Machakel Woreda Government Communication Affairs Office

Machakel Woreda Government  Communication Affairs Office ራዕይ ፦
በመረጀ የበለጸገ ሁለገብ ተሳትፎ የሚያደርግና በጋራ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት የፈጠረ ህዝብ መገንባት!!
የማቻክል ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ፌስቡክ ገፅ

 #እንኳን ደስ አላችሁ !!በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ሚንስትሪ  ፈተና የወሰድ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማስ...
02/08/2026

#እንኳን ደስ አላችሁ !!

በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ክልል አቀፍ የ8ኛ ክፍል ሚንስትሪ ፈተና የወሰድ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን አስታወቀ።

የሰላም ማስከበር አቅምን ለማጠናከር የሠለጠኑ ጥምር የፀጥታ ኃይሎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቁ ። የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚደረገውን የአቅም ግንባታ ሥራ የበለጠ ለማጠናከር በ...
02/08/2026

የሰላም ማስከበር አቅምን ለማጠናከር የሠለጠኑ ጥምር የፀጥታ ኃይሎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቁ ።

የአካባቢን ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር የሚደረገውን የአቅም ግንባታ ሥራ የበለጠ ለማጠናከር በደብረ ማርቆስ ከተማ በሚገኘው የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ደብረ ማርቆስ መሠረታዊ ፖሊስ ማሠልጠኛ ኢንስቲትዩት ከደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጋር በመቀናጀት ያሠለጠናቸው ጥምር የፀጥታ ኃይሎች በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመርቀዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ የአገርን ሰላም፣ ሉዓላዊነትና ሕዝባዊ ደህንነት ለማደፍረስ የሚደረጉ ማናቸውም ሙከራዎች ሊሳኩ እንደማይችሉ ገልጸው የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ከሕዝብ ጋር በመተባበር የሰላም ጠባቂነት ተልዕኳቸውን በብቃት እየተወጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

አቶ ተሾመ አክለውም ተመራቂዎቹ የሕዝብን ሰላምና ደህንነት የማስከበር ከባድ ኃላፊነት እንደተጣለባቸው በማስገንዘብ፣ ከሕግ አስከባሪ ተቋማትና ከማኅበረሰቡ ጋር በተቀናጀ ሁኔታ በመስራት ዜጎች በሰላምና በመረጋጋት እንዲኖሩ የተጠበቀባቸውን ግዴታ በታማኝነትና በሙያዊ ብቃት እንዲወጡ አሳስበዋል።

አቶ ተሾመ ዋለ በመልዕክታቸው፣ የኢትዮጵያ አርበኞች የሀገራቸውን ነፃነትና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የከፈሉት መስዋዕትነት የዛሬው ትውልድ የሚወስደው ታሪካዊ አደራ መሆኑን ገልጸው ፤ ተመራቂዎቹም ያንን ታሪካዊ ወግ በመጠበቅ ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው ታማኝ በመሆን፣ የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት፣ በሙያዊ ብቃትና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት እንዲወጡ አሳስበዋል።

ተመራቂዎቹ በበኩላቸው በሥልጠና ቆይታቸው ያገኙት የወታደራዊ ዕውቀት፣ ሙያዊ ክህሎትና የአመለካከት ግንባታ ለሚጠበቅባቸው ተልዕኮ በቂ ዝግጅት እንዳደረገላቸው ገልጸው በቀጣይም የሕዝብን ሰላምና ደህንነት ለማስከበር በቁርጠኝነትና በሙሉ ኃላፊነት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ኃላፊዎች፣ አሠልጣኞች፣ የፀጥታ ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች የተጋበዙ እንግዶች ተገኝተው ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
East Gojjam Zone Prosperity Party

የአማራ ክልል የ2019 ዓመታዊ በጀት ከ402 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ኾኖ ጸደቀ።የአማራ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በ201...
01/08/2026

የአማራ ክልል የ2019 ዓመታዊ በጀት ከ402 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ኾኖ ጸደቀ።

የአማራ ክልል ምክር ቤት እያካሄደ በሚገኘው 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በ2019 በጀት ዓመት ለክልሉ የልማት ሥራዎች ማስፈጸሚያ በጀት 402 ቢሊዮን 285 ሚሊዮን 713 ሺህ 544 ብር ኾኖ አጽድቋል።

የ2019 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀቱ በ2018 በጀት ዓመት ከተመደበው የ78 ነጥብ 4 በመቶ ወይም የ176 ቢሊዮን 831ሚሊዮን 934 ሺህ 307 ብር ዕድገት እንዳለው የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ ኀላፊ አታላይ ጥላሁን ገልጸዋል፡፡

ከዓመታዊ በጀቱ 71 ነጥብ 3 በመቶ የሚኾነው በክልሉ ከሚሠበሠብ ገቢ፣ 27 ነጥብ 6 በመቶ የሚኾነው ከፌዴራል መንግሥት ጥቅል የቀመር መደበኛ ድጋፍ ድርሻ እንዲኹም ቀሪው ደግሞ ከልዩ ልዩ ምንጮች እንደሚሸፈን ተገልጿል።

