የሀላባ ዞን ግብርና መምሪያ

የሀላባ ዞን ግብርና መምሪያ This is the official page.

የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ጉብኝት በማድረግ እየተከበረ ነው=====ጳጉሜ 2/2018 በሀላባ ዞን ጳጉሜ 2 "ዘላቂ ልማት ...
07/09/2026

የማንሰራራት ቀንን ምክንያት በማድረግ በሀላባ ዞን በቁሊቶ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ጉብኝት በማድረግ እየተከበረ ነው
=====

ጳጉሜ 2/2018 በሀላባ ዞን ጳጉሜ 2 "ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የማንሰራራት ቀን ምክንያት በማድረግ የተሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ጉብኝት በማድረግ እየተከበረ ይገኛል።

ከተጎበኙት መሰረተ ልማቶችን መካከል የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ግንባታ፣ የሀላባ ዞን አስተዳደር ህጻን፣ በኢንዱስትሪ እና በጥቅል የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች የታዩትን ማንሰራራት ተመልክቷል።

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ መሶብ አንድ አገልግሎት፣ ከሰንበት እስከ ሰንበት ገበያ ማዕከል ግንባታ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ግርን ኤርያ፣ ጎበኝተዋል።

"የማንሰራራት ቀን" ሲከበር ሀገራችን ኢትዮጵያ ብሎም ክልላችን እና ዞናችን ከጎታች የእድገት ማነቆዎች ተላቅቃ ወደ ማንሠራራት ጉዞዋን ያፋጠነችበት ዓመት ለመሆኑ ማሳያ መሆኑን በጉብኝቱ ተመላክቷል።

በከተማ ስለተከናወኑ የልማት ስራዎች ስለተገኙ ውጤቶች ገለጻ ሰጥተዋል።

በከተማ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች የስራ እድል በመፍጠር እና የወረዳውን ኢኮኖሚ በማጠናከር የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል ያላቸው አስተዋጽኦ ተገልጿል።

ከተማ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በማንሰራራት ጉዞዋ በርካታ ፕሮጀክቶችን ፈጽማለች፣ እያከናወነችም ትገኛለች ተብለዋል።

ከተማዋ በልማት የማንሰራራት ጉዞዋና በልማት ጉዞዋና በለውጥ አብሳሪ የቁርጥ ቀን ልጆቿ ጥረት ተደርገዋል ተብለዋል።

የተጀመሩ የልማት ሥራዎች በተጀመሩበት ፍጥነትና ጥራት እንዲጠናቀቁ እና ህዝብን በሰፊው ተሳትፎ የሀገር መንሰራራት ጉዞ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የመንሰራራት ቀን የተሰሩ ልማቶችን የምንገመግምበት፣ የተገኙ ስኬቶችን የምናጎለብትበት እና ለቀጣይ እድገት በጋራ ቁርጠኝነታችንን የምናረጋግጥበት ዕለት መሆኑም ተመልክቷል።

በዞኑ "የማንሰራራት ቀንን" ምክንያት በማድረግ የሀላባ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ መሀመድአሚን መሀዲ፣ የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ገመዳ መሀመድ፣ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ምክትል የመንግስት ተጠሪዎች አቶ ራመቶ መሀመድ እና አቶ አደም ጀማል፣ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
ሲል የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ዘግቧል።

‎የኢትዮጵያ ግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መርህ ቃል በአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጰጉሜ  የተለያዩ የግብርና ሥራዎች ጉብኝት በመደረግ ተጠናቋል።**************(ጳጉሜ፣01/2018 ዓ.ም)...
06/09/2026

‎የኢትዮጵያ ግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መርህ ቃል በአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጰጉሜ የተለያዩ የግብርና ሥራዎች ጉብኝት በመደረግ ተጠናቋል።
**************
(ጳጉሜ፣01/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ‎በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ የጰጉሜ 1 የኢትዮጵያ የግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መርህ ቃል መከበር የተጀመረ ስሆን በዚህ ፕሮግራም በወረዳው የተሰሩ አመርቂ የግብርና ስራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።

‎በእዚህ ጉብኝት በወረዳው በተለየዩ ቀበሌዎች የተሰሩ የቦቆሎ ሜጋ ክላስተር እርሻዎች ፤የድንች ክላስተር ፣የማር መንደሮች የዝሪያ ማሻሸያ ፣ የዶሮ መንደር እና የበርበሬ ክላስተር እና ሌሎች በግብርናው ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች ጉብኝት ተደርገዋል።

‎የኢትዮጵያ የግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ ጰጉሜ 1 አቶቲ ኡሎ ወረዳ!!

