በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication

  • Home
  • Ethiopia
  • Aleta
  • በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication

በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication እውነተኛና ተአማኒ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ለማቅረብ እንተጋለን።
(1)

‎ለውጤታማ የመማር ማስተማር ሥራ ትምህርት ቤቶችን ዝግጁ ከማድረግ ጀምሮ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማብቃትም ከወዲሁ ልሰራ እንደሚገባ ጥሪ አቀረቡ፦ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር‎‎ነሐሴ 11/...
17/08/2026

‎ለውጤታማ የመማር ማስተማር ሥራ ትምህርት ቤቶችን ዝግጁ ከማድረግ ጀምሮ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማብቃትም ከወዲሁ ልሰራ እንደሚገባ ጥሪ አቀረቡ፦ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር

‎ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎በላስካ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ካሉ ርዕሰ መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች እንዲሁም ከትምህርት አመራሮች ጋር የ2019 የትምህርት ዘመንን ውጤታማ ማድረግ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር ለውጤታማ የመማር ምስተማር ሥራ ትምህርት ቤቶችን ዝግጁ ከማድረግ ጀምሮ ብቁና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማብቃትም መምህራን፣ የተማሪ ወላጆች፣ ተማሪዎች እና የትምህርት አመራሮች ከወዲሁ በቅንጅት ልሰሩ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

‎ምቹ የትምህርት ከባቢን ከመፍጠር እና በትምህርት ቤቶች የትምህርት ቁሳቁሶችን ከማሟላት ረገድ የህብረተሰብ ተሣትፎ በእጅጉ እንደሚያስፈልግ ያመላከቱት ከንቲባው ለውጤታማነቱም በጋራ ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

‎አክለውም የተማሪዎችን ውጤት በማሻሻል ሂደት የአንበሳውን ድርሻ የሚወጡት መምህራን ከዕቅድ ዝግጅት ጀምሮ በቂ ዝግጅት ማድረግና የማጠናከሪያ ትምህርቶችንም በመስጠት የነገዋ ሀገር ተረካቢ ዜጋን የመቅረጽ ኃላፊነታቸውን በተገቢው እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።

‎ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚቀላቀሉ ተማሪዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተመናመነ መምጣቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ያወሱት ከንቲባው በዘንድሮው የትምህርት ዓመት የሚመዘገበውን ውጤት በማላቅ የተማሪዎችን መጻዕ ዕድሎቻቸውንም ብሩህ ማድረግ እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ትምርት ቤቶች ዩኒት አስተባባሪ አቶ አንተነህ አጥናፉ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ ጀምሮ የመጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ፣ የልዩ ፍላጎት እንዲሁም ተግባር ተኮር የጎልማሳዎች ትምህርት ብሎም በአማራጭ መሠረተ ትምህርት በመደበኛ እና መደበኛ ባልሆኑ የሚማሩ ተማሪዎችን ለመቀበልና ምዝገባ አካሂዶ ወደ መማር ማስተማር ሥራ ለመሰማራት ትምህርት ቤቶች ከወዲሁ እንዲዘጋጁም ጥሪ አቅርበዋል።

‎በትምህርት ቤቶች እየተስተዋለ የሚገኘውን መጠነ ማቋረጥን ለማስቀረት አስመላሽ ኮሚቴዎችን በየትምህርት ቤቶች ከማደራጀት በዘለል ወደሥራ ማስገባት እንደሚጠበቅ ያወሱት አቶ አንተነህ የመጠነ መድገምን ቁጥር ዝቅ ለማድረግም በየትምህርት ክፍሉ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የግብ ስምምነቶችን መልሶ ማጤን እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

‎በ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ስራው ከመስከረም 05/2019 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ እንደሚጀምር ያስታወቁት የዩኒት አስተባባሪው የምዝገባ ሂደቱም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ከነሃሴ 13/2018 ዓ.ም ጀምሮ አስከ ጳጉሜ 05/2018 ዓ.ም እንደሚካሄድ ታውቆ ተማሪዎች በጊዜ እንዲመዘገቡም ጥሪ አቅርበዋል።

