የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ

ካለን ላይ ...........አካፈልን!!!!  በጎነት የሌላን ሰዉ ችግር እንደራሳችን በመመልከት መፍትሄ ለማምጣት መረባረብ ነዉ::              ነሐሴ 30/2018          የሀላ...
05/09/2026

ካለን ላይ ...........አካፈልን!!!!

በጎነት የሌላን ሰዉ ችግር እንደራሳችን በመመልከት መፍትሄ ለማምጣት መረባረብ ነዉ::

ነሐሴ 30/2018

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ ብልፅግና ቤተሰብ በክረምት በጎ ፍቃድ ለአንድ ቤተሰብ የመኝታ አልጋ ከነፍራሹና ፍራሽ ልብሱ አበረከተ:: # # # # # # # # #

የሀላባ ዞን ኢኮኖሚ ቁጥር 2 ህብረት እንደ ህብረት በክረምት በጎ ፍቃድ ለአንድ ቤተሰብ ቤት ማስገንባቱ ይታወቃል::የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ ብልፅግና ቤተሰብ እንደህብረት ባስገነባነዉ ቤት እንደ ቤተሰብ የመኝታ ቤቱን ኮታ ሸፍነናል:: በርክክቡ ወቅት የምሪያዉ ኃላፊ ወ/ሮ ፋጤ ዩሐንስ እንደገለፁት ዛሬ በትንሿ ነገር በጎ የዋልነዉ ተግባር ነገ በማህበረሰብ በጎ መዋልን ለማስተማር ከትንሿ ስጦታ በላይ በጎ የሚዉል ማህበረሰብ ግንባታ ላይ ትልቅ አስተዋፅኦን ያበረክታል ብለዋል::

በርክክቡ የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፋጤ ዩሐንስን ጨምሮ የመምሪያዉ ማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል::

"በጎነት ለኢትዮጲያ ከፍታ"

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ

05/09/2026
ግብይትን በደረሰኝ የምናካሂደው ለምንድነው ?ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ለገዛው ዕቃ ወይም አገልግሎት ለሚከፍለው ገንዘብ ደረሰኝ መጠየቅ አለበት፡፡ ለዚህም ደግሞ የተለያዩ ጠቃሚ ምክንያቶች ...
04/09/2026

ግብይትን በደረሰኝ የምናካሂደው ለምንድነው ?

ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ለገዛው ዕቃ ወይም አገልግሎት ለሚከፍለው ገንዘብ ደረሰኝ መጠየቅ አለበት፡፡

ለዚህም ደግሞ የተለያዩ ጠቃሚ ምክንያቶች አሉ።

በግብይት ወቅት ደረሰኝ መቀበል ግዢ በትክክል መፈጸሙን ያሳያል። የከፈሉት ገንዘብ እና የገዙት ዕቃ ወይም የአገልግሎት አይነት በደረሰኙ ላይ በግልጽ ሰፍሮ ስለሚገኝ ግብይቱ ግልጽ እና ህጋዊ እንዲሆን ያደርጋል።

ከገዙ በኋላ ዕቃው ላይ ችግር ቢያጋጥም ወይም ዕቃውን ለመመለስ ቢፈልጉ ፣ ደረሰኝ እንደማስረጃ ሆኖ ያገለግላል። ደረሰኝ ከሌለ የገዙትን ዕቃ ለመመለስ ወይም ለማስቀየር ችግር ይገጥሞታል።

ደረሰኝ ጠይቆ መቀበል ሕጋዊና ስልጡን የንግድ ስርዓት መኖሩን ያመላክታል። ደረሰኝ ሲቀበሉ፣ ገቢዎች በትክክል ይመዘግባሉ። መንግስትም ትክክለኛውን የግብር ገቢ ያገኛል፡፡ የሚሰበሰበውም ግብር ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ መሰረተ ልማቶችን ማለትም መንገድ ፣ ትምህርት ቤት እና ሆስፒታሎችን ወዘተ. ለመገንባት እና ለማሻሻል ያግዛል።