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

‎የኢትዮጵያ ግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መርህ ቃል በአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጰጉሜ 1 በይፋ መከበር ተጀመረ**************(ጳጉሜ፣01/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒ...
06/09/2026

‎የኢትዮጵያ ግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መርህ ቃል በአቶቲ ኡሎ ወረዳ ጰጉሜ 1 በይፋ መከበር ተጀመረ
**************
(ጳጉሜ፣01/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ‎በሀላባ ዞን አቶቲ ኡሎ ወረዳ የጰጉሜ 1 የኢትዮጵያ የግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ በሚል መርህ ቃል መከበር የተጀመረ ስሆን በዚህ ፕሮግራም በወረዳው የተሰሩ አመርቂ የግብርና ስራዎች ጉብኝት እየተደረገ ይገኛል።

‎በእዚህ ጉብኝት በወረዳው በተለየዩ ቀበሌዎች የተሰሩ የቦቆሎ ሜጋ ክላስተር እርሻዎች ፤የድንች ክላስተር ፣የማር መንደሮች የዝሪያ ማሻሸያ ፣ የዶሮ መንደር እና የበርበሬ ክላስተር እና ሌሎች በግብርናው ዘርፍ የተሰሩ ስራዎች እየተጎበኛ ስሆን ይህ በሴንቄሌ ቢጣና ቀበሌ የተዘራ የድንች ክላስተርን እየጎበኙ ነው

‎የኢትዮጵያ የግብርና እመርታ ለዘላቂ ከፍታ ጰጉሜ 1 አቶቲ ኡሎ ወረዳ!!

የአቶቲ ኡሎ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል !!

በሀላባ ዞን የጳጉሜ 1 እምርታ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች መከበር ጀመረ=====ጳጉሜ 1/2018 በሀላባ ዞን የጳጉሜ 1 እምርታ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች መከበር ጀምረዋል።በዞኑ "የማንሰራራት "በ...
06/09/2026

በሀላባ ዞን የጳጉሜ 1 እምርታ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች መከበር ጀመረ
=====

ጳጉሜ 1/2018 በሀላባ ዞን የጳጉሜ 1 እምርታ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች መከበር ጀምረዋል።

በዞኑ "የማንሰራራት "በሚል መሪ ቃል ዛሬ ጳጉሜ 1 እምርታ ቀን በተለያዩ ደማቅ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል።

በዚህም የሀላባ ቁሊቶ አጠቃላይ ሆስፒታል ጥምር ግብርና ስራዎች የመስክ ምልከታ በመካሄድ የጳጉሜ 1 እምርታ ቀን መከበር የተጀመረው።

በአከባበሩ ላይ የሀላባ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ ሀጂ ኑሪዬ፣ የሀላባ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ መሀመድአሚን መሀዲ፣ የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ምክትልና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ አቶ ራመቶ መሀመድ እና ሌሎች የዞኑ አጠቃላይ አመራሮች ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የዞኑ መንግስት ኮሚዪኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በኡዳና ጮሎቅሳ ቀበሌ በአርሶአደሩ ማሳ በቅድመ በልግ አዝመራ የለማው በቆሎ ምርት አሰባሰብ እየተደረገ ነው።
05/09/2026

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በኡዳና ጮሎቅሳ ቀበሌ በአርሶአደሩ ማሳ በቅድመ በልግ አዝመራ የለማው በቆሎ ምርት አሰባሰብ እየተደረገ ነው።

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በላይኛው አርሾ ቀበሌ በአርሶ አደር መሀመድ ከበቶ ጓሮ እየለማ የለው ቡና፣እንሰት እን የተለየዩ የፍራፍሬ ልማት አሁናዊ ገጽታ በከፊል።
05/09/2026

በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በላይኛው አርሾ ቀበሌ በአርሶ አደር መሀመድ ከበቶ ጓሮ እየለማ የለው ቡና፣እንሰት እን የተለየዩ የፍራፍሬ ልማት አሁናዊ ገጽታ በከፊል።

በዘንድሮው መኸር እርሻ 10ሺህ 751 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን በሀለባ ዞን የዌራዲጆ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀየሰብል ጥበቃና የአረም ቁጥጥር ሥራ በትኩረት እያከናወ...
04/09/2026