‎የውይይት መድረኩ ተሣታፊዎችም በዘንድሮው የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ከማሻሻል ጀምሮ የተማሪዎችን ውጤት ለማላቅም አስቀድሞ ውይይት መካሄዱ በተማሪዎች ውጤት መሻሻል ላይ ማነቆ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቀን ሳለ ለመረባረብ ምቹ ምህዳር የሚፈጥር መሆኑን አስታውቀዋል።


‎ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም
‎ ላስካ

በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር በላስካ 02 ቀበሌ ዛባ ሰፈር የንቃቴ ህግ ግንዛቤ መፍጠሪያ ከተማ አቀፍ የስልጠና ማስጀምሪያ መድረክ ተካሄደ።‎‎ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬ...
17/08/2026

በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር በላስካ 02 ቀበሌ ዛባ ሰፈር የንቃቴ ህግ ግንዛቤ መፍጠሪያ ከተማ አቀፍ የስልጠና ማስጀምሪያ መድረክ ተካሄደ።

‎ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር በላስካ 02 ቀበሌ ዛባ ሰፈር የንቃቴ ህግ ግንዛቤ መፍጠሪያ ከተማ አቀፍ የስልጠና ማስጀምሪያ መድረክ ተካሂዷል።

‎የባስኬቶ ዞን ምክር ቤት ዋና አፌጉባኤ የተከበሩ አቶ ማርቆስ ልፋቱ በአዕምሮ፣በስነ-ምግባር እና በኢኮኖሚ የተሻለ አካባቢን ለመፍጠር ዜጎች ህግን በአግባቡ መረዳት አስፈላጊ እንደሆነ በመልዕክታቸው ተናግረዋል።

‎መንግስት በህገመንግስቱ የደነገገውን የሕዝብ መሠረታዊ ፍላጎት እውን ለማድረግ ዜጎች ከሙስና እና ከብልሹ አሰራሮች የፀዱ መሆን እንዳለባቸው የተናገሩት የዞኑ አፌጉባኤው ለዚህም የዛሬው የንቃቴ ህግ ስልጠና መሰጠት ሚናው ጉልህ መሆኑን አብራርተዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳዳር ዋና ከንቲባ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር ህግን በመረዳት ከአላስፈላጊ ጥሰት ራስን በመጠበቅ የተሰጠንን ውድ ጊዜን በህብረተሰብ ተሳትፎ ልማት ላይ ማትኮር አለብን ብለዋል።

‎ዜጎች ህግን ባለማወቅና ባለማክበር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ኪሳራ ውስጥ እንደሚገቡ የገለፁት የላስካ ከተማ ከንቲባው የሚሰጠውን ስልጠና በተገቢው በመከታተል ለነጌያቸው ስንቅ መቋጠር እንደሚገባቸውም ተናግረዋል።

‎ህግ የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል መብት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን በተገቢው እየተወጣ መሆኑን የገለፁት የላስካ ከተማ አስተዳደር የፍትህ እና ጸጥታ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሙሴ ጉጆ ማህበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም በማስፈን ረገድ ያላቸውን አስተዋጽኦ በጉልህ ማበርከት አለባቸው ሲሉ ተደምጠዋል።

‎አክለውም ስለጤናው ለተከታታይ 5 ቀናት ከነሔሰ 11_15/2018 ዓ.ም የሚቆይ መሆኑም ጠቁመው ሰልጣኞች በንቃት እንዲከታተሉም ጥሪ አቅርበዋል።


‎ ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም
‎ ላስካ

‎የላስካ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርቲያን የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት ግንባታን አስጀመረች።‎‎ላስካ: ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)‎‎"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል ...
17/08/2026

‎የላስካ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርቲያን የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት ግንባታን አስጀመረች።

‎ላስካ: ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በተጀመረው የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል በሆነው የአረጋዊያንና አቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ መርሃግብር የላስካ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርቲያን የአንዲት አቅመ ደካማ እናት ቤት ግንባታን አስጀምራለች።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጳውሎስ ኃይሌ በጎነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተና በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ዘንድ ባህል እየሆነ ከመምጣቱም ባሻገር ማህበራዊ መስተጋብሮችን በማጠናከር የህብረተሰቡን የእርስ በርስ ግንኙነት ለማሻሻልም አበርክቶው ጉልህ እንደሆነ ገልጸዋል።

