Gubagala

Gubagala Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gubagala, Landmark & historical place, gubagala, Alamat'a.

16/09/2019

እንኳን አደረሳችሁ ጉቤዎች

15/05/2019

3ኛ. የአዳም የውርስ ኀጢአት ያልደረሰባት መሆኑን (ጥንተ አብሶ የሌለባት መሆኑን)

እመቤታችን ድንግል ማርያም በአዳምና በዘሩ የነበረው የውርስ ኀጢአት ያልደረሰባት ናት። አዳም በፈጸመው ስህተት የእርሱ ልጆች በሙሉ መከራ በበዛበት በዚህ ዓለም ለመኖር ተገደዋል። የነበረው የውርስ ኀጢአት ሸክም ከባድ ስለነበር የሰው ልጆች ሕይወት በድቅድቅ ጨለማ የመኖር ያህል ነበር ። ለዚህም ነው ጌታችን ሲወለድ በድቅድቅ ጨለማ የሚኖር ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ የተባለው ፡ የነበረውን ሕይወት ከባድነት ለመግለጽ ነው ( ኢሳ 9፡2 )። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን የተወለደው ፡ በመስቀል ላይ የተሰቀለው ይህንን የእዳ ደብዳቤ ሊቀድልንና ዘላለማዊ ክብር የምናገኝበትን ሕይወት ሊሰጠን ነው ። የጌታችን መምጣት አዳምንና ዘሩን ከዚህ የውርስ ኀጢአት ነጻ የሚያደርግ ስለሆነ የዓለም መድኃኒት ተብሏል።መጥምቁ ዮሐንስም ሲመሰክር የዓለሙን ሁሉ ኀጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ያለው ከዚህ በመነሳት ነው (ዮሐ 1፡29 )። ይህ የተነገረው የውርስ ኀጢአት ግን በእመቤታችን አልነበረም ፤አልደረሰምም ። አንዳንድ ሰዎች ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም የሚለውን ቃል በመዘንጋት ድንግል ማርያም የአዳም የውርስ ኀጢአት አለባት ለማለት ሲሞክሩ እንሰማቸዋለን ። ይህ ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የማትቀበለው መጻሕፍትን ያላገናዘበ በጥርጣሬ ማእበል ከተጎዳ ህሊና (ልቦና) የሚወጣ ደካማ አስተሳሰብ ነው። በዚህ ቦታ ብዙ ዝርዝር ትንታኔ ለመስጠት ባንችልም ለምስክርነት ያህል ግን እመቤታችን ጥንተ አብሶ ( የውርስ ኀጢአት) እንደሌለባት ሁለት ቦታዎችን በቀላሉ እንመለከታለን ።

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችንን ሲያበስራት የተናገረው ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ ብሎ ነው የተናገራት ( ሉቃ 1፡28) መቼም የውርስ ኀጢአት ነበረባት ከተባለች ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ልትባል አትችልም ምክንያቱም የውርስ ኀጢአት ካለ ከጸጋ በታች ያደርጋልና ። አንዳንዶች እንደሚናገሩት ደግሞ ወልድ በማህፀኗ ሲያድር አነጻት ቀደሳት እንዳንል የመልአኩ ምስክርነት ጌታን ከመፅነሷ በፊት ነው ። ቅዱስ ገብርኤል ይህንን ለእመቤታችን የነገራት ሦስት ጊዜ በተለያየ ቦታና ወቅት ነው ።እመቤታችን በመልአኩ የቀረበላትን ቃል ተቀብላ እንደቃልህ ይሁንልኝ ከማለቷ በፊት ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ማለቱ ከውርስ ኀጢአት ነጻ እንደነበረች የተነገረ ምድራዊ ሳይሆን ሰማያዊ ምስክርነት ነው ። በተጨማሪም ነብዩ ኢሳይያስ አስቀድሞ የተናገረው ምስክርነት ይህንን እውነታ የበለጠ የሚያረጋግጥ ነው። “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር” ኢሳ 1፡9 እዚህ ላይ ዘርን ባያስቀርልን የተባለችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በመሆኗ ከሌሎች የአዳም ዘር ሁሉ የሚለያት ነገር እንዳለ ፤ በእነርሱ የደረሰ በዚህች ዘር ላይ ግን ያልደረሰ ነገር መኖሩን የሚያስረዳ ነው ። ይህም የአዳምን ዘርን በሙሉ የሚመለከተው ኀጢአት ጌታችን በሞቱ ባያጠፋልን ኖሮ ለዘላለማዊ ቅጣት ያበቃን ነበር። ከዚህ በመነሳት ነው እመቤታችን ከአዳም ዘር የተገኘች ብትሆንም አስቀድማ በአምላክ ህሊና ታስባ ትኖር ነበር በማለት ሊቃውንት የሚገልጹት።

22/01/2017

በሩቅ መፍራት ተገቢ አይደለም፡፡ቀረብቀረብ በሉ እና እንወያይ ካልተወያዩ ችግር አይፈታም፡፡

14/08/2016

ውድ የጉባጋላ ልጆች እንደምን አላችሁ እንዴትስ ሰነበታችሁ?

01/05/2016

እንኳን ለበዓለ ትንሳዔው በሰላም አደረሳችሁ፡፡

ይህን የመሰለ ቦታ አድገን ይህን የመሰለ ተፋ አለን
27/04/2016

ይህን የመሰለ ቦታ አድገን ይህን የመሰለ ተፋ አለን

24/04/2016

ሕብረት ኃይል ነው፡፡ ተባብረን እንስራ እና እንለወጥ
ሀሳባችሁን አካፍሉ

Address

Gubagala
Alamat'a
02

Telephone

0913650178

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gubagala posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share