Halaba Zone Health Department - የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ

Halaba Zone Health Department - የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ This is the official Halaba Zonal Health Dept page you can get all the latest information’s.

Detail contact information to follow us:
https://halaba.gov.et/

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት በወቅታዊ እና ዋና ዋና የጤና ልማት ስራዎች ግምገማ አካሄደ ፡፡የቢሮ ማኔጅመንት ፣ የዞን እና ልዩ ወረዳ ጤና ኃላፊዎች በተገኙበት ...
16/08/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት በወቅታዊ እና ዋና ዋና የጤና ልማት ስራዎች ግምገማ አካሄደ ፡፡

የቢሮ ማኔጅመንት ፣ የዞን እና ልዩ ወረዳ ጤና ኃላፊዎች በተገኙበት በተካሄደው የቨርቹዋል ግምገማ ወርሃዊ መደበኛ እና ወቅታዊ የጤና ልማት ስራዎች አፈጻጸም ሪፖርት ዞኖች በማቅረብ ተገምግሟል ፡፡

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዳርጌ በማጠቃለያው በሰጡት ማብራሪያ አብዛኛዎቹ መደበኛ እና ወቅታዊ የጤና ልማት ስራዎች በእቅድ በመመራቱ በጥሩ ሁኔታ እየተፈጸመ መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ በቢሮው ኃላፊዎች የተመራ ቡድን ለጤና ልማት ስራው አጋዥ የሆነ ጉብኝት በቤተሰብ በጤና ተቋማት ደረጃ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል፡፡

አገራዊ የጤና ገባኤ (MOH ARM) አዘጋጅ ክልል መሆናችንን ታሳቢ ያደረጉ ዝግጅቶች በተጀመረው ልክ ከሚመለከታቸው ባለድረሻ ጋር በቅንጅት ማጠናከር እንደሚገባ አቶ ሳሙኤል አሳስበዋል ፡፡

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በአጆ ሁሉቆ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡንና የመሰረተ ልማት ስራዎች የቦርድ አባላት ተዟዙረው ምልከታ አደረጉ።በዌራ ዲጆ ወረዳ ...
14/08/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በአጆ ሁሉቆ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡንና የመሰረተ ልማት ስራዎች የቦርድ አባላት ተዟዙረው ምልከታ አደረጉ።

በዌራ ዲጆ ወረዳ የአጆ ሁሉቆ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡንና የመሰረተ ልማት ስራዎች የቦርድ አባላት ተዟዙረው ምልከታ አድርጓል።

በምልከታው ወቅትም በጤና ጣቢያው ውስጥ እየተከናወነ የሚገኘው የውስጥ ለውስጥ መንገድ ጥገና ስራ፣በድንገተኛ ህክምና ክፍል፣በእናቶና ህፃናት ህክምና ክፍል፣በመድሀኒት ክፍል እንድሁም በአዋቂዎችና በሌሎች በተለያዩ ህክምና ክፍሎች ተዟዙረው ምልከታ ለማድረግ ችለዋል።

ከምልከታው ቀጥሎ የጤና ጣቢያውን የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦርዱ አባላት የሚካሄድ ይሆናል።

በምልከታው የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዲ አደም፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሃእሻ አበቴ፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/ቃድር ናስር፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በድሩ ዴብሶን ጨምሮ ሌሎች የቦርድ አባላት፣ከጤና ጣቢያው ከየስራ ክፍሉ የተወጣጡ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የኤች አይ ቪ ስርጭትንና በኤድስ አማካኝነት የሚመጣውን የጤና ተጽዕኖ ለመቀነስ በየደረጃው ያሉ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተነገረ።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ...
14/08/2026

የኤች አይ ቪ ስርጭትንና በኤድስ አማካኝነት የሚመጣውን የጤና ተጽዕኖ ለመቀነስ በየደረጃው ያሉ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተነገረ።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ኤድስ፣ ቫይራል ሄፓታይተስ እና የአባላዘር በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት የ2018 ዓ/ም የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

