በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና!!

የዌራ ዲጆ ጤና ጽ/ቤት የጤና ቤተሰብ አባላት የነሐሴ ወር ውይይት በልሳነ-ማዕከላዊ 1ኛ ዓመት ቁጥር 5 የአባላት አጀንዳ ላይ የቤተሰብ ውይይት አደረጉ ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም | በሸኖ የዌ...
04/09/2026

የዌራ ዲጆ ጤና ጽ/ቤት የጤና ቤተሰብ አባላት የነሐሴ ወር ውይይት በልሳነ-ማዕከላዊ 1ኛ ዓመት ቁጥር 5 የአባላት አጀንዳ ላይ የቤተሰብ ውይይት አደረጉ

ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም | በሸኖ

የዌራ ዲጆ ጤና ጽ/ቤት የጤና ቤተሰብ አባላት በነሐሴ ወር ልሳነ-ማዕከላዊ የአባላት መወያያ "ለጠንካራና ቅቡልነት ያለው ዘላቂ አገረ-መንግስት ግንባታ " በሚል አጀንዳ ላይ የአባላት ውይይት ተደረገ::

ሀገራችን ኢትዮጵያ ጠንካራና ቅቡልነት ያለው አገረ መንግሥት ለመመስረትና ለመገንባት የተለያዩ ተግባራትንና የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እየሰራች እንዳለ የሚታወቅ ሲሆን በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ ዘርፎች ተጨባጭ ለውጥ በማምጣት ሀገራችንን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ቀንና ማታ እየሰራ እንዳለ ከውይይቱ መረዳት ተችሏል ፡፡

የሀገራችን ዜጎች በአካታችና በአቃፊ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ በሁሉም የልማትና ዕድገት አጀንዳዎች ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ በሁሉም አጋጣሚዎች አይተኬ ሚናቸውን ማሳረፍ እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል፡፡

በአጠቃላይ ለአንድ አገር ጠንካራና በሁሉም የልማትና የዕድገት መንገዶች ፊት የወጣ የመንግሥት አደረጃጀት መኖር ለዜጎች ዋስትና ስለሆነ የቤተሰቧ አባላት ለዚህ ሁሉ አቀፍና አካታች የፖለቲካ ሥርዓት መገንባት ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚገባ የቤተሰቧ አባላት ተናግረዋል ፡፡

በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች በናፍጣ አገልግሎት እየሰጡ  የሚገኙ የንጽሁ መጠጥ ውሃ ተቋማትን በኤሌክትሪክ ለመቀየር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።በዌራ ዲጆ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች በናፍጣ አገ...
03/09/2026

በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች በናፍጣ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የንጽሁ መጠጥ ውሃ ተቋማትን በኤሌክትሪክ ለመቀየር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዌራ ዲጆ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች በናፍጣ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የንጽሁ መጠጥ ውሃ ተቋማትን በኤሌክትሪክ ለመቀየር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም የያቶ ባረሆ ቀበሌ የንጽሁ መጠጥ ውሃ በኤሌክትሪክ ለመቀየር የኤሌክትሪክ ፖል በማስገባት በህብረተሰቡ ተሳትፎ ፖሉን ወደ ሚተከልበት ስፍራ የማጓጓዝ ስራ እየተሰራ ነው።

መርሃ-ግብሩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣ከሌሎች የወረዳ አመራሮችና ከቀበሌ አመራሮች ጋር በቦታው ተገኝተው ምልከታ በማድረግ፣ህብረተሰቡን አበረታተዋል።

በቀጣይ የቀበሌው የንጽሁ መጠጥ ውሃ ተቋም በኤሌክትሪክ ተቀይሮ ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ከወረዳው ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 28/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

የጤና መድህን አባል በመሆን የቤተሰብዎንና የወገንዎን ጤና እና ህይወት ይታደጉ።
02/09/2026

የጤና መድህን አባል በመሆን የቤተሰብዎንና የወገንዎን ጤና እና ህይወት ይታደጉ።

የጤና ባለሙያዎች አለባበስ፡ የሙያዊነት፣ ንጽህናና የታካሚ እምነት መገለጫበጤና ተቋማት የጤና ባለሙያዎች አለባበስ የግል ገጽታ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሙያዊነት፣ የንጽህና፣ የደህንነትና የታካሚ ...
01/09/2026

