ በግብር ስሌቱ ውስጥ የሚካተት ይሆናል።
የምንዛሪ ኪሳራ ማካካሻ እና ማሸጋገርያ መንገዶች ግብር ከፋዩ በግብር ዓመቱ የወጪ ሀገር ገንዘብ ምንዛሪ ኪሳራ ካጋጠመው፣ ይህንን ኪሳራ በዚያው ዓመት ካገኘው የምንዛሪ ጥቅም ጋር ማካካስ ይችላል።

•በዓመቱ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ያልተካካሰ የኪሳራ መጠን ካለ፣ ግብር ከፋዩ ያንን ያልተካካሰ ኪሳራ ወደ ሚቀጥሉት ዓመታት በማሸጋገር ወደፊት ከሚያገኘው የምንዛሪ ጥቅም ጋር ሙሉ በሙሉ እስኪካካስ ድረስ ኪሳራውን ላልተወሰነ ጊዜ የማሸጋገር ይችላል፡፡

•ሆኖም ይህ መብት ተፈጻሚ የሚሆነው ግብር ከፋዩ የደረሰበትን የኪሳራ መጠን ለገቢዎች ባለሥልጣን በሚያሳምን አኳኋን ማረጋገጥ ሲችል ብቻ ነው።
በሌላ በኩል፣ የምንዛሪ ኪሳራ የገጠመው አካል የፋይናንስ ተቋም (እንደ ባንክ እና ኢንሹራንስ) ከሆነ፣ ከላይ የተጠቀሰው የኪሳራ ማሸጋገርያ ሥርዓት በእነሱ ላይ ተፈጻሚ የማይደረግ ሲሆን የፋይናንስ ተቋሙ የደረሰበትን ኪሳራ መጠን ለባለሥልጣኑን በሚያሳምን አኳኋን ማረጋገጥ ከቻለ የኪሳራው መጠን እንደተቀናሽ ወጪ ይያዝለታል፡፡
ጥቅምና ኪሳራው እውን የሚሆንበት ሁኔታ

•ግብር ከፋይ በውጭ ሀገር ገንዘብ ምንዛሬ ጥቅም አገኘ ወይም ኪሳራ ገጠመው የሚባለው ጥቅሙ ወይም ኪሳራው በተግባር እውን (Realized) ሲሆን ብቻ ነው።

•ግብር ከፋይ በውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይት የውጭ ሀገር ገንዘብ ምንዛሪ ጥቅም ማግኘቱ ወይም የውጭ ሀገር ገንዘብ ምንዛሪ ኪሳራ ያጋጠመው መሆኑን ለመወሰን ከግብይቱ ጋር በተያያዘ
ግብር ከፋዩ ራሱ ወይም ከእሱ ጋር ግንኙነት ያለው ሰው በገባው ከኪሳራ ሥጋት የመዳን ውል (Hedging) ላይ ያለው አቋም አብሮ ከግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል።

መሠረታዊ የቃላት ትርጓሜዎች

የሕጉን አፈጻጸም ግልጽ ለማድረግ የተወሰኑ ቃላት ፍቺ ተሰጥቷቸዋል። በዚህም መሠረት

የውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይት፡- ማለት የንግድ ሥራ ገቢ ለማግኘት ሲባል በውጭ ሀገር ገንዘብ የሚደረግ ግብይት፣ በውጭ ሀገር ገንዘብ የተገለጸን የዕዳ ግዴታ መስጠትን ወይም መቀበልን ወይም በውጭ ሀገር ገንዘብ የተገለፀ ሌላ ማንኛውም ግብይትን የሚያካትት ነው።

የዕዳ ግዴታ ፡- ማለት ገንዘብ ለሌላ ሰው ለመክፈል የተገባ ግዴታ ሆኖ፣ ተከፋይ ሂሳቦችን እንዲሁም ከቃልኪዳን ሰነዶች፣ ከሃዋላ ሰነዶች ወይም ከቦንዶች የሚመነጩ ግዴታዎችን ይጨምራል።

የውጭ ሀገር ገንዘብ ምንዛሪ ጥቅም እና ኪሳራ፡- የሚባሉት ከውጭ ሀገር ገንዘብ ግብይት ጋር በተገናኘ በምንዛሪ ተመን መዋዠቅ ምክንያት የሚገኙ ጥቅሞች ወይም የሚደርሱ ጉዳቶች ሲሆኑ፤