‎ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ማድረግ ከብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር እሳቤዎች መካከል አንዱ መሆኑን ያወሱት አቶ ጳውሎስ የተቸገሩ ወገኞችን መደገፍ የመንፈስ እርካታን የሚያጎናጽፍና ከተግባሮች ሁሉ የላቀ ዋጋ ያለው በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

‎አቶ ጳውሎስ ይህንን በጎ ተግባር በመከወን ላይ የሚትገኘውን የላስካ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርቲያንን አመስግነው ስራውን በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅና ሌሎችንም ለማስጀመር መረባረብ እንደሚያስፈልግ ጥሪ አቅርበዋል።

‎በጎ ፈቃደኝነት ያለምንም አስገዳጅነትና በራስ ተነሳሽነት ለሌሎች የመኖር ዕሴት በመሆኑ ጊዜን፣ ጉልበትን፣ እውቀትንና ገንዘብን ለህብረተሰቡ ችግር ፈችነት ማዋል አስፈላጊ መሆኑን የላስካ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የማዘጋጃ ቤት ሥራአስኪያጅ አቶ ለማ መንገሻ ገልጸዋል።

‎የላስካ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ሰብሳቢ አቶ ተፈራ ኃይሉ የበጎነት አገልግሎት እየሱስ ክርስቶስ በምድር ሳለ ካስተማራቸውው ትምህርቶች ትልቁን ስፍራ የሚይዝ መሆኑን አመላክተው ቤተክርስቲያኒቱም የሌሎችን እገዛ ለሚሹ ወገኖች ለመድረስ በሁሉም ዘርፍ እየተንቀሳቀሰች እንደምትገኝ አስታውቀዋል።

‎አክለውም በዛሬው ዕለት ያስጀመሩትን የቤት ግንባታ መላው የቤተክርስቲያንቱን ምዕመን በማስተባበር በተያዘለት ጊዜ አጠናቅቀው ለማስጠለል ተግተው እንደሚሰሩ ገልጸው የክረምቱ ወራት እስኪጠናቀቅ ድረስ የበጎ ሥራን በተመረጡ ዘርፎች አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ አስታውቀዋል።

‎በቤተክርስቲያኒቱ የቤት ግንባታው የተጀመረላቸው በላስካ 01 ቀበሌ የግብይት ሞቲኬሳ ሠፈር ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ዘነበች መርሻ ለተደረገላቸው በጎነት አመስግነው የቤቱ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በተለይም በክረምት ወራት ከሚደርስባቸው እንግልት የምታደጋቸው መሆኑንም ገልጸዋል።


‎ ነሃሴ 11/2018 ዓ.ም
‎ ላስካ

‎የቱሪስት መዳረሻዎችን ማልማት እና ጠብቆ ማቆየት አካባቢያችንን ከማስተዋወቅ ረገድ ሚናው የጎላ እንደሆነ ገለጹ:- ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር‎‎ላስካ: ነሃሴ 10/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒ...
16/08/2026

‎የቱሪስት መዳረሻዎችን ማልማት እና ጠብቆ ማቆየት አካባቢያችንን ከማስተዋወቅ ረገድ ሚናው የጎላ እንደሆነ ገለጹ:- ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር

‎ላስካ: ነሃሴ 10/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎በሰው ለሰው ግብረሰናይ ድርጅት የሚለማውን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራን ከግለሰቦች ይገባኛል ነጻ በማድረግ ለመዳረሻነት እንዲውል ለማስቻል ከባለይዞታ አርሶአደሮች ጋር ውይይት ተካሂዷል።

‎የቱሪስት መዳረሻዎችን ማልማት እና ጠብቆ ማቆየት አካባቢያችንን ከማስተዋወቅ ረገድ ሚናው የጎላ እንደሆነ የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር ገልጸዋል።

‎በአካባቢያችን የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን አልምቶ የሀብት ምንጭ እንዲሆኑ ለማስቻልም ሆነ በሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የመጣውን ግብረሰናይ ድርጅት መደገፍና አብሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ከንቲባው አስታውቀዋል።