የጤና ባለሙያዎች አለባበስ፡ የሙያዊነት፣ ንጽህናና የታካሚ እምነት መገለጫ

በጤና ተቋማት የጤና ባለሙያዎች አለባበስ የግል ገጽታ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሙያዊነት፣ የንጽህና፣ የደህንነትና የታካሚ እምነት ግንባታ አንዱ አካል መሆኑ ተገለጸ።

ተገቢ፣ ንጹህና ሥርዓታማ የሥራ ልብስ መልበስ የጤና ባለሙያውን ሙያዊ ማንነት ከማሳየት ባለፈ፣ ታካሚዎች በባለሙያውና በተቋሙ እንዲተማመኑ ያግዛል። ዩኒፎርምና የመለያ ባጅም ታካሚዎች የተለያዩ የጤና ሙያተኞችን በቀላሉ እንዲለዩ ያመቻቻል።

ከዚህ በተጨማሪ ንጹህ የሥራ ልብስ፣ ተገቢ ጫማና በሥራው ዓይነት መሠረት ጓንት፣ ማስክና ሌሎች የግል መከላከያ መሣሪያዎችን (PPE) መጠቀም የኢንፌክሽን ቁጥጥርንና የሥራ ደህንነትን ይደግፋል። በተለይም በላብራቶሪ፣ በቀዶ ሕክምናና በኢንፌክሽን ስጋት ባላቸው የሥራ አካባቢዎች ተገቢውን የመከላከያ ልብስ መጠቀም ወሳኝ ነው።

የጤና ባለሙያዎች የሥራ ልብሳቸውን ንጹህና የተስተካከለ ማድረግ፣ የግልና የሥራ ልብስን በአግባቡ መለየት፣ የግል ንጽህናን መጠበቅና የተቋሙን የአለባበስ መመሪያ መከተል ይጠበቅባቸዋል። ሥራን የሚያደናቅፍ አለባበስ፣ ከመጠን ያለፈ ጌጣጌጥ ወይም የቆሸሸና የተበከለ የሥራ ልብስም መወገድ አለበት።

በመጨረሻም፣ ሙያዊ አለባበስ ብቻውን ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን አያረጋግጥም፤ ነገር ግን ከእውቀት፣ ክህሎት፣ ንጽህና፣ ትህትናና ሙያዊ ሥነ-ምግባር ጋር ሲጣመር የታካሚን እምነት እና የተቋሙን መልካም ስም ለማጠናከር ወሳኝ ሚና ይኖረዋል።

ንጹህ አለባበስ— ሙያዊ ክብር_የተሻለ የጤና አገልግሎት።

እንኳን ደስ አላችሁ - እንኳን ደስ አለን!!!የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ በክልል ደረጃ በከፍተኛ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ!የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ በክልል ደረጃ በ2018 ከፍተኛ አፈጻጸም  በማስ...
01/09/2026

እንኳን ደስ አላችሁ - እንኳን ደስ አለን!!!

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ በክልል ደረጃ በከፍተኛ አፈጻጸም ተሸላሚ ሆነ!

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ በክልል ደረጃ በ2018 ከፍተኛ አፈጻጸም በማስመዝገቡ ተሸላሚ ሆኗል።

በዚህም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጤና ቢሮ በወልቂጤ ከተማ ባካሄደው የ2018 እቅድ አፈጻጸምና የ2019 ግቦች ሴክቶሪያል ጉባኤ የሀላባ ዞን ጤ መምሪያ በ2018 አጠቃላይ ተግባራት አፈጻጸም ከክልሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች 2ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫ፣ የኮምፒውተር እና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል።

የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ ለዚህ ከፍተኛ ውጤት መመዝገብ አስተዋጽኦ ያበረከቱ የዞን አስተዳደርና የፊት አመራሮች የወረዳና የከተማ አስተዳደሮችና አመራሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል።

