20/08/2026
ለግንባር ቀደም ባለሀብቶች የእውቅናና የሽልማት መርሃ-ግብር ተካሄደ!!!
“ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ”
በሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የባለሀብቶች ግንባር በፓርቲው የሥራ እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ በሀብት በእውቀት በሙያና በሌሎች የድጋፍ መንገዶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግንባር ቀደም ባለሀብቶች ልዩ የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ተካሂዷል።
በመርሃ ግብሩም ለከተማው የልማት እንቅስቃሴና ለፓርቲው የሥራ አፈጻጸም አንጸባራቂ ውጤት የራሳቸውን የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለሀብቶች የዋንጫ የሜዳሊያና የምስክር ወረቀት ና የእዉቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የእውቅናና የሽልማት መርሃ ግብሩ ባለሀብቶች በከተማው የልማት ጉዞ ውስጥ ያላቸውን ሚና የበለጠ ለማጠናከር በቀጣይም በልማትና በፓርቲ ሥራዎች ላይ በተሻለ መንፈስ እንዲሳተፉ ለማበረታታት ያለመ ነው።
ባለሀብቶች የከተማውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በማፋጠን የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ሀብትን በማስፋፋትና ለልማት የሚያበረክቱትን ድርሻ በማጠናከር የከተማዋን የብልጽግና ጉዞ ለማስቀጠል ወሳኝ አጋሮች መሆናቸው በመድረኩ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አ/መጅድ ፊጣሞ ገልጿል።
በ2018 ዓ.ም የተመዘገቡ ውጤቶችን በመጥቀስ በ2019 በጀት ዓመት የበለጠ ውጤታማ ተሳትፎአዊና ተጨባጭ የሆነ የሥራ አፈጻጸም ለማስመዝገብ የባለሀብቶች የፓርቲ አመራሩና የከተማው ማህበረሰብ ትብብር እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።