‎በስፍራው ለበርካታ ዓመታት በህጋዊ መንገድ መሬት ይዘው እያለሙ ለሚገኙ አርሶአደሮች ምትክ የእርሻ መሬት ማዘጋጀታቸውን ያወሱት ኢንጂነር በኃይሉ የልማት ተነሺዎችን በዘላቂነት ማቋቋም ጊዜ የማይሰጠው መሆኑንም አስገንዝበዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጳውሎስ ኃይሌ በመንግስት አቅም ተደራሽ ማድረግ ያልተቻሉትን የተለያዩ አልሚ ባለሀብቶችን እና ድርጅቶችን በመጋበዝ እንዲያለሙ ማስቻል የከተማችንን እድገት እንደሚያፋጥን አስታውቀዋል።

‎የሲርሶ እና ቤርሶ መንቲያ ፏፏቴዎች በከተማችን መገኘት መዳረሻ ሆኖ የቱሪዝም ዘርፉን እንደሚያግዝ ያመላከቱት አቶ ጳውሎስ ኃይሌ የተካለለው መሬት በደን ስሸፈን ከካርበን ሽያጭ ገቢ የሚያስገኝና የከተማችንን ገጽታ በእጅጉ የሚያጎላ በመሆኑ ለተግባራዊነቱም በጋራ መረባረብ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

‎የይዞታ ባለቤት በሆኑ አርሶአደሮች ዘንድ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ እንዳይፈጠርና በያዙት መሬት ልክ የሚያለሙበትን የእርሻ መሬት በመስጠት ድርጅቱ ለሚያለማው የደን ልማት የተካለለውን ይዞታ ማስረከብና እንዲያለሙ የማስቻል ሥራም ከዛሬ ቀጥሎ እንደሚሠራ አቶ ጳውሎስ አስታውቀዋል።

‎የልማት ተነሺ አርሶአደሮችም በበኩላቸው የአካባቢው ልማት የጋራ በመሆኑ ልያለማ የመጣው ግብረሰናይ ድርጅት ችግኝ ከማፍላት ጀምሮ ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል እየፈጠረ ያለና በማህበራዊ አገልግሎቶችም የያዛቸውን ውጥኖች መሬት ላይ ለማውረድ በዝግጅት ላይ ያለ መሆኑን ገልጸዋል።

‎አክለውም ለልማት የተፈለገውን ይዞታ ለማካለል መንግስት ኮሚቴ አዋቅሮና እስከ ቦታው ድረስ ወርዶ ልየታ በማድረግ ወደሥራ ለመግባት ማወያየት በመቻሉ መደሰታቸውን ጠቁመው የመሬት አዋጅ በሚፈቅደው መሠረት ለመዳኘት ብሎም ከድርጅቱ ጋር በጋራ ለማልማት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

‎ ላስካ ኮሙኒኬሽን
‎ ነሃሴ 10/2018 ዓ.ም
‎ ላስካ

‎በተያዘው ዓመት 4 መቶ ሄክታር መሬት በደን ለመሸፈን ታቅዶ በሰው ለሰው ግብረሰናይ ድርጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ተገለጸ፦ አቶ ተመስገን አዘነ‎‎ላስካ: ነሃሴ 09/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮ...
15/08/2026

‎በተያዘው ዓመት 4 መቶ ሄክታር መሬት በደን ለመሸፈን ታቅዶ በሰው ለሰው ግብረሰናይ ድርጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ተገለጸ፦ አቶ ተመስገን አዘነ

‎ላስካ: ነሃሴ 09/2018 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎በባስኬቶ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ በአቶ ተመስገን አዘነ የተመራው በዞን ደረጃ የተደራጀ ኮሚቴ ልዑክ በሰው ለሰው ፕሮጀክት የሚለማውን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራን ከግለሰቦች ይገባናል ነጻ በማድረግ ለመዳረሻነት እንዲውል ለማስቻል ከስፍራው ተገኝተው ምልከታ አካሂደዋል።

‎በመዳረሻው ለሚለማው የደን ልማት የሚውለው መሬት ለደን ልማት በመያዙ እና ለእርሻ ሥራ ምቹ ካለመሆኑም ባሻገር የስርሶ እና ቤርሶ መንቲያ ፏፏቴዎች የሚገኙበት ውብ ተፈጥሯዊ የቱሪስት መዳረሻ በመሆኑ አልምቶ ለትውልድ ለማስተላለፍ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አቶ ተመስገን ገልጸዋል።