በተያያዘም በዞን ደረጃ በሁሉም ዘርፎች የታቀዱ እቅዶች ከግብ እንዲደርሱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተለመደ ትብብራቸውንና ቅንጅታዊ ስራዎችን አጠናክረው እንዲያስቀጥሉ መምሪያው የጥሪ መልዕክቱን አስተላልፏል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማት አገልግሎት እና የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት  በተከናወኑ ስራዎች ውጤት ተመዝግቧል :- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ (ሆሳዕና...
01/09/2026

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማት አገልግሎት እና የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ስራዎች ውጤት ተመዝግቧል :- ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ

(ሆሳዕና ፣ነሐሴ 26/2018)"ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሀሳብ በወልቂጤ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የጤና ሴክተር ጉባኤ ተጠናቋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ እንደገለጹት በክልሉ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትን እና ተደራሽነትን ለማሻሻል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል።

በክልሉ ባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማት አገልግሎት እና የመሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ስራዎች ውጤት መመዝገቡን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ጠቁመዋል።

በጤና ተቋማት ቀልጣፋ፣ውጤታማ እንዲሁም ጥራት ያለው አገልግሎት ከመስጠት አንጻር በሚፈለገው ደረጃ አለመሆኑን አቶ አንተነህ አንስተዋል።

የጤና ተቋማት የህብረተሰቡን እርካታ መሰረት አድርገው መስራት እንዳለባቸውም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

በክልሉ ሞዴል ወረዳዎችን ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት በልዩ ትኩረት ሊሰራ እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በክልሉ በዲጂታል መድሀኒት ቤቶች አገልግሎት ላይ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ስራ ውጤታማ ስለመሆኑም ጠቅሰዋል።

የነፍሰ ጡር እናቶች እና የህጻናት ማቆያ ማዕከላትን በማቋቋም ረገድ መሰረታዊ ለውጥ ስለመኖሩም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በአብነት ጠቅሰዋል።

በክልሉ በ54 ጤና ጣቢያዎች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማዘመን የአልትራ ሳውንድ አቅርቦት ላይ የተጀመረውን ጥረት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

ክልሉ ሲመሰረት ተቀዛቅዞ የነበረው የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም በአዲስ መልክ ማነቃቃት መቻሉን ጠቁመዋል።

የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ የማድረግ ጥረት፣የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ እና አጠቃቀም፣የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥር እና ህክምና ላይ ለውጥ መኖሩን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አብራርተዋል።

በክልሉ የጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ካለው የላቀ ጠቀሜታ አንጻር በዘርፉ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አቶ አንተነህ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የጤና አገልግሎትን በማሻሻል የእናቶችን እና የህጻናትን ሞት መቀነስ ስለመቻሉም አመላክተዋል።

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የተናገሩት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ይህን አስቀድሞ ለመከላከል የጤና ተቋማት በትኩረት መስራት አለባቸው ብለዋል።

የግብአት አስተዳደር እንዲሁም የመድሀኒት አቅርቦት ስራ ውጤታማ እንዲሆን መስራት እንደሚገባም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

ተላላፊ በሽታዎችን በቅድመ መከላከል ስራ ምላሽ መስጠት እንደሚገባም ጠቅሰዋል።

ህብረተሰቡን በማሳተፍ የሀብት አሰባሰብ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ያሉት አቶ አንተነህ በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራት ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ ሚፈለገው ደረጃ ለማድረስ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እንደሚገባም ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ እንደገለጹት በጤናው ዘርፍ እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት በማሻሻል ለዘርፉ እድገት በትኩረት መስራት ተገቢ ነው ብለዋል።

በጤና ተቋማት የመድሀኒት እና የግብአት አቅርቦትን በማሻሻል ረገድ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አቶ ሳሙኤል ጠቁመዋል።

በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል ለባለሙያዎች ምቹ ሁኔታ መፍጠር ተገቢ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በአንድ አንድ አካባቢዎች የጤና ተቋማትን ደረጃ ማሻሻል ላይ ፍላጎት መኖሩን የጠቆሙት ኃላፊው ዘርፉ በቂ የፋይናንስ እና የሰው ሀይል የሚጠይቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በጥንቃቄ ሊመራ ይገባል ብለዋል።

በዋናነት በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት ጥራት እና የህዝብ እርካታ ማረጋገጥ ተገቢ መሆኑን አቶ ሳሙኤል አስታውቀዋል።

ከተማ አስተዳደሮች በጤናው ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የመሰረተ ልማት አቅርቦት ላይ እየሰሩ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

በክልሉ በ2019 በጀት ዓመት በጤና ተቋማት የሚሰጠውን አገልግሎት በውጤታማነት ለማሻሻል የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ኃላፊው ጠቁመዋል።

በጉባኤው በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በተስፋዬ መኮንን

ምርጫችሁ ስላደረጋችሁን እናመሰግናለን !!

የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የአልጋ አጎበር አጠቃቀም ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለፀ።ነሃሴ 26/2018፦ በሸኖበዌራ ዲጆ ወረዳ የወባ መከላከልና መቆጣጠር ተግባራት ክትትልና የተቋማት...
01/09/2026

የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የአልጋ አጎበር አጠቃቀም ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገለፀ።

ነሃሴ 26/2018፦ በሸኖ

በዌራ ዲጆ ወረዳ የወባ መከላከልና መቆጣጠር ተግባራት ክትትልና የተቋማት ድጋፍ ክትትል ሥራዎች ተጠናክረዉ ቀጥለዋል።

ወቅቱ የክረምት ወራትን ተከትሎ የወባ በሽታ ስርጭት የሚከሰትበት ወቅት በመሆኑ የመከላከል ስራዎች ተጠናክረዉ ቀጥለዋል።

በዚህም በወረዳው በሚገኙ ጤና ተቋማት ስር በሚገኙ ቀበሌዎች ማህበረሰቡን ያሳተፉ የወባ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ተግባር የአልጋ አጎበር አጠቃቀም ክትትል፣የግንዛቤ ማስጨበጥ ማህበረሰቡን የማንቃት ስራዎች በሰፊዉ እየተተገበሩ ይገኛሉ።

የተጀመሩ የወባ መከላከያ መንገዶች ቀጣይነት ባለዉ መልኩ ተጠናክረዉ የሚቀጥል በመሆኑም በሁሉም አከባቢ ያላችሁ የማህበረሰብ ክፍሎች የመከላከያ መንገዶቹን በመተግበር የበሽታዉን ስርጭት መግታት እንዲቻል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ተጠናክሮ ልቀጥል ይገባል።

በድጋፍ ክትትሉ ስራ የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ ባለሙያዎች፣ የጤና ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የጤና ጣቢያ ባለሙያዎች እንዲሁም የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

ወባን በጋራ እንከላከል !!

በክልሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል በቅንጅት በተሰሩት ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል - ምክትል  ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነሀ ፈቃዱነሐሴ 26/2018 ዓ.ም  በክል...
01/09/2026

በክልሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል በቅንጅት በተሰሩት ተግባራት አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነሀ ፈቃዱ

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም በክልሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን በማሻሻል በቅንጅት በተሰሩት ተግባራት አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አሰተባባሪና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነሀ ፈቃዱ ገለጹ፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ ጤና ተጠቃሚነት በሚል መሪ ቃል የ2018 የአፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት የንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው።

በንቅናቄ መድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላስተር አሰተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነሀ ፈቃዱ፤ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ መነቴ ሙንዲኖ፣ የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ክላሰተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነሀ ፈቃዱ በንቅናቄ መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በክልሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት በማሻሻል በቅንጅት በተሰሩት ተግባራት አበረታች ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

ህብረተሰቡ ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ለማሰቻል የተጀመሩ የለውጥ ሥራዎችን በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ አመላክተዋል።

የጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር በትኩረት እየተሰራ ያለው ተግባር ሊጠናከር እንደሚገባም አቶ አንተነህ አመላክተዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሣሙኤል ዳርጌ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የጤና አመራር አቅምን ማጎልበት፣ የተቋማትን አቅም ማሳደግና ጠንካራ የጤና ሥርዓት ለመገንባት በትኩረት በተሠራው ሥራ ለውጥ መጥቷል ብለዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸዉ፤ በዞኑ ፅዱ መንደር እና የበለፀገ ቤተሰብ ለመፍጠር በቅንጅት በተከናወኑ ተግባራት ለውጦች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