ግብይቶች ያለደረሰኝ ሲካሄዱ፤ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግ ይችላል። ደረሰኝ መቀበል አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይደረግ ለመቆጣጠር ይረዳል፡፡

በአጠቃላይ ፣ ግብይቶችን በደረሰኝ ማካሄድ በግል ከምናገኘው ጥቅም ባሻገር የሀገርን የገቢ አሰባሰብ፣ የንግድ ስርአት እና ኢኮኖሚን ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

ኃላፊዋ በቁሊቶ ከተማ የሚሰበሰበዉን ዕለታዊ ገቢ ተዟዙረዉ ምልከታ አደረጉ::              ነሐሴ 28/18  የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፋጤ ዩሐንስ በቁሊቶ ከተማ የሚሰበ...
03/09/2026

ኃላፊዋ በቁሊቶ ከተማ የሚሰበሰበዉን ዕለታዊ ገቢ ተዟዙረዉ ምልከታ አደረጉ::

ነሐሴ 28/18

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፋጤ ዩሐንስ በቁሊቶ ከተማ የሚሰበሰበዉን ዕለታዊ ገቢ(የጫት ቀረጥ) ተዟዝረዉ ምልከታ አድርገዋል::

እንደሚታወቀዉ በዞኑ በሁሉም መዋቅር የበጀት አመቱን ዕቅድ እስከ ጳጉሜ 3/18 ድረስ 18.4 በመቶ ለማድረስ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል::ይህን ዕቅድ ለማሳካት ተቋሙ በተለያዩ የታክስ ማዕከላት ላይ ድጋፍ እያደረገም ይገኛል::

ኃላፊዋ በየታክስ ማዕከላቱ ለድጋፍ ስምሪት የተሰጣቸዉን ባለሞያዎችን ድጋፍና ክትትል ያደረጉ ሲሆን ሁሉም የተቋሙ ባለሞያ ይህን ዕቅድ ለማሳካት የድርሻዉን ማዋጣት እንዳለበት እና በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንደሚገባ አፅኖኦት ሰጥተዉ አስገንዝበዋል::

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ

የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያን ለማስተካከል የሚያስችሉ ምክንያቶች(ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም )በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 96 መሰረት በታክስ ውሳኔ ...
03/09/2026

የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያን ለማስተካከል የሚያስችሉ ምክንያቶች

(ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም )በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 96 መሰረት በታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ላይ ማስተካከያ ሊደረግ የሚችለው፦

👉 የስሌት ወይም የሂሳብ ስህተት ያለ ከሆነ፤
👉 በታክስ አወሳሰን ወቅት ያልታየ አግባብነት ያለው ማስረጃ ወይም በዚህ አዋጅ መሰረት የቀረበ አዲስ ማስረጃ ያለ እንደሆነ፤
👉 የታክስ ውሳኔው አስገዳጅ ከሆነው የታክስ ህጎች ትርጉም ጋር የማይጣጣም ከሆነ፤ ወይም
👉 ታክስ የመክፈል ግዴታን በመወሰን ረገድ የተሳሳተ ውጤት የሚያስከትል ሌላ ስህተት ካለ ነው፤

👉(የገቢዎች ሚኒስቴር)

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
02/09/2026

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች

ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”

ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”

ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”

ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”

ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታትነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር) በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የ...
02/09/2026

የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታት

ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ለመፍታት ያለውን ስልጣን በተመለከተ የሚከተለውን ይላል፡-