‎ከ5 መቶ ሚሊዮን በጀት በላይ ፈሰስ በማድረግ በደን ልማት ሥራ ብሎም በትምህርት እና በጤና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ለማሳደግ የሚሰራው የሰው ለሰው ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በተያዘው ዓመትም 4 መቶ ሄክታር መሬትን በደን ለመሸፈን እየሰራ እንደሚገኝም አቶ ተመስገን አስታውቀዋል።

‎አያይዘውም ሞዴል ትምህርት ቤት ግንባታን በላስካ ከተማ አስተዳደር ወርዥመይሳ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በቅርቡ ለማስጀመር የሳይት ርክክብ እንደሚያደርጉ እና በላስካ ጤና ጣቢያም ጥገና እንደሚያካሂዱ ኃላፊው ገልጸዋል።

‎ደኑን በማልማት የአየር ንብረት ለውጥን ሚዛን ከመጠበቅ ባሻገር ለካርበን ሽያጭ ለማዋል እየተሰራ እንደሚገኝ ያመላከቱት አቶ ተመስገን ዛሬ ላይ ለሚተከለው ችግኝ መሬቱን ነጻ በማድረግና ለግብረሰናይ ድርጅቱ ለማስተላለፍ በስፍራው በእርሻ ሥራ ለሚተዳደሩ አርሶ አደሮችም ተለዋጭ መሬት ቀድሞ መዘጋጀቱንም አስገንዝበዋል።

‎አክለውም በደን የሚሸፈነውን መሬት ከግለሰቦች አላቅቆ ድርጅቱ እንዲያለማ ከማስቻል በዘለል የተተከሉ ችግኞችንም ተንከባክቦ እንዲያድጉ ከመከታተል ረከድ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ በጋራ መረባረብ እንሚያስፈልግም ገልጸዋል።


‎ ነሃሴ 09/2018 ዓ.ም
‎ ላስካ

‎የህዝቡን አዳጊ ፍላጎቶችን በትክክል በማጠንም ሆነ ቅደም ተከተል በማስያዝና ምላሽ በመስጠት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ገለጹ፦ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር‎‎ላ...
15/08/2026

‎የህዝቡን አዳጊ ፍላጎቶችን በትክክል በማጠንም ሆነ ቅደም ተከተል በማስያዝና ምላሽ በመስጠት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ገለጹ፦ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር

‎ላስካ: ነሃሴ 09/2018 ዓ/ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ጠቅላላ አመራሮች ወቅታዊ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈጻጸምን በመገምገም በቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በጋራ መክረዋል።

‎የህዝቡን አዳጊ ፍላጎቶችን በትክክል በማጠንም ሆነ ቅደም ተከተል በማስያዝና ምላሽ በመስጠት የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ዕውን ለማድረግ መዘጋጀታቸውን የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር አስታውቀዋል።

‎አክለውም የማትፈርስ ከተማን በመገንባት ሂደት የተጀመሩና ህብረተሰቡን በማስተባበር የሚሰሩ የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው የገቢ አማራጮችን ሁሉ በመጠቀምና ገቢን አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ጥያቄዎችን መመለስና ተደራሽነታቸውንም ማስፋት ቀዳሚው ተግባር ተደርጎ እንደሚመራ ከንቲባው አመላክተዋል።

‎በህብረተሰቡ ተሣትፎና በመንግስት የተጀመሩትንና በአዲስ የሚጀመሩ የልማት ሥራዎችን በአጭር ጊዜ አጠናቆ ህብረተሰቡን የልማቱ ተጠቃሚ በማድረግ የከተማዋን ደረጃ ለማሻሻል የተሰጠውን ትኩረት ቀጣይነት ባለው መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ማህበረሰብ ድጋፍና አስተዋፅኦ አበርክቶው ከፍ ያለ እንደሆነም ኢንጂነር በኃይሉ ገልጸዋል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጳውሎስ ኃይሌ ‎ማህበራዊ ብልጽግናን በማረጋገጥ ሂደት ፍትሃዊና ቀጣይነት ያለዉ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ሽፋን ለመስጠት በትኩረት መሰራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

