07/09/2026
ኮማንደር ኑርዬ ከድር በወቅታዊና በሀገራዊ ጉደዮች ዙሪያ ከማኔጅመንት አባለት ጋር ውይይት አደረገ
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳
ጳጉሜ 2/2018 ዓም ሀላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በሀላባ ዞን በወቅታዊ ጉደዮች ዙሪያ፦ በቁሊቶ ከተማ ህገወጥ ግንባታ መከላከልን በተመለከተ፣ ፣በሀሰተኛ ሚዲያ፣የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ፀጥታ በተመለከተ ፣መረጃ ከመሰብሰብና ክትትል በማድረግ ለሚመለከተው በወቅቱ ከማስተላለፍ ጋር በተመለከተ ከዞኑ ፖሊስ መምሪያ ማኔጅመንት አባለት ጋር ኮማንደር ኑርዬ ከድር ውይይት አድርገዋል።
በዞኑ ዋና ከተማ በሆነችዉ በቁሊቶ ከተማ የህገወጥ መሬት ወረራንና ህገወጥ ግንበታን ለመከላከልና ለመግታት ከዞኑንና ከክልል ከተወጣጡ ግብረ ሃይሎች ጋር ተቀናጅተው ወደ ስራ መግባታቸውን ኮማንደሩ ገልፀዋል።
ግብረሃይሉ ህገወጥ መሬት ወረራና ህገወጥ ግንባታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚያደርገው ክትትልን ለመደገፍ በዞኑ መዋቅር ስር የሉ የፖሊስና የፀጥታ አካለት በግብረ ሃይሎች ሆኖ ድጋፍ እያደረጉ ስለመሆናቸው ተነግሯል።
ኮማንደሩ አክለው ህገወጥ የከተማ መሬት ወረራና ህገወጥ ግንባታ ለከተማው እድጋትና ለመሠረተ ልማት መስፋፋት አዳጋች መሆኑን በመግለፅ ህገወጥ ግንባታና ህገወጥ መሬት ወረራን ለመከላከል ሁሉም ባለድርሻ አካለት የበኩላቸውን እንድወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ሀሰተኛ ሚዲያ፦ግለሰቦች የራሳቸውንና ግብረአበሮቻቸውን ጥቅምና የግል ፍላጎታቸውን ለመራመድ ሆን ብለው ሀሰተኛ ሚዲያ ወይም ጭንብል አካውንት ከፍተው የዞኑን መንግስትና ህዝብን ለማደናገር የፊት አመራሮችና አስተባባሪዎች ስም መጥፋትና ዛቻ እየተደረጉ መሆናቸውን ኮማንደሩ ተነግሯል።
በሀሰተኛ ሚዲያ መሰራጨትና በሀሰተኛ ሚዲያ ግለሰብን መስደብ ወይም በአሉባልታ ሰውን ስም መጥፋት ወንጀል መሆኑን ገልፀዋል።
በሀሰተኛ ሚዲያ በዞኑ ህዝብና መንግስት የተሰሩ በረከተ መሠረተ ልማቶችን ለመጥፋትና ስም ለማጠልሸት እንቅስቃሴ በሚያደርጉ አካለት ለይ እርምጃ ለመውሰድ ግብረሃይል ተቋቋመው ወደ ስራ መግባቱን ገልጾ በሀሰተኛ ሚዲያ እንደፈለጉ የሚሳደቡ ሃይሎች አደብ እንድገዙ ኮማንደሩ አሳስበዋል።
መረጃ፦መረጀ ህይወት ነው። መረጀ ለፖሊስ ደም ስር እንደሆነ ኮማንደር ኑርዬ ከድር አብራርተዋል።
ትክክለኛና ወቅቱን የጠበቀ መረጀ በመሰብሰብ ለሀገርና ለህዝብ ሠላም ቅድሚያ ተሰጥተው መስራት እንደሚገባ ኮማንደሩ ተነግሯል።
በመጨረሻም የሀገራችንና የህዝባችን ሠላም መጠበቅ የፖሊስና የፀጥታ አካለት ብቻ አለመሆኑን በመግለፅ የሀገርን ሠላምና ደህንነት መጠበቅ የሁሉም ነው ሁሉም ለሠላም ዘብ መቆም እንደለበት ኮማንደሩ አሳስበዋል።
ወንጀልን በጋራ እንከላከል!!