ኤች አይ ቪ ኤድስ በአለማችን መከሰቱ ከታወቀበት ጀምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ ከ42.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን 39.9 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ በአሁኑ ጊዜ ኤች አይ ቪ በደማቸው እንደሚገኝ የ2024 UNAIDS ሪፖርት ያሳያል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ መድረኩን ባጠቃለሉበት ወቅት እንደተናገሩት የኤች አይ ቪ ስርጭትንና በኤድስ አማካኝነት የሚመጣውን የጤና ተጽዕኖ ለመቀነስ በየደረጃው ያሉ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ ነው።

አቶ አሸናፊ፦ ስርጭቱ በ2030 ላይ የህብረተሰቡ የጤና ችግር በማይሆን ደረጃ ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አንስተዋል።

በበጀት አመቱ የመጣውን ውጤት ለማስቀጠልና የተሻለ የጤና ስርዓት ለመገንባት የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል የተገባ ነው ሲሉም ተደምጠዋል ኃላፊው።

ለዘርፉ ስኬታማነት የውስጥ ገቢ ማመንጨት ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባም ተናግረዋል።

ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑ ህብረተሰብ ክፍሎች ላይ መሠረት አድርጎ በመሥራት በልዩነትና በእቅድ ለውጤት መትጋት ያስፈልጋል ብለዋል።

በኤች አይ ቪ ኤድስ ዙሪያ የሚሰሩ ማህበራትን መደገፍና አቅም ማጎልበት ልየለ ተግባር ሊሆን እንደሚገባም አንስተዋል አቶ አሸናፊ።

የተሻለ የጤና ሥራ አፈጻጻምና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመሥጠት ተቋማዊ ቅንጅት ተግባሮች ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።

በቢሮው የዘርፈ ብዙ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ጌታቸው በበኩላቸው በበጀት ዓመቱ ወቅቱን የጠበቀ መደበኛ የኤች አይ ቪ ፕሮግራም ተኮር ድጋፋዊ ክትትል ሲደረግ መቆየቱን አንስተዋል።

በተለያዩ ጊዜያት ፕሮግራም ክፍተቶችን መሰረት ያደረገ ድጋፋዊ ክትትል ተደርጎ በዚህም ከእናቶችና ህጻናት፣ ከክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ጋር በመተባር የተጋላጭ ህጻናት ህጻናት ኤች አይ ቪ ምርመራ አገልግሎት ለማጠናክር በበርካታ ጤና ተቋማት ሜንቴር ሽፕ እና ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል

በዞኑ የምገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ከመዘናጋትና ቸልተኝነት ወጥተው ጤናቸውን መጠበቅ እንድችሉ ችግሩን የመለየትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተሰርቷል ያሉት ደግሞ የሀዲያ ዞን ጤና መማሪያ ኃላፊ ዶ/ር ደሣለኝ ሽጉጤ ናቸው።

ለዚህም የተቀመጣውን ሀገራዊ ዕቅድ ለማሳካት ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማዕከል በማድረግ በልዩ ትኩረትና በላቀ ቁርጠኝነት ይሰራል ነው ያሉት ኃላፊው።

በወቅቱም ዳይሬክቶሬቱ ከታች ካሉ መዋቅሮች ጋር የ2019 ዓ/ም የዕቅድ ግብ ስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በወጀጎ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡን የቦርድ አባላት ተዟዙረው ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።በዌራ ዲጆ ወረዳ የወጀጎ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡን...
14/08/2026

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በወጀጎ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡን የቦርድ አባላት ተዟዙረው ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።

በዌራ ዲጆ ወረዳ የወጀጎ ጤና ጣቢያ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጡን የቦርድ አባላት ተዟዙረው ምልከታ እያደረጉ ነው።

በምልከታው ወቅትም በበጎ ፍቃድ አገልግሎት የስኳርና የግፊት ምርመራ፣በድንገተኛ ህክምና ክፍል፣በእናቶና ህፃናት ህክምና ክፍል፣በመድሀኒት ክፍል እንድሁም በአዋቂዎችና በሌሎች በተለያዩ ህክምና ክፍሎች ተዟዙረው ምልከታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

ከምልከታው ቀጥሎ የጤና ጣቢያውን የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በቦርዱ አባላት የሚካሄድ ይሆናል።

በምልከታው የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አብዲ አደም፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሃእሻ አበቴ፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/ቃድር ናስር፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በድሩ ዴብሶን ጨምሮ ሌሎች የቦርድ አባላት፣ከጤና ጣቢያው ከየስራ ክፍሉ የተወጣጡ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

(ዌራ ዲጆ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን)

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የተቋሙንና የጤና ጠቢያዎችን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2019 እቅድ ላይ ውይይት አካሄደ!!!የሀላባ ዞን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ...
13/08/2026

የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የተቋሙንና የጤና ጠቢያዎችን የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2019 እቅድ ላይ ውይይት አካሄደ!!!