‎በመድረኩ ትኩረት ካገኙት መካከል ''ፋይዳ'' ዲጂታል መታወቂያና የ''ኢትዮ ኮደርስ'' ኢንሼቲቭ ሌላኛው የአመራር የውይይት አጀንዳ ሲሆኑ አሁናዊ ደረጃቸውን በማሻሻል በተቋምም ሆነ በቀበሌያት ሀገራዊ ግቡን በማሳካት ሂደት የተጀመረውን ሥራ ዕውን ለማድረግ ከወትሮው በተለየ በኃላፊነት መፈጸም እንዳለበት አቶ ጳውሎስ አመላክተዋል።

‎አክለውም አቶ ጳውሎስ የፓርቲም ሆነ መንግስታዊ አደረጃጀቶችን በማጠናከር የሚወርዱ ተልዕኮዎችን በብቃት ለመፈጸም በሚደረገው ጥረት የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ፈር ቀዳጅ በመሆን ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መልኩ በግምባር ቀደምትነት ተግባራትን ልመሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎የመድረኩ ተሣታፊ የሆኑ የላስካ ከተማ አስተዳደር ጠቅላላ አመራሮችም በተግባር አፈጻጸም የሚስተዋሉ ውስንነቶችን በማረም የፓርቲንም ሆነ መንግስታዊ ተግባራትን በብቃት በመፈጸም የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

‎መድረኩን የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር እና የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጳውሎስ ኃይሌ በጋራ ሲመሩ የከተማ አስተዳደሩ አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ የካቢኔ አባላት እና የዩኒት አስተባባሪዎችም ተሣታፊ ሆነዋል።


‎ ነሃሴ 09/2018 ዓ/ም
‎ ላስካ

አረጋዊያንን እና አቅሜ ደካሞችን ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ጋር የማስተሳሰር ሥራ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ይገኛል።ላስካ: ነሀሴ 08/2019 ዓ.ም (ላስካ ...
14/08/2026

አረጋዊያንን እና አቅሜ ደካሞችን ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ጋር የማስተሳሰር ሥራ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ይገኛል።

ላስካ: ነሀሴ 08/2019 ዓ.ም (ላስካ ኮሙኒኬሽን)
አረጋዊያንን እና አቅሜ ደካሞችን ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ጋር የማስተሳሰር ሥራ በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ይገኛል።

የባስኬቶ ዞን አስተዳዳሪ ኢንጂነር በዛብህ ገበየሁ በመካሄድ ላይ የሚገኘውን አረጋዊያንን እና አቅሜ ደካሞችን ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ጋር የማስተሳሰር ሥራን በላስካ ከተማ አስተዳደር ተገኝተው ምልከታ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ለአገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገትና የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት እንቅስቃሴን ከማቅለል ረገድ የጎላ ሚና እንደሚጫወት የባስኬቶ ዞን አስተዳዳሪ ኢንጂነር በዛብህ ገበየሁ አስታውቀዋል።

አክለውም የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ የኢትዮጵያን ዲጂታል ሽግግር የሚያፋጥን አዲስ ምዕራፍ ከመሆኑም ባሻገር የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመረው ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ንቅናቄ በአገሪቱ የዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝም አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል።

በመካሄድ ላይ የሚገኘው ሥራ በሁሉም ማህበራዊ መሠረት በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው ጥሪ ያቀረቡት ኢንጂነር በዛብህ ''ፋይዳ'' ሰብዓዊ ድጋፍ ልደረግላቸው ለሚገባቸው ልየታ ለተደረጉ አረጋዊያን እና አቅሜ ደካሞች በቀጥታ እንዲደርሳቸው ለማስቻልም እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

የመንግሥት አገልግሎቶችን ውጤታማ ከማድረግ ረገድ ብሔራዊ መታወቂያ መንግሥት ስለ ሕዝቡ ፍላጎትና ስብጥር ትክክለኛ መረጃ እንዲኖረው የሚያስችል መሆኑን የጠቆሙት የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊና የመንስት ዋና ተጠሪ አቶ ጳውሎስ ኃይሌ መንግስት የማኅበራዊ ልማት ዘርፎች ላይ ውጤታማ ሥራ ለመስራትና ትክክለኛ ዕቅድ ለማውጣት አጋዥ መሆኑንም አስታውቀዋል።