ከኪሳራ ሥጋት የመዳን ውል (Hedging Contract) የሚባለው ደግሞ አንድ ሰው በዚህ የምንዛሪ ተመን መዋዠቅ ምክንያት ሊደርስበት የሚችለውን የፋይናንስ ጉዳት ለማስቀረት ወይም ለመቀነስ ከሌላ ወገን ጋር የሚገባው ውል መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።

02/06/2026

ለተጫማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበ ሰው ግዴታዎች
*************************

1. ታክስ የሚከፈልበትን የስራ እንቅስቅሴ በማይንቀሳቀስ የሥራ ቦታ የሚያከናውን ማናቸውም የተመዘገበ ሰው፡-

•ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ በሚያካሂድበት ዋንኛ የስራ ቦታ በግልጽ በሚታይ ሥፍራ ዋናውን የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት የመለጠፍ፣

•የተሰጠውን የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ቅጂ ታክስ የሚከፈልበት እንቅስቃሴ በሚያካሂድባቸው ሌሎች የስራ ቦታዎች ሁሉ በግልጽ በሚታይ ሥፍራ የመለጠፍ፣ ግዴታ አለበት፡፡

2. የተመዘገበ ሰው ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበበትን ዝርዝር መረጃ ታክስ የሚከፈልበትን ስራ በሚያከናውንበት ዌብሳይት፤ የማህበራዊ ሚዲያ እና ሌላ የኤሌክትሮኒክ መድረክ ላይ ማስፈር አለበት፡፡

3. ከላይ ከተዘረዘሩት መረጃዎች በተጨማሪ በሚከተሉት መረጃዎች ላይ ለውጥ ሲያጋጥም የተመዘገበ ሰው ይህንኑ በ30 ቀን ጊዜ ውስጥ ለታክሱ ባለስልጣን ማስታወቅ አለበት፡፡

•የተመዘገበው ሰው የስልክ ቁጥር፣ የፋክስ ቁጥር፣ የኤሌክትሮኒክ እና ሌሎች የግንኙነት አድራሻዎች፡፡

•አዳዲስ ቅርንጫፎችን ወይም የሥራ ክፍሎችን መክፈትና መዝጋትን እንዲሁም የኢንተርኔት፤ የማህበራዊ ሚዲያ ወይም ለንግድ ስራ እንቅስቃሴ ጥቅም ላይ የሚውል ሌላ የኤሌክትሮኒክ መድረክ አድራሻ መለወጥን ጨምሮ የተመዘገበው ሰው ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ በሚያከናውንበት ቦታ ወይም በሚያከናውንባቸው ቦታዎች፡፡

•የተመዘገበው ሰው የንግድ ሥራ ባህሪ፣ እና ሌሎች የሚዘረዘሩ መረጃዎች፡፡

02/06/2026
02/06/2026

የክሬዲት እና የዴቢት ሰነዶች
**********************************

የተከፈለው የተጨማሪ እሴት ታክስ በመብዛቱ ወይም በማነሱ ምክንያት የሚደረግ ማስተካከያ ስለማድረግ የተመለከቱት ሁኔታዎች በሚሟሉበት ጊዜ የተመዘገበው ሰው ለሌላው የተመዘገበ ሰው እንደሁኔታው የክሬዲት ሰነድ ወይም የዴቢት ሰነድ መስጠት አለበት፡፡

የተመዘገበው ሰው ለአቅርቦቱ ገዢ የክሬዲት ወይም የዴቢት ሰነድ የሚሰጠው ሰነዱ እንዲሰጥ ምክንያት የሆነው የማስተካከያ ተግባር በተፈጸመበት የሒሣብ ጊዜ መጨረሻ ሊሆን ይገባል፡፡

የክሬዲት ሰነድ የሚከተሉትን መረጃዎች ሊይዝ ይገባል፦
ሀ) በሚታይ ቦታ ላይ “የክሬዲት ሰነድ” የሚል ጽሁፍ፤
ለ) የአቅራቢው ስም፤ አድራሻ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ቁጥር፤
ሐ) የአቅርቦቱ ተቀባይ ስም፤ አድራሻ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የተመዘገበ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ቁጥር፤
መ) የክሬዲት ሰነዱ መለያ ቁጥር እና የተሰጠበት ቀን፤
ሠ) ክሬዲት ሰነዱ የተሰጠበትን ታክስ የሚከፈልበት አቅርቦት ለይቶ ማወቅ የሚያስችል ግልጽ የሆነ መረጃን ጨምሮ፤ የክሬዲት ሰነድ ለመስጠት ምክንያት የሆነውን የሚያስረዳ አጭር መግለጫ፤ እና
ረ) በታክስ ደረሰኙ የተመለከተው የአቅርቦቱ ዋጋ፤ ትክክለኛው የአቅርቦቱ ዋጋ፤ በእነዚህ ሁለት ዋጋዎች መካከል ያለው ልዩነት፤ እና በልዩነቱ ላይ የሚታሰበው የተጨማሪ እሴት ታክስ መጠን::