የሀላባ ዞን የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የተቋሙንና የጤና ጣቢያዎችን የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወራት አፈፃፀም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ላይ የሚደረግ የውይይት መድረክ አካሄደዋል።

መድረኩን መክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ እንደገለፁት ጤና ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ ያከናወናቸው ተግባራት አበረታች መሆናቸውን ገልጸው ጤናማ ትውልድ ለመፍጠር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ በተቋሙ እና በከተማ አስተዳደሩ ጤና ጣቢያዎች የተከናወኑ ዋና ዋና የስራ አፈፃፀሞች በዝርዝር ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በቀረበው ሪፖርት መነሻነት የሀላባ ቁሊቶ ከተማ አስተዳደር የምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ስቲና ሁሴን እና የከተማ አስተዳደሩ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈዲን ቱልሳ በጋራ በመሆን የመድረኩን ተሳታፊ አወያይተዋል።

የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ ሰይፈዲን በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ስኬቶች ይበልጥ በማስቀጠል እና ክፍተቶችን በማረም የህብረተሰባችንን የጤና ችግሮች በዘላቂነት ለመቅረፍ ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል።

የጤና ባለሙያዎችና አመራሩ የህዝብ አገልጋይ በመሆናቸው ከሁሉም ባለድርሻ ጋር ተቀናጅተን ጥራት ያለውና ፍትሃዊ አገልግሎት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

ጽ/ቤቱ ህብረተሰቡን ያማከለ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ፣ የእናቶችና ህፃናት ጤናን በይበልጥ ለመጠበቅ እንዲሁም የበሽታ መከላከል ስራዎችን አጠናክሮ ለመቀጠል በ2019 በጀት ዓመት አበክሮ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ሰብሳቢ የወ/ሮ ስቲና ሁሴን በበኩላቸው ጤናማ እና አምራች ህብረተሰብ ሳይገነባ የተሟላ ልማት ማምጣት እንደማይቻል ጠቁመው በጤናው ዘርፍ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎችን የምክር ቤቱ ማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ በቅርበት እየደገፈና እየተከታተለ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ጽ/ቤቱም ሆነ የጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ህብረተሰቡን በማንቃትና የመከላከል ስራዎችን በባለቤትነት በማጠናከር ወደ 2019 በጀት ዓመት ስራዎች መግባት ይኖርባቸዋልም ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ ሐጅ ሰመሩ አብደላ፣ የከተማ ምክር ቤት ማህበራዊ ዘርፍ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ስቲና ሁሴን፣ የጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈዲን ቱልሳ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤፎ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወር እቅድ አፈጻጸም የ2019 ዕቅድ ትውውቅና የሪፖርት ግምገማ መድረክ ተካሄደ!************(ነሐሴ ፣7/2...
13/08/2026

በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤፎ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወር እቅድ አፈጻጸም የ2019 ዕቅድ ትውውቅና የሪፖርት ግምገማ መድረክ ተካሄደ!
************
(ነሐሴ ፣7/2018 ዓ.ም)ጉባ አቶቲ ኡሎ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ የጤፎ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት የ12 ወር እቅድ አፈጻጸም የ2019 ዕቅድ ትውውቅና የሪፖርት ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የጤፎ ጤና ጣቢያ ሀላፊ የሆኑት አቶ አለባቸው ሲሳይ እንደገለጹት በጤናው ዘርፍ አመርቂ ውጤት የተመዘገበበት ዓመት መሆኑን ጠቅሰው፦ቀጣይነት እንዲኖረው በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባ ተናገረዋል።

አያይዘውም የጤና ባለሙያዎች ቅንጅት በጤና ጣቢያው ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አስችሏል ብለዋል።

የአፈጻጸም መድረኩን ምክንያት በማድረግ የክራምት በጎ ተግባር አካል የሆነውን የፍራፍሬ ችግኝ ተከላ መርሃግብር ተካሂዷል።

የ2018 በጀመት ዓመት ሪፖርትና ለ2019 ዕቅድ ለተዘጋጀው ሰነድን አቶ አለባቸው በዝርዝር አቅርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።

