07/08/2026
የሀላባ ቁሊቶ ማረሚያ ተቋም የሕግ ታራሚዎች የይቅርታ መልማይ ኮሚቴ በይቅርታ በሚፈቱ ታራሚዎች አፈፃፀም ዙሪያ ውይይት ተካሄደ
*********
ነሐሴ፣1/2018 የቁሊቶ ከተማ ማረሚያ ተቋም የይቅርታ ተጠቃሚ የሕግ ታራሚዎች ምልመላና መረጣ ኮሚቴ የይቅርታ ጥያቄ የተመለከቱ ተግባራት ላይ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሄዷል።
ውይይቱ በተካሄደበት ወቅት እስካሁን ድረስ በታራሚዎች ምልመላና መረጠ ዙሪያ የተሰሩ ተግባራትን የቁሊቶ ማረሚያ ተቋም ኃላፊና መልማይ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ረዳት ኢንስፔክተር ሁሴን ጉንታ በዝርዝር አቅርበው የኮሚቴው አባላት በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ሀሳብ አንስተው ወይይት ተደርጓል።
የይቅርታ መልማይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ገራሙ ሱንክቻ እንደገለጹት የይቅርታ ጥያቄ ምልመላና መረጣ ኮሚቴ በመመሪያ መሠረት ይቅርታን የተመለከቱ የህግ ማዕቀፎች ዋና ዓላማ በማረሚያ ተቋማት የሚታረሙ የህግ ታራሚዎች ይቅርታ የሚያሰጡ ዝርዝር መስፈርቶችን በመደንገግ እንዲሁም
በማረሚያ ተቋማት ውስጥ በመታረም ላይ የሚገኙ የህግ ታራሚዎች የሚያቀርቧቸውን የይቅርታ ጥያቄዎችን ተቀብሎ በመርመር በፍትሃዊነት የሕግ ታራሚዎችን የይቅርታ ጥያቄዎችን መርምሮ የይቅርታ የውሳኔ ሃሳብ ለክልሉ ፍትህ ቢሮ ለማቅረብ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተሻሻለው አዋጅ መሰረት ይቅርታ የማያሰጡ ለአብነትም አስገድዶ መድፈር፣ጠለፋ፣ግብረሰዶም፣የግፍ ግ ዲያ።ከባድ ውንብድና የሙስና ወንጀሎች፣ህገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት፣በልማት አውታሮች ላይ ወንጀል መፈጸም፣
ይቅርታ አግኝቶ ዳግም ወንጀል ፈጽሞ ወደ ማረሚያ ተቋም የገባ፣ከማረሚያ ቤት ልያመልጥ የሞከረ ለማምለጥ የዲሲፕሊን ጥሰት መፈጸም በዐቃቤ ሕግ የይግባኝ ወይም የሰበር አቤቱታ የቀረበበት ታራሚ እነዚህ በዋነናነት ይቅርታን የማያሰጡ ወንጀሎች መሆናቸውን የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ገረሙ ተናግረዋል ።
በመጨረሻም የቁሊቶ ማረሚያ ተቋም የሕግ ታራሚዎች የይቅርታ ጥያቄ መልማይ ኮሚቴ የ2018 1ኛ ዙር የይቅርታ ተጠቃሚ የህግ ታራሚዎች ምልመላና መረጣው በመስፈርቱ መሠረት መሆኑን በማረጋገጥ ለሚመለከተው ለክልሉ ፍትህ አካል እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ ውሳኔ በማሳለፍ የዕለቱን ውይይት አጠናቋል።