Asrat Ajawo /አስራት አጃዎ አላቲ

Asrat Ajawo /አስራት አጃዎ አላቲ የነገርክልኝን እረሳለሁ ግን እንድሰማኝ
ያደረከውን አልረሳውም!!!

 ። በሳውዲ አረቢያ ለ13 ረጅም ዓመታት በጽኑ እስር ላይ ቆይታ የሞት ፍርድ ተበይኖባት የነበረችው እህታችን ለይላ ኑርሰቦ ረዲ ከእስር ተፈትታ ዛሬ በትውልድ ሀገሯ ምድር አዲስ አበባ ስትገባ...
29/06/2026



በሳውዲ አረቢያ ለ13 ረጅም ዓመታት በጽኑ እስር ላይ ቆይታ የሞት ፍርድ ተበይኖባት የነበረችው እህታችን ለይላ ኑርሰቦ ረዲ ከእስር ተፈትታ ዛሬ በትውልድ ሀገሯ ምድር አዲስ አበባ ስትገባ የታየው እጅግ ልብ የሚነካና በከፍተኛ ስሜት የተሞላው የቤተሰብ መገናኘት ትዕይንት መላውን ህዝብ በአንድነት ያስለቀሰና ያስደሰተ ታላቅ ተአምር ሆኗል።

ከአስራ ሶስት ዓመታት ረጅም ስቃይ ስጋትና መከራ በኋላ በአካል ተገናኝተው እናትና ልጅ እርስ በእርሳቸው ተቃቅፈው ያነቡት የእንባ ጎርፍ፣ "አትሙቺ ያላት ነፍስ አትሞትም" የሚያሰኝና የፈጣሪን ታላቅነት በግልጽ ያሳየ እውነተኛ አስገራሚ አጋጣሚ ነው።

ይህ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው እና በአሁኑ ወቅት እውን የሆነው እጅግ ስሜት ቀስቃሽ የምስራች በሰላም ወደ እናቷ ሙቅ ጉያ በመመለሷ ሁላችንም በታላቅ እፎይታና ደስታ “እግዚአብሔር ይመስገን” ብለን የተቀበልነው ታላቅ ክስተት ነው።

ይህንን የመሰለ ታላቅ ሰብአዊና ብሔራዊ ስኬት በድል ለማጠናቀቅ የተቻለው በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባደረገው ተከታታይነት ያለው ሰፊ የዲፕሎማሲ ጥረት ብቻ ሳይሆን፣ ከተጎጂው ወገን ቤተሰቦች ጋር በተደረገው ሰፊ የእርቅ ሂደትና መከፈል የነበረበት የካሳ ክፍያ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በመፈጸሙ ነው።

በዚህ እጅግ አስቸጋሪና ሌሊትና ቀን በተሰራበት አገራዊ የልፋት ውጤት ላይ የበኩላቸውን ታላቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የኮሚቴ አባላት፣ ለሀገር ሽማግሌዎች፣ ለሃይማኖት መሪዎች፣ ለሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም በአንድነት ለቆሙት መላው ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ኤምባሲው የላቀ ምስጋናውንና አክብሮቱን አቅርቧል።

እኛም ለዚህ ሰብአዊ ትብብር ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ አብረው ለቆሙት ወገኖቻችን ሁሉ ያለንን ታላቅ አክብሮት እየገለጽን፣ የእህታችን የለይላ ኑርሰቦ በሰላም አገር ቤት መግባት የተባበረ ክንዳችን ውጤት በመሆኑ ለሁላችንም እንኳን ደስ አለን እንላለን።

ዶ/ር ተክለአብ ቡሎ የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾሙ
25/10/2025

ዶ/ር ተክለአብ ቡሎ የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሆነው ተሾሙ

22/10/2025

Address

Adiya

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asrat Ajawo /አስራት አጃዎ አላቲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share