በመጨረሻም ለጤና ባለሙያዎች የእውቅና ሰርተፊኬት በመስጠት የዕለቱ መድረክ ተጠናቋል።

በመድረኩ ከወረዳው ጤና ጽ/ቤት የተወጣጡ ባለሙያዎች፣የጤፎ ጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ከአምስቱ ጤና ኬላዎች የተወጣጡ ጤና እክስትሽኖች ሌሎችም ባለድርሻ አካላቶች ተገኝተዋል።

የኡዳና ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ።ነሃሴ 07/2018 ዓ.ም | በሸኖበዌራ ዲጆ ወረዳ የኡዳና ጤና ጣቢያ የ2018 ...
13/08/2026

የኡዳና ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደ።

ነሃሴ 07/2018 ዓ.ም | በሸኖ

በዌራ ዲጆ ወረዳ የኡዳና ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ መድረክ አካሄደዋል።

የጤና ጣቢያ ሃላፊ አቶ ናደሞ ሱልጣን በበጀት ዓመት የተከናወናውን የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር አቅርበዋል።

በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ከመድረኩ ተሳታፊዎች በሚነሱ ሃሳቦች ዙሪያ የጤና ጽ/ቤት የተቋሙ ደጋፊዎች እና የጤና ጣቢያው ሃላፊ በጋራ አወያይተዋል።

በበጀት ዓመቱ የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ በተሰራው ስራ አበረታች ውጤት መመዝገቡ ተገልጸዋል።

የጤና ጣቢያው ሃላፊ አቶ ናደሞ ሱልጣን በበኩላቸው ቅንጅታዊ አሰራሮችን በማጠናከር ያለውን የሰው ሃይል አብቃቅቶ በመጠቀም በበጀት ዓመቱ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

በጤና ጣቢያው በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የጤና ባለሙያዎች እና የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በመጨረሻም በ2019 ዕቅድ ዝግጅትን በመገምገም ከየስራ ክፍሉ አስተባባሪዎችና ጤና ኤክስቴንሽኖች ጋር የግብ ስምምነት ተፈራርመዋል።

በመድረኩ ከጤና ጽ/ቤት የተቋም ደጋፊዎች ፣ የጤና ጣቢያ ማኔጀመንትና ባለሙያዎች ፣ የሁሉም ቀበሌ ጤና ኤክስቴንሽኖች ተገኝተዋል።

የእናቶችንና የህፃናትን ህመምና ሞት ለመቀነስ በተሰሩ የተቀናጁ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።ይህ የተገለጸው በዓለም የምግብ ፕሮግራም (WF...
13/08/2026

የእናቶችንና የህፃናትን ህመምና ሞት ለመቀነስ በተሰሩ የተቀናጁ ተግባራት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ይህ የተገለጸው በዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ድጋፍ እየተተገበረ ያለውን የተቀናጀ የምግብ እጥረት ሕክምናና የምግብ ድጋፍ ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም በቡታጅራ ከተማ በተገመገመበት መድረክ ነው።

የጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ጴጥሮስ እንደገለጹት፣የእናቶችና የህፃናት ጤናን ለማሻሻል በተሰራዉ ጠንካራ ስራ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡

የእናቶችንና ህጻናትን ሞት ለመቀነስ እንደ ክልል ትልቅ ግብ ተጥሎ እየተሰራ መሆኑን ያነሱት አቶ አሸናፊ ቀደም ሲል ከ100,000 እናቶች 267 እናቶች የሚሞቱ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ይህ ቁጥር ወደ 140 በ100,000 መቀነሱን ገልጸዋል። የህፃናትና የጨቅላ ህፃናት ሞትም በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱ ተገልጿል።

በተጨማሪም በተመረጡ ወረዳዎች ለነፍሰጡርና ለሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ለህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ድጋፍ ተደርጓል።

ይህን ተግባር ከማገዝ አንፃር የአለም የምግብ ፕሮግራም በርካታ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን ያነሱት አቶ አቨናፊ ህፃናት ፣ነብሰ ጡር እናቶች እንዲሁም የሚያጠቡ እናቶችን በምግብ እጥረት እንዳይጎዱ በተለይም በመካከለኛ የምግብ እጥረት የተጎዱ አካላትን የመደገፍ ስራዎች መሰራቱን ተናግረዋል ።