የተመደበው በጀት በዓመቱ ለዘላቂ ልማት ዕቅድ ማስፈጸሚያ፣ ለልዩ ልዩ ሪፎርሞች እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፣ ለድህነት ተኮር ሥራዎች እና የክልሉን የመልማት አቅም ታሳቢ ያደረገ ስለመኾኑም ተመላክቷል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በ2018 በጀት ዓመት የክልሉ መንግሥት ሥራ ላይ ላዋለው ከ39 ነጥብ 1ቢሊዮን ብር በላይ የተጨማሪ በጀት አጽድቋል።

መረጃው፦ የአማራ ኮሙኒኬሽን

 #በማቻክል  ወረዳ በ2018/19 የመኸር ምርት ዘመን ከ24  ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ማሳ በስንዴ ዘር መሸፈን መቻሉ ተገለጸ።****************************በምስራቅ ጎጃም ዞ...
01/08/2026

#በማቻክል ወረዳ በ2018/19 የመኸር ምርት ዘመን ከ24 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ማሳ በስንዴ ዘር መሸፈን መቻሉ ተገለጸ።
****************************
በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ግብርና ጽህፈት ቤት በ2018/19 የመኸር ምርት ዘመን 24 ሺህ 800 ሄክታር መሬት ማሳ በዘር መሸፈኑን አስታወቀ።

የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መላኩ ተበጀ የ2018/19 በመኸር ምርት ዘመኑ ከ39ሽህ 884 ሄክታር መሬት ውስጥ 24ሺህ 800 ሄክታር መሬት በስንዴ ሰብል የተሸፈነ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በቂ የስንዴ ምርጥ ዘር ለአርሶአደሩ የተሰራጨ መሆኑን ጠቁመው ለምርት መጨመር ወሳኝ የሆኑ የአሰራር ዘዴዎችን መጠቀም መቻሉን ተናግረዋል።

አቶ መላኩ አያይዘው አርሶ አደሩን ተመሳሳይ አመለካከት እንዲኖር የክላስተር የአዘራር ዘዴን በተደራጀ መልኩ ግንዛቤ በመፍጠር ምርትና ምርታማነትን የበለጠ ለማሳደግ
ከግብዓት አቅርቦት ጀምሮ ከባለፈው አመት በተሻለ መልኩ ጤናማ የሆነ ስርጭት እንዲመራ ከማድረግ በተጨማሪ አርሶአደሩ ተደናግሮ ወደ ሌላ አስተሳሰብ ሳይጠለፍ በግብርና ስራው ብቻ ትኩረት እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

 #የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማጎልበት ከተለያዩ በሽታዎች ራስን መጠበቅ እንደሚገባ በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡**************...
01/08/2026

#የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማጎልበት ከተለያዩ በሽታዎች ራስን መጠበቅ እንደሚገባ በምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ፅህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
***********************
የማቻክል ወረዳ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ፅህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ልወየሁ ሰጥዓርጌ በተያዘዉ የክረምት ወቅት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፣ ስልጠናና ዉድድርና ሌሎች ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰሩ መሆኑን ገልፀዉ ዜጎች የጎዳና ላይ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በማጎልበት ራሳቸውን ከተለያዩ በሽታዎች ሊጠብቁ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

እንደ ወረዳ ሀምሌ 27 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት በአማኑኤል ከተማ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለማካሄድ እየሰሩ መሆኑን የተናገሩት ሀላፊዋ የዚህ ፕሮግራም ዋና አላማም ህብረተሰቡ በሚኖርበትና በሚሰራበት አካባቢ ዘወትር የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እያደረገ ጤንነቱን የሚጠብቅ አምራች ዜጋ እንዲሆን ማስቻል ነው ብለዋል፡፡

ሀላፊዋ አያይዘዉም እንደዚህ አይነት ፕሮግራሞች ህብረተሰቡ በጋራ በመሰባሰብ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን እየሰራ ማህበራዊ መስተጋብሩን የሚያጠናክርበት፤ ወዳጅነትን፣ፍቅርንና ሰላሙን የሚገነባበት ልዩ መርሃ-ግብር እንደሆነ ህዝቡ አውቆ ህዝብ በየአካባቢው በመውጣት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በመስራት ጤናውን እንዲጠብቅ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል ።

"በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የሰኔ 15ቱ የከፍተኛ አመራሮች ግድያ አንዳች ግብ ያላሳካ መጥፎ ጠባሳ ጥሎ ያለፈ ነው"- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በአ...
31/07/2026

"በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የሰኔ 15ቱ የከፍተኛ አመራሮች ግድያ አንዳች ግብ ያላሳካ መጥፎ ጠባሳ ጥሎ ያለፈ ነው"- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በአማራ ክልል እና በአዲስ አበባ የተከሰተው አሳዛኝ ድርጊት በስሑት የመረጃ ግምገማ እና በሁለት እግር ለማንከስ በተደረገ የፖለቲካ ስሌት የተከሰተ ጥቁር ጠባሳ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአሚኮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ በወቅቱ ያጋጠመውን ሁኔታ ሲያብራሩ ድርጊቱ ለሀገር ለውጥ ከፍተኛ ሚና የነበራቸውን እንደ ዶክተር አምባቸው እና ጄኔራል ሠዓረ ያሉ ቁልፍ የለውጥ ኃይሎችን ያሳጣ፣ በፖለቲካ አመራሩ መካከል የነበረውን መተማመን ያቀዘቀዘ እና በኃይል ሥልጣን ለመያዝ የሚደረግን አጥፊ የፖለቲካ ባሕል ያስቀጠለ መሆኑን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁንም ድረስ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እያንዣበበ ያለውን አደገኛ የትርክት ስብራት አጥብቀው ኮንነዋል።

ገዳይም ሟችም በእኩል ደረጃ በጀግንነት የሚወደሱበት ሁኔታ አደገኛ የፖለቲካ ብዥታ መሆኑን ጠቅሰው፣ ታሪክን እያንሻፈፉ እና እየመረጡ ማቅረብ የነገውን ትውልድ ዋጋ የሚያስከፍል በመሆኑ ታሪክ እንዳለ በትክክለኛው መንገድ መቀመጥ እንዳለበት አሳስበዋል።

የሰኔ 15ቱን ክስተት አስመልክቶ በወቅቱ ስለተሰጠው መግለጫ ሲራገቡ የነበሩት የሴራ ትንተናዎችም እውነቱን ለመቅበር የሞከሩ መሆኑን ጠቅሰው፣ ድርጊቱ ከጅምሩ ምንም ግብ ያላሳካ እና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጠባሳነቱ የሚታወስ ዘግናኝ አጋጣሚ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

31/07/2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻክል ወረዳ በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ከ137 ሺ ቶን በላይ የወተት ምርት ለገበያ ቀርቧል :- የወረዳዉ እንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ፅ/ቤት

 #‎የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ በአልማ የሚደረገውን የተቋማት ግንባታ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ፡፡‎*******************የምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳና የ...
30/07/2026

#‎የማህበረሰቡን ተሳትፎ በማሳደግ በአልማ የሚደረገውን የተቋማት ግንባታ ድጋፍ አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
‎*******************
የምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳና የአማኑኤል ከተማ አስተዳድር አልማ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት “ በራስ የመልማት አቅምን እናሳድግ" በሚል መሪ መልዕክት የወረዳ ና የከተማ አስተዳድሩ አመራሮች፣የአልማ ኮሚቴ አባላት እንዲሁም አጋር አካላት በተገኙበት የ2018 የአልማ ጉባኤ ተካሄደ።

የጉባኤ ሪፖርት ያቀረቡት የማቻክል አማኑኤል አልማ ቅርጫፍ ጽህፈት ሃላፊ አቶ ይነበብ ደርሰህ አልማ በራስ አቅም የማህበረሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግርን በራስ አቅም በመፍታት በትምህርት፣ በጤና፣ በስራ ዕድል ፈጠራና እንዲሁም ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን ለማቋቋም የሚሰራ የእኔ፤የአንቺ፤ የሁላችንም የልማት ማህበር መሆኑን ተናግረዋል።

‎በጉባኤው ላይ የተገኙት የአማኑኤል ከተማ አስተዳድር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ሽታው የሻነህ በአልማ የተጀመሩና በአዲስ የሚገነቡ አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት በመስራት በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን ታአማኒነት ለማሳደግ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኞችእና የግንባታ ፍትሐዊነት ላይ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

‎የማቻክል ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አንዷለም አልማ በጸጥታ ችግር ውስጥ ሆኖ የማህበረሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳድር ጥያቄዎችን ምላሽ የሰጠ ያልተዘመረለት የወረዳችን ባለውለታ የልማት ማህበር መሆኑን በመግለጽ በአልማ የተጀማመሩ የትምህርት ቤት ግንባታዎችን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ በትምህርት ላይ የተፈጠረውን ስብራት ወደ ነበረበት በመመለስ እና ከትምህርት ገበታ ውጭ የሆኑ ተማሪዎችን ወደትምህርት ገበታቸው ለመመለስ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻክል ወረዳ በ2018/2019 የመኸር የምርት ዘመን  እለማ የሚገኝ የበቆሎ ሰብል አሁናዊ ቁመና ከፊል ገፅታ:-
30/07/2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻክል ወረዳ በ2018/2019 የመኸር የምርት ዘመን እለማ የሚገኝ የበቆሎ ሰብል አሁናዊ ቁመና ከፊል ገፅታ:-

‎"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!" #የክረምት የበጎ ፈቃድ ማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው።‎**************‎የምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በአማኑኤል  ከተ...
30/07/2026

‎"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ!"
#የክረምት የበጎ ፈቃድ ማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ነው።
‎**************
‎የምስራቅ ጎጃም