አክለውም "ፋይዳ" ዲጂታል ኢትዮጵያን በ2025 ዕውን ለማድረግ የተጣለ ትልቅ ሀገራዊ መሠረት በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ ይህንን ዲጂታል መታወቂያ በማውጣት በፈጣንና ዘመናዊ መልክ የሚቀርቡ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን አቀላጥፈው እንዲገለገሉበትም አቶ ጳውሎስ ጥሪ አቅርበዋል።


ነሀሴ 08/2019 ዓ.ም
ላስካ

በላስካ ከተማ አስተዳደር የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።‎‎ነሐሴ 08/2018 ዓ/ም(ላስካ ኮሙኒኬሽን)‎‎በላስካ ከተማ አስተዳደር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ...
14/08/2026

በላስካ ከተማ አስተዳደር የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎ነሐሴ 08/2018 ዓ/ም(ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎በላስካ ከተማ አስተዳደር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የተለያዩ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነው የአቅሜ ደካማ ቤት ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር በኃይሉ አጎናፍር በክረምት ወቅት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የአቅመ ደካሞችን እንግልት የሚቀንሱና የህብረተሰቡን ማህበራዊ ችግሮች የሚያቃልሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

‎በከተማ አስተዳደሩ የተጀመረው ይህ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል ።

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጳውሎስ ኃይለ በጎ ፈቃደኝነት የህዝብን ችግር በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

‎የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑት አቶ ማሃ መንገሻ አቅመ ደካማ በመሆናቸው ለተደረገላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

‎በበጎ ተግባሩ ላይ የከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አካትን ጨምሮ የክላስተር አስተባባሪ የቀበሌው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል ።

‎ ነሐሴ 08/2018 ዓ/ም
‎ ላስካ

14/08/2026

የላስካ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 7ኛ ዙር 6ኛ የሥራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል።

ምክር ቤቱ ልዩ ልዩ የሥራ ሪፖርቶች፣ የዋና ከንቲባን ጨምሮ ሌሎችንም ሹመቶች መርምሮ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

በላስካ ከተማ አስተዳደር አዲስ የተሾሙ አመራሮች ከቀድሞ አመራሮች የሥራ ርክክብ አደረጉ ።‎‎ነሐሴ 07/2018 (ላስካ ኮሙኒኬሽን)‎‎የላስካ ከተማ አስተዳደር አፌ ጉባኤን ጨምሮ ጠቅላላ አስ...
13/08/2026

በላስካ ከተማ አስተዳደር አዲስ የተሾሙ አመራሮች ከቀድሞ አመራሮች የሥራ ርክክብ አደረጉ ።

‎ነሐሴ 07/2018 (ላስካ ኮሙኒኬሽን)

‎የላስካ ከተማ አስተዳደር አፌ ጉባኤን ጨምሮ ጠቅላላ አስተባባሪው ከቀድሞው የከተማ አስተዳደሩ አስተባባሪ ጋር ይፋዊ የሥራ ርክክብ አድርገዋል።

‎በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ወቅት አዲሶቹ አመራሮች የተጣለባቸውን የህዝብ ኃላፊነት በታማኝነትና በትጋት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን የቀድሞው አመራር ለአካባቢው እድገት ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

‎ጠንካራ አሰራሮችን በማስቀጠል በከተማዋ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል መግባባት ላይ ተደርሷል።

‎የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ግልጽ እና ፍትሃዊ በማድረግ የህብረተሰቡን እርካታ ማሳደግ የመጀመሪያ ትኩረት እንደሚሆን ተመላክቷል።

‎አዲሱ አፌ ጉባኤ እና ጠቅላላ አስተባባሪው የከተማዋን ሁለንተናዊ እድገት ለማፋጠን ከህዝቡና ከየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

‎ይህ የሥራ ርክክብ የኃላፊነት ቅብብሎሽ ብቻ ሳይሆን የህዝብ አደራን በመቀበል የከተማችንን እድገት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚደረግ የአዲስ ምዕራፍ መሆኑ ተገልጿል ።

‎በመጨረሻም የቀድሞው የከተማ አስተዳደር አስተባባሪ ለአዲሶቹ ተሿሚዎች መልካም የሥራ ዘመን የተመኙ ሲሆን በቀጣይ የልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።


‎ ነሐሴ 07/2018 ዓ/ም
‎ ላስካ

Address

Basketo, Laska
Aleta

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በባስኬቶ ዞን የላስካ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት Laska Communication:

Shortcuts

Share