የዴቢት ሰነድ የሚከተሉትን መረጃዎች ሊይዝ ይገባል፦
ሀ) በሚታይ ቦታ ላይ “የዴቢት ሰነድ” የሚል ጽሑፍ፤
ለ) የአቅራቢው ስም፤ አድራሻ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዘገባ ቁጥር፤
ሐ) የአቅርቦቱ ተቀባይ ስም፤ አድራሻ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የተመዘገበ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ቁጥር፤
መ) የዴቢት ሰነዱ መለያ ቁጥር እና የተሰጠበት ቀን፤
ሠ) ዴቢት ሰነዱ የተሰጠበትን ታክስ የሚከፈልበት አቅርቦት ለይቶ ማወቅ የሚያስችል ግልጽ የሆነ መረጃን ጨምሮ፤ የዴቢት ሰነድ ለመስጠት ምክንያት የሆነውን የሚያስረዳ አጭር መግለጫ፤ እና
ረ) በታክስ ደረሰኙ የተመለከተው የአቅርቦቱ ዋጋ፤ ትክክለኛው የአቅርቦቱ ዋጋ፤ በእነዚህ ሁለት ዋጋዎች መካከል ያለው ልዩነት፤ እና በልዩነቱ ላይ የሚታሰበው የተጨማሪ እሴት ታክስ መጠን::

02/06/2026

በግምት የተወሰነ የታክስ ስሌት ስህተት እንዴት ይታረማል?

*********************
ባለሥልጣኑ በታክስ ሕግ መሠረት የታክስ ከፋዩ የሰጠው የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ወይም ሌላ ሰነድ በታክስ ሕግ ወይም በጉዳዩ ኩነቶች ላይ ትርጉም ጥያቄ የማያስነሳ የጽሑፍ፣የሂሳብ ስሌት ወይም ሌላ ማንኛውንም ስህተት የያዘ በሚሆንበት ጊዜ ባለስልጣኑ ስህተቱን ለማረም ሲባል የታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ወይም ሌላውን ሰነድ የታክስ ስሌት ማስታወቂያው ወይም ሰነዱ ለታክስ ከፋዩ ከተሰጠበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ዓመታት ውስጥ ማሻሻል ይቻላል፡፡

በዚህ መሠረት የሚታረም የታክስ ስህተት የሚባለው፡-

•የመደመር፣የመቀነስ፣የማባዛትና የማካፈል ስህተት፤

•በስሌት ማጠቃለያ ላይ ከመንደርደሪያ ሀሳብ መለየት ወይም መቃረን፤

•ከአንድ የሂሳብ ቁጥር ከፊት ወይም ከኋላ የቁጥር መጨመር ወይም መቀነስ ወይም የሂሳብ ቁጥር ቦታ መቀያየር (transposition)፤

•የገቢ ወይም የወጪ ኮድ አመዘጋገብ ስህተት፤

•የቃል ወይም የሐረግ በአዎንታ ወይም አሉታ መቀያየር፤

•የሒሳብ ቁጥር ወይም ሀሳብ መተው ወይም መዘለል (omission)፤

•ከግብር ነጻ የሆነ ገቢን ግብር በሚከፈል ገቢ ውስጥ መጨመር፤

•በአንድ ታክስ ከፋይ ሒሳብ ውስጥ የሌላ ታክስ ከፋይ ሒሳብ መጨመር ወይም ማቀያየር፤

•የታክስ መጣኔን ወይም የትርፍ ህዳግን መሳሳት፤

•በታክስ ቅሬታ አጣሪ የሥራ ክፍል፣ በታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ወይም በመደበኛ ፍ/ቤት እንዲስተካከል የተወሰነን ጉዳይ አለማስተካከል፤

•በዚህ መሠረት ስህተት ሊታረም የሚችለው በታክስ ውሳኔ መጠን ላይ በመጨመር ወይም በመቀነስ ለውጥ የሚያመጣ ሲሆን ብቻ ሆኖ ለውጥ የማያመጣ በመሆኑ የማይታረም ስህተት ሲኖር ለታክስ ከፋዩ በጽሑፍ ይገለጻል፡፡