በዘንድሮው መኸር እርሻ 10ሺህ 751 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን በሀለባ ዞን የዌራዲጆ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታወቀ

የሰብል ጥበቃና የአረም ቁጥጥር ሥራ በትኩረት እያከናወኑ እንደሚገኙ የወረዳው አርሶ አደሮች ገልፀዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጎበና ሰማን እንደገለጹት በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወቅት የታቀደውን ያህል መሬት በዘር ለመሸፈንና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ የተቀናጁ የግብርና ሥራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።

በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወቅት 10ሺህ 751 ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለማልማት ታቅዶ ሙሉ በሙሉ በዘር መሸፈኑን ገልጸዋል።

በወረዳው በመኸር እርሻ በክላስተር የተዘሩ ሰብሎች በአሁኑ ወቅት በጥሩ የእድገት ደረጃ ላይ እንደሚገኙም አቶ ጎበና ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ሊከሰቱ የሚችሉ የሰብል ተባዮችንና የስንዴው ዋግ በሽታዎችን ለመከላከል የቅድመ ማስጠንቀቂያና የቁጥጥር ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በወረዳው ከመኸር እርሻ 381 ሺህ 600 ኩንታል ምርት ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመላክተዋል።

አርሶ አደሩ በመስመር መዝራት፣ የተመጠነ ማዳበሪያ መጠቀም እንዲሁም የአረም፣ የተባይና የዋግ በሽታዎችን በራሱ አቅምና በባለሙያ ድጋፍ የመከላከል ሥራ እየሠራ ይገኛል ብለዋል።

በወረዳው ያነጋገርናቸው አርሶ አደሮች በሰጡት አስተያየት የግብርና ግብዓቶች በወቅቱ በመቅረቡና የባለሙያ ድጋፍ በመኖሩ በዘንድሮው የመኸር እርሻ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

ወቅቱ የሰብል ጥበቃና የአረም ቁጥጥር ወቅት በመሆኑ ሥራውን በትኩረት እያከናወኑ እንደሚገኙ ጠቁመው፥ የግብርና ባለሙያዎች እያደረጉ ያለውን የሰብል ጥበቃና የክትትል ሥራው እስከ ምርት መሰብሰብ ድረስ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አርሶ አደሮቹ ጠይቀዋል።
ደ.ሬ.ቴ.ድ

በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በጉባ ሸረሮ ቀበሌ በአርሶአደሮችና ማሳ እና በአመመ ውስጥ  በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን ዳጉሳ እና የተለያዮ ኢንሼቲቭ  የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና  ጽ/ቤት ...
03/09/2026

በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በጉባ ሸረሮ ቀበሌ በአርሶአደሮችና ማሳ እና በአመመ ውስጥ በኩታ ገጠም እየለማ የሚገኘውን ዳጉሳ እና የተለያዮ ኢንሼቲቭ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ ከአቶ ገመዳ ሄለሞ፣ ግብርና ጽ/ቤት ምክትል ሀላፊና እርሻ ዘርፍ ሃላፊ ከአቶ አብድልቃድር አማንና ከቀበሌዉ ግብርና ባለሙያዎች ጋር ያለበትን ሁኔታ ምልከታ አደረጉ።

ነሃሴ 28/2018 ዓ.ም
የአቶቲ ኡሎ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ!!

‎የአዲስ የእይታ ውጤት በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ የ30 40 30 ኢንሼትቭ አከል የሙዝ ክላስተር በንዶጮሎቅሳ ቀበሌ አርሶአደሮች ማሰ አሁናዊ ገጽታ ፦‎‎    የሀላ...
03/09/2026

‎የአዲስ የእይታ ውጤት በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል የሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ የ30 40 30 ኢንሼትቭ አከል የሙዝ ክላስተር በንዶጮሎቅሳ ቀበሌ አርሶአደሮች ማሰ አሁናዊ ገጽታ ፦

‎ የሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ የግብርና /ጽ/ቤት

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በጮባሬ ሜኖ ቀበሌ በቅድመ በልግ የተዘራ የበቆሎ ምርት አሰባሰብ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
03/09/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በጮባሬ ሜኖ ቀበሌ በቅድመ በልግ የተዘራ የበቆሎ ምርት አሰባሰብ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

Address

Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀላባ ዞን ግብርና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የሀላባ ዞን ግብርና መምሪያ:

Shortcuts

Share