Lideta woreda 7 Communication Office

Lideta woreda 7 Communication Office ይህ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ኮሙኒኬሽን ፔጅ ነው!!!
ፈጣን መረጃ እንዲደርስዎ ላይክ, ሼር ያድርጉ ለሌሎች ያጋሩ

ኢትዮጵያ መርጣለች ፤ አሸንፋለች!ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የተደመረ  የመራጮች ድምፅ በየምርጫ ጣቢያዎች መለጠፍ መጀመሩን ተከትሎ የልደታ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ውጤቱን እየተመለከቱ ይገኛሉ።7ኛው ሀገ...
02/06/2026

ኢትዮጵያ መርጣለች ፤ አሸንፋለች!

ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የተደመረ የመራጮች ድምፅ በየምርጫ ጣቢያዎች መለጠፍ መጀመሩን ተከትሎ የልደታ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ውጤቱን እየተመለከቱ ይገኛሉ።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሕዝብ በድምጹ የሚመራውን ሕጋዊ መንግሥት ለማቋቋም ያለው ጉጉት እጅግ በጣም የላቀ መሆኑን ትልቅ አስረጅ ሆኖ በፖለቲካ ታሪካችን ውስጥ ተመዝግቧል።

የፖለቲካ ሀሳብን በሰላማዊ መንገድና በሕዝበ ውሳኔ መዳኘት የሰለጠነ ፖለቲካ ነው።

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስ...
01/06/2026

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።

የኢፌዴሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች  ሚኒስትር ዶ/ር አብረሃም በላይ  በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ምርጫ መሐንዲስ ኮንዶሚንዬም ...
01/06/2026

የኢፌዴሪ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር ዶ/ር አብረሃም በላይ በ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ምርጫ መሐንዲስ ኮንዶሚንዬም ድምፃቸውን ሰተዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።
01/06/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በበሻሻ ድምፅ ሰጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በትውልድ ቀያቸው በሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!የክ/ከተማችን ነዋሪዎች በሌሊት በመውጣት የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብቱን በተግባር እያረጋገጠ ነው።የሕዝብን ነፃ ምርጫ ማክበር የዲሞክራሲያዊነታችን መለኪ...
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

የክ/ከተማችን ነዋሪዎች በሌሊት በመውጣት የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብቱን በተግባር እያረጋገጠ ነው።

የሕዝብን ነፃ ምርጫ ማክበር የዲሞክራሲያዊነታችን መለኪያ ብቻ ሳይሆን የሀገራዊ ሕልውናችን እና የአንድነታችን ፅኑ መሠረት ነው።

በምርጫ ብቻ!

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!የከተማችን ነዋሪዎች በሌሊት በመውጣት የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብቱን በተግባር እያረጋገጠ ነው።የሕዝብን ነፃ ምርጫ ማክበር የዲሞክራሲያዊነታችን መለኪያ ...
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

የከተማችን ነዋሪዎች በሌሊት በመውጣት የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብቱን በተግባር እያረጋገጠ ነው።

የሕዝብን ነፃ ምርጫ ማክበር የዲሞክራሲያዊነታችን መለኪያ ብቻ ሳይሆን የሀገራዊ ሕልውናችን እና የአንድነታችን ፅኑ መሠረት ነው።

በምርጫ ብቻ!

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

በልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ከሌሊቱ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያው በመገኘት ድምፃቸውን ለመስጠት እየተጠባበቁ ነው።​በልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኙ መራጮች በዛሬው ዕለት ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምር...
01/06/2026

በልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ከሌሊቱ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያው በመገኘት ድምፃቸውን ለመስጠት እየተጠባበቁ ነው።

​በልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኙ መራጮች በዛሬው ዕለት ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ከመጀመሩ አስቀድሞ ከሌሊቱ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎቹ በመገኘት ድምፃቸውን ለመስጠት በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

ይህ ምርጫ የሀገሪቱን ቀጣይ አቅጣጫ የሚወሰን በመሆኑ ለቀጣይ አምስት ዓመታት ይመራናል፣ ሀገርንና ህዝብን ይበጃል የሚሉትን የፖለቲካ ፓርቲ በነጻነት ለመምረጥ በጠዋት ተገኝተዋል።