25/05/2026

ጥቅም ላይ የማይውል ደረሰኝ ስለመሰረዝ

▫️ ታክስ ከፋዩ የንግድ ሥራውን ሲያቋርጥ ወይም የዘርፍ፣ የአድራሻና የስም ለውጥ ሲያደርግ ታትመው ጥቅም ላይ የዋሉ ደረሰኞችን ታክስ ለሚከፈልበት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ይዞ በግንባር በመቅረብ እንዲሰረዝ ማድረግ አለበት፡፡
▫️ በተራ ቁጥር i የተገለፀው ቢኖርም ታክስ ከፋዩ ዘርፍ የቀነሰ እንደሆነ በእጁ ላይ ያለው ደረሰኝ ሳይሰረዝ የንግድ ሥራውን ለቀጠለበት ዘርፍ ጥቅም ላይ እንዲውል በታክስ ባለሥልጣኑ ሊፈቀድ ይችላል፡፡
▫️ የታክስ ባለሥልጣኑ እንዲሰረዝ በቀረበለት በእያንዳንዱ ደረሰኝ ቅጠል ላይ “ቮይድ” (VOID) የሚል ማህተም በማድረግ ለታክስ ከፋዩ መመለስ ያለበት ሲሆን ቮይድ (VOID) የተደረገውን ደረሰኝ ብዛት እና ሴሪያል ቁጥር የሚገልፅ ማረጋገጫም ለታክስ ከፋዩ ይሰጣል፡፡
▫️ የንግድ ሥራውን ያቋረጠ ታክስ ከፋይ የንግድ ሥራው ከተቋረጠ እና ደረሰኙን ከመለሰ በኃላ ለሚቀበላቸው ተሰብሳቢ (Receivable) ሂሳቦች አስቀድሞ ታክስ ይከፈልበት ለነበረው ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት (ቅ/ፅ/ቤት) ለግብይቱ መረጋገጫ የሚሆን ደብዳቤ እንዲፃፍለት ሊጠይቅ የሚችል ሲሆን ቅ/ፅ/ቤቱም የግብይቱን ዋጋ እና ቀን የሚያሳይ ደብዳቤ ለከፋዩ በአድራሻ መፃፍ አለበት፡፡

25/05/2026

የቴምብር ቀረጥ የክፍያ ግዴታ እነማን ላይ ይወድቃል?
**************************
1 በአንድ ሰነድ ተጠቃሚ የሆነ ሰዉ ሰነዱ ላይ የሚተመነዉን የቴምብር ቀረጥ የመክፈል ግዴታ አለበት፤

2 በኢትዮጵያ ዉስጥ ሰነዱን የሚሰራዉ ወይም የሚሰጠዉ ሰዉ ሰነዱ እንደተፈጸመ ቀረጡን የመክፈል ግዴታ ሲኖርበት ከኢትዮጵያ ዉጭ ከሆነ በኢትዮጵያ ዉስጥ መጀመሪያ ያስፈጸመዉ ሰዉ ቀረጡን የመክፈል ግዴታ አለበት፤

3 በኪራይ ዉል ዉስጥ የተለየ ስምምነት ከሌለ በስቀር ተከራይ ቀረጡን ይከፍላል፤

4 በንብረት ባለቤትነት ስም ማስመዝገቢያ ሰነድ ላይ ሊከፈል የሚገባዉን የቴምብር ቀረጥ ሌላ ስምምነት ከሌለ በስተቀር የመክፈል ግዴታ ያለበት የንብረት ባለቤትነት የሚመዘገብለት ሰዉ ያሆናል፤

5 ዉል ወይም ስምምነት የሚመሰርቱ ወገኖች ለቴምብሩ ቀረጥ በጋራና በተናጥል ተጠያቂ ይሆናል፤

6 በስራ/ቅጥር ዉል ላይ የሚከፈለዉን ቀረጥ የመክፈል ግዴታ የአሰሪዉ ይሆናል፤

7 ጉዳያቸዉን በግልግል የሚያስወስኑ ወገኖች እና በሕብረት ስምምነት ላይ ለሚከፈለዉ የቴምብር ቀረጥ አከፋፈል በጋራና በተናጥል ተጠያቂ ይሆናሉ፤

8 በሕብረት ስምምነት ላይ ለሚከፈለዉ የቴምብር ቀረጥ አሰሪዉና ሰራተኞቹ በጋራና በተናጥል ተጠያቂ ይሆናል፡፡

Address

እንቁላል ፋብሪካ አካባቢ ቃሲም ሕንፃ ላይ
Addis Abeba
-

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gullele Sub City Small Tax Payers Branch Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share