👉 የታክሱ ባልስልጣን የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን ተሰጥቶታል።
👉 ማናቸውም በስምምነት የሚፈታ የታክስ ያለመግባባት በጽሁፍ የሚደረግ እና የተስማሚ ወገኖች ፊርማ ያረፈበት ሊሆን ይገባል።
👉 የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን የሰጠው ድንጋጌ ቢኖርም የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲኖሩ ጉዳዩ በማስማማት ሊታይ አይችልም፦
1. የታክስ ማጭበርበር ወይም ሆን ተብሎ የተደረገ ታክስን የመሰወር ድርጊት መኖሩ ወይም ሌላ ከታክስ ጋር የተገናኘ ወንጀል መኖሩ ሲጠረጠር፤
2. በማስማማት የሚደረግ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት እና ከሚመለከታቸው የታክስ ሕጎች ጋር የሚጋጭ ሲሆን፤
3. ከሁለቱ ወገኖች አንዱ በሽምግልና ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ካልሆነ።
👉 ሚኒስቴሩ የአስማሚውን የትምህርት እና ሙያ ደረጃን ጨምሮ የመስማማት ሂደት የሚመራበትን ሥርዓት የሚወስን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ያወጣል፡፡

እንኳን ደስ አለን....እንኳን ደስ...አላችሁ!!!! መስሪያ ቤታችን የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገቡ የዋንጫና የዕዉቅና ሰርተፍኬት ተበረከተለት።             ነሐሴ 26/2018የሀላባ ዞ...
01/09/2026

እንኳን ደስ አለን....እንኳን ደስ...አላችሁ!!!!

መስሪያ ቤታችን የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገቡ የዋንጫና የዕዉቅና ሰርተፍኬት ተበረከተለት።
ነሐሴ 26/2018
የሀላባ ዞን ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የዞን ማዕከል ተቋምና ለመዋቅሮች የእውቅና እና የሽልማት መድረክ አካሂዷል========

በበጀት አመቱ በዞኑ ውስጥ ካሉት መንግስት መ/ቤቶች የመንግስት ሀብት አጠቃቀምን ከብሊሹ አሰራር በመከላከል እና የአገለግሎትን አሰጣጥን በማዘመን የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ 3 መስሪያ ቤቶች ተሸልመዋል::

#1ኛደረጃ ፋይናንስ መምሪያ ፤ #2ተኛደረጃ የሀላባ ቁሊቶ አጠቃላይ ሆስፒታል ፤ 3ተኛደረጃ የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ የዋንጫና የእውቅና ሰርተፍኬት አግኝተዋል።

ይህ እዉቅና በጋራ ጥረት እና ዉጤት የተገኘ በመሆኑ በድጋሚ አንኳን ደስ አለን/አላችሁ!!

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በሀላባ ዞንና ቁሊቶ ከተማ የ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን የድጋፍና ክትትል ስራ አደረገ(ነሀሴ 25/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በሀላ...
01/09/2026

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በሀላባ ዞንና ቁሊቶ ከተማ የ2019 በጀት ዓመት የገቢ አሰባሰብ ስራዎችን የድጋፍና ክትትል ስራ አደረገ

(ነሀሴ 25/2018) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ በሀላባ ዞን የነሀሴ ወር 18 እስከ 25 ድረስ የገቢ አፈጻጸምና ግምገማ ቀጣይ ገቢ አሰባሰብ ላይ የድጋፍና ክትትል ሥራ አካሂዷል።

በዞኑ የበጀት ዓመቱን የገቢ ዕቅድ እስከ ጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም ድረስ 18.4 በመቶ ለማድረስ በተያዘው ዕቅድ መሰረት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በየወቅቱ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

በዛሬው ዕለትም ባለፉት 7 ቀናት ገቢ አሰባሰብ ስራዎችን ከዞኑ ገቢዎች መምሪያ እና ከሀላባ ቁሊቶ ከተማ የገቢ ማኔጅመንት ጋር በመሆን የአፈጻጸም ሂደትን በጥልቀት ገምግመዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ደግፍ መለሰ እንደገለጹት የተቀመጠው የገቢ ግብ እንዲሳካ ባለድርሻ አካላት ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንዳለበት ጠቁመዋል።

መሰረታዊ የገቢ አሰባሰብ እና ቁጥጥር ዘርፎች፣ የደረሰኝ ቁጥጥር ስርዓትን ማጠናከር፣ የኦዲት ግኝት ገቢዎችን ከመቶ ፐርሰንት በላይ አጥልቆ መሰብሰብ፣ የማዘጋጃ ቤት መደበኛ ገቢ አሰባሰብን ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