​በምርጫ ጣቢያዎቹ አካባቢ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እንዲኖር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን መራጮችም የድምፅ አሰጣጥ የሂደቱን መጀመር በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

​ምርጫ ዜጎች በሉዓላዊ የስልጣን ባለቤትነታቸው የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር የሚጠቀሙበት ሁነኛ መሳሪያ ነው።

በልደታ ክ/ከተማ ለ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን ተዘዋውረን ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገለጹ።የልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት ዝግጅት...
31/05/2026

በልደታ ክ/ከተማ ለ7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን ተዘዋውረን ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገለጹ።

የልደታ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

​ይህንኑ የምርጫ ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት የተለያዩ ነዋሪዎችን አነጋግሯል።

ያነጋገራቸው ነዋሪዎችም እንደገለፁት በመምረጥ የዜግነት ግዴታቸውን ለመወጣትና ድምፃቸውን ለመስጠት በከፍተኛ ዝግጅት እለተ ሰኞን እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ አክለውም የምርጫ ካርድ ለማውጣት የነበረውን ጉጉት አስታውሰው ካርድ ያወጣነው ድምፃችን ዋጋ ያለው በመሆኑና እሱንም የምናረጋግጠው በእለተ ሰኞ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተን በመምረጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሀገራዊ ምርጫው ሰላማዊና ፍትሀዊ እንዲሆንም እንደ ማህበረሰብ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱም አረጋግጠዋል።

ኢትዮጵያ ትመርጣለች !የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር ይረጋገጣል!!ምርጫ የሕዝብ ሉዓላዊነት እውነተኛ መገለጫ፣ የዜጎች የባለቤትነት እና የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር የ...
30/05/2026

ኢትዮጵያ ትመርጣለች !
የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር ይረጋገጣል!!

ምርጫ የሕዝብ ሉዓላዊነት እውነተኛ መገለጫ፣ የዜጎች የባለቤትነት እና የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር የሚረጋገጥበት ወሳኝ መድረክ ነው።

እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚገነባውም፣ የሕዝብን ፍጹም ውሳኔ ሰጪነት በመቀበልና በማክበር ላይ ብቻ ነው። ሕዝብን "በምርጫ አትሳተፉ፣ አትምረጡ" በማለት ለማስፈራራት መሞከር፣ እንዲሁም “እኔ አውቅልሃለሁ" በሚል የተሳሳተ የሞግዚትነት መንፈስ የዜጎችን ነፃ ፈቃድ ለመቀማት መሻት ለሕዝብ ያለን ንቀት የሚያሳይ፣ ከዘመኑ የሕዝብ የፖለቲካ ንቃተ ሕሊና ጋር የማይሄድ ኋላ ቀር አካሄድ ነው።

ሕዝባችን ግን ከእነዚህ ሁሉ የተዛቡ የፖለቲካ አመለካከቶች እጅግ ልቆ የሄደ፣ የሚበጀውንና የማይበጀውን ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ እንዲሁም የሀገሩን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በራሱ ሚዛናዊነት መወሰን የሚችል እጅግ አስተዋይና እውነተኛ ዳኛ ነው። ለዚህም አንዱና ዋነኛው ማረጋገጫ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች ከወዲሁ በንቃት በመመዝገብ የሀገራቸውን ብሩህ መጻኢ ዕድል ለመወሰንና የሚበጀውን ለመምረጥ ያሳዩት ከፍተኛ ዝግጁነትና ታሪካዊ ቁርጠኝነት ነው።

ስለሆነም፣ የሕዝብን ነፃ ምርጫ ማክበር የዲሞክራሲያዊነታችን መለኪያ ብቻ ሳይሆን የሀገራዊ ሕልውናችን እና የአንድነታችን ፅኑ መሠረት ነው። ይህ 7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን፣ በመላው የአፍሪካ አህጉር የእውነተኛ ዲሞክራሲንና የሕዝብን የውስጥ አቅም በተግባር ለማሳየት የሚኖረው አዎንታዊ አንድምታ እና ምሳሌነት እጅግ የላቀ ነው።

#ዲሞክራሲ
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Address

Addis Abeba

Telephone

+251973027010

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lideta woreda 7 Communication Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Lideta woreda 7 Communication Office:

Share