16/08/2026
ከነገ ሰኞ ነሐሴ 11 ጀምሮ በዞኑ በሁሉም ት/ቤቶች የ2019 የተማሪዎች ምዝገባ በኦንላይን እንደሚጀምር ተገለፀ።
የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባን በማስመልከት መግለጫ ሰጥቷል።
መግለጫውን የሰጡት የሀላባ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ዘለቀ ከነገው ሰኞ ጀምሮ በቅድመ-አንደኛና በመደበኛ በሁሉም የትምህርት እርከን የተማሪዎች የ2019 የትምህርት ምዝገባ እንደሚጀመር ገልፀዋል።
በመሆኑም ሁሉም ባለድርሻ አካላት የምዝገባ አፈጻጸሙ በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ በቅንጅት እንዲሰሩ ያሳሰቡ ሲሆን የተማሪ ወላጆችም በቅድመ አንደኛም ሆና በመደበኛ ትምህርት ልጆቻቸው ፈጥነው እንዲያስመዘግቡ አሳስበዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ የተጀመሩ የክረምት በጎ ስራዎች፣ የት/ቤቶች ዕድሳትና ጥገና፣ የት/ቤቶችን ውስጥ ገቢ በማሳደግ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተጀመሩ ኢንሼቲቮችና የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጨምረው አሳስበዋል።
ከተለያዩ ምንጮች በሚገኘው ሀብትም የት/ቤቶችን ግብዓትን በማሟላት የት/ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል ት/ቤቶች ለተማሪዎች ሳቢና ማራኪ እንዲሆኑ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የተማሪዎች ምዝገባ ሂደቱ ከተያዘለት ጊዜ ቀደም ብሎ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላትና የትምህርት አመራሩ በቅንጅት እንዲሰሩ አሳስበዉ በዞኑ በ2019 በአጠቃላይ 123,367 ተማሪዎችን ለመመዝገብ መታቀዱን ጨምረው ገልፃዋል።
ነሐሴ 10/2018 ሀላባ ቲቪ