03/09/2026
የዞኑ ትምህርት መምሪያ በዞኑ በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመገኘት የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን የምዝገባ ሂደት ክትትል እያደረገ ነው
=========
ነሐሴ፣28/2018 የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ በዞኑ በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች በመገኘት የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎችን የምዝገባ የእስከአሁን ያለውን አፈጻጸም ክትትል አደረገ እያደረገ ይገኛል።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ በወረዳው ያለውን የምዝገባ አፈጻጸም ሂደትን በተመለከተ ከወረዳው አስተባባሪ አመራሮች ጋር ወይይት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በክትትሉ የሀላባ ዞን የዋና አስተዳዳሪ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ አቶ ሁሴን ሮባና የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ እንዲሁም የወረዳው የትምህርት ጽ/ቤት አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