የልየታ ስራዉ ከሁለት ዓመት በታች ላሉ ህፃናት፣ አጥቢ እናቶችና ነብሰጡር እናቶች ለምግብ እጥረት ተጋላጭ እንዳይሆኑ 1780 እማ / አባወራ ድጋፍ እንዲያገኙ ተደርገዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ የእናቶች እና ህፃናት ጤናና ስርዓተ ምግብ አገ/ት ዳይሮክተሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፉዬ ሌጅሶ በበኩላቸው
እንደሀገር ብልም እንደክልል የተረጅነት አመለካከትን በመቅረፍ ራስን የመቻል አቅምን ለማጠናከር የወስጥ አቅማችንን በማሳደግ በትኩረት መስራት ይገባል።

በአጠቃላይ፣ የእናቶችና የህፃናት ህመምና ሞትን ለመቀነስ የተጀመሩ ተግባራት በቀጣይም በተቀናጀ አሰራር ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ተጠቁሟል።

የወይይቱ ተሳታፊዎች እንደተናገሩት ዘላቂ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለማቅረብ ቅንጅታዊ አሰራርን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አንስተዋል

በመድረኩ የዞን ጤና መምሪያ ሀላፊዎች ፣የወረዳ አስተዳዳሪዎችና ጤና ጽ/ቤት ሀለፊዎች፣የዞን የእናቶችና ህፃናት አስተባባሪዎችና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት የቦርድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።በዌራ ዲጆ ወረዳ የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ...
12/08/2026

የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት የቦርድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በዌራ ዲጆ ወረዳ የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት የቦርድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

ለውይይት መድረኩ የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት ሪፖርት በሆስፒታሉ ስራአስኪያጅ አቶ ሱሊመን ግርሚሶ አማካኝነት በሰፊው ተብራርቶ እየቀረበ ነው።

በመድረኩ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የሆስፒታሉ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሙህዲን ሁሴን፣የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አብዲ አደም፣የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ሸምሱ ረሺድን ጨምሮ የዞንና የወረዳ የቦርድ አባላት ተገኝተዋል።

በሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቦርድ ሰብሳቢ በሆኑት በአቶ ሙህዲን ሁሴን የተመራ ቡድን በሆስፒታሉ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጥ፣የችግኝ ተከላና የግብርና ስራ...
12/08/2026

በሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቦርድ ሰብሳቢ በሆኑት በአቶ ሙህዲን ሁሴን የተመራ ቡድን በሆስፒታሉ ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጥ፣የችግኝ ተከላና የግብርና ስራዎች ምልከታ አደረጉ።

በዌራ ዲጆ ወረዳ በበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ በሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪና በሆስፒታሉ ቦርድ ሰብሳቢ በሆኑት በአቶ ሙህዲን ሁሴን የተመራ ቡድን በግቢው ውስጥ የአገልግሎት አሰጣጥ፣የችግኝ ተከላና የግብርና ስራዎች ምልከታ አድርጓል።

በምልከታው መርሃግብር ላይ የሆስፒታሉን አጠቃላይ አገልግሎት አሰጣጥ፣የግብርና ስራዎችን እንድሁም የፓፓያ ችግኝ ተከላ መርሃግብር ተከናውኗል።

የመርሃ-ግብሩ ዋና አላማው የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ አመት የቦርድ ውይይት ለማድረግ እንደሆነ ተገልጿል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ ሰብሳቢ በአቶ ሙህዲን ሁሴን፣የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የደቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አብዲ አደም፣የወረዳው የመንገድ ዋና ተጠሪ አቶ ሱራጅ ጎድሶ፣የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ሸምሱ ረሺድ፣የበሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራአስኪያጅ አቶ ሱሊመን ግርሚሶን ጨምሮ ሌሎች የወረዳ አስተባባሪዎችና፣ከዞን ከወረዳ የተወጣጡ የቦርድ አመራሮችና አባላት ተገኝተዋል።

Address

Halaba
Alaba K'ulito

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaba Zone Health Department - የሀላባ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share