የገቢ አማራጮችን በመፈለግ የተሻለ ገቢ በመሰብሰብ የኢኮኖሚ አቅም ለማጎልበት በቅንጅትና በትጋት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የከተማውን የውስጥ ገቢ አሰባሰብ አቅምን ለማሳደግ የገቢ ምንጪዎችን በማስፋት ገቢውን አሟጦ በመሰብሰብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ ሀላፊ ወይዘሮ ፋጤ ዮሀንስ በበኩላቸው በሁሉም ዘርፍ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ ለህብረተሰቡ መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መመለስና የአመቱን ዕቅድ ለማሳካት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

እስካሁን የታዩ ጥንካሬዎችን በማስቀጠልና ጉድለቶችን በማረም የታቀዱ የልማት ጥያቄዎችን የሚመልስ ገቢ ለመሰብሰብ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በውይይቱ ላይም የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ገቢ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አ/ቃድር ኢማም ሎላሶ፣ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ እና የዞንና የከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ማኔጀመንት አባላት ተገኝተዋል።

👉የሀ/ዞ/መ/ኮ

የተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ የማስረዳት ኃላፊነት እና አዲስ ማስረጃ ማቅረብን በተመለከተ ምን ይላል?(ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም )በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁ...
31/08/2026

የተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ የማስረዳት ኃላፊነት እና አዲስ ማስረጃ ማቅረብን በተመለከተ ምን ይላል?

(ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም )በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 59 መሰረት ከታክስ ውሳኔ ጋር በተገናኘ በሚደረግ ማናቸውም የታክስ ክርክር ሂደት የታክስ ውሳኔ ትክክል ያለመሆኑን የማስረዳት ኃላፊነትን እና አዲስ ማስረጃ ማቅረብን በተመለከተ የሚከተለውን ይላል፡-

ከታክስ ውሳኔ ጋር በተገናኘ በሚደረግ ማናቸውም የታክስ ክርክር ሂደት የታክስ ውሳኔ ትክክል ያለመሆኑን የማስረዳት ኃላፊነት የታክስ ከፋዩ ነው፡፡

በዚህ አዋጅ መሰረት ቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም የውሳኔ ማስተካከያ ጥያቄን የሚያቀርብ ታክስ ከፋይ በታክስ ውሳኔ ወቅት ካቀረበው የተለየ አዲስ ማስረጃን ማቅረብ አይችልም፡፡

ይሁን እንጂ ይህ ድንጋጌ ቢኖርም አዲስ ማስረጃ በቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም ስህተትን ለማረም በሚቀርብበት ወቅት ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው፦

👉 የማስረጃው አለመታየት በታክስ ከፋዩ የታክስ እዳ ላይ ከፍተኛ ጫናን የሚያስከትል ከሆነ፤
👉 ታክስ ከፋዩ ማስረጃውን ያገኘው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ ከሆነ፤ ወይም
👉 ሰነዱ ያልቀረበው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሆነ፤ ይሆናል፡፡

በዚህ አዋጅ መሰረት “አዲስ ማስረጃ” ማለት የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ በታክስ ከፋዩ የሚቀርብ አዲስ ሰነድ፤ መረጃ፤ ማስረጃ፤ ፍሬ-ነገር ሲሆን፤

👉 በመጀመሪያው የታክስ አወሳሰን ሂደት ለታክስ ባለስልጣኑ ያልቀረበ፤
👉 ለታክስ ውሳኔ ማስታወቂያው ትክክለኛነት አግባብነት ያለው እና መሰረታዊ የሆነ፤ እና
👉 በተወሰነው የታክስ መጠን ወይም በታክስ ከፋዩ ግዴታ ላይ መሰረታዊ ለውጥ የሚያስከትል ነው፡፡

(የገቢዎች ሚኒስቴር)

Address

Halaba Zone Revenue Department
Alaba K'ulito

Telephone

+251923905357

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሀላባ ዞን ገቢዎች መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share