የህዝቡ ጤና እንዲጠብቅ በርካታ የልማት ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙና በዚህም ለውጥ መመዝገቡን ገልፀዋል።

በአሁን ወቅት በክልሉ ጤና ቢሮ የተዘጋጀ የንቅናቄ ሰነድ ላይ ዉይይት እየተደረገ ይገኛል።

‎ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ የጤናውን ዘርፍ የአፈጻጸም ግምገማና የንቅናቄ መድረክ አስጀመሩ‎‎ሆሳዕና፦ነሐሴ 26/2018‎‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደ...
01/09/2026

‎ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ የጤናውን ዘርፍ የአፈጻጸም ግምገማና የንቅናቄ መድረክ አስጀመሩ

‎ሆሳዕና፦ነሐሴ 26/2018

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር፣
‎የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ የክልሉ ጤና ቢሮ መደበኛ ጉባኤና የንቅናቄ መድረክ በወልቂጤ ከተማ አስጀመሩ።

‎ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመድረኩ የተዘጋጀውን የጤና ልማት ፎቶ አውደ ርዕይና ኤግዚቪሽን የመረቁ ሲሆን ፣የቢሮው የ2018 አፈጻጸሞች ግምገማና የቀጣይ በጀት ዓመት የጤና የንቅናቄ ስራዎች ላይም ምክክር ይደረጋል።


‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2018 ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤውን "ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ሀሳብ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እያካሄደ ነው።

‎መድረኩ የጤናው ዘርፍ ሪፎርም ስራዎች ያሉበትን ደረጃ በአግባቡ በመገምገም በጥንካሬና በጉድለት የታዩ ጉዳዮችን የሚፈትሽ ሲሆን ፣በቀጣይ በንቅናቄ ለማሳካት በተያዙ ዋና ዋና የጤና ጉዳዮች ላይ በመወያየት የጋራ አረዳድና ተነሳሽነት ለመፍጠር የታሰበ ስለመሆኑም ተገልጿል።

‎በመድረኩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ሃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ፣የክልሉ ከፍተኛ የፓርቲና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ፣የዞን የልዩ ወረዳና የወረዳ አመራሮች፣
‎የዘርፉ ባለሙያዎች፣የጤናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላትና ሌሎች ተጋባዢ እንግዶች ተገኝተዋል።

የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሳምንታዊ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ (PHEM) ሳምንታዊ RRT ግምገማ አካሂዷል።‎ነሃሴ 25/2018 ዓ.ም | በሸኖ‎በሳምንቱ ውስጥ የወ...
31/08/2026

የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሳምንታዊ የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝትና ምላሽ (PHEM) ሳምንታዊ RRT ግምገማ አካሂዷል።

‎ነሃሴ 25/2018 ዓ.ም | በሸኖ

‎በሳምንቱ ውስጥ የወባ ጫናን ጨምሮ ሌሎች ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ላይ የተከናወኑ ቅኝትና ምላሽ ተግባራት ሪፖርት በቢሮው ጤናና ጤና ነክ አደጋዎች ቅኝት ምላሽ ዳይሬክቶሬት በአቶ አ/መጂድ ሙንድኖ ቀርቦ ሰፊ ዉይይት ተደርጎባቸዋል።

‎የወረዳው የጤ/ፅ/ቤት እንደገለፁት በወረዳው የወባ ጫና በብዛት የሚስተዋልባቸዉ አከባቢዎችን በመለየት መከላከልን መሠረት ያደረገ የክትትል እና የቁጥጥር ስራዎች ላይ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

‎የስርዓተ ምግብ ጫና ያለባቸው አከባቢዎችን የልየታ ስራ ላይ ማተኮር ተገቢ መሆኑ እና በምግብ እጥረት የተጎዱ ህፃናት የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ በልዩ ትኩረት መሰራት ያስፈልጋልም ተብሏል።

‎በመድረኩ የወባና በሌሎችም ጉዳዮች ዙሪያ በሳምንቱ ውስጥ የተከናወኑ ተግባራትና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በውይይቱ የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና የጽ/ቤት ባለሙያዎች እንዲሁም የጽ/ቤቱ RRT አባለት ተገኝተዋል።

Address

Alaba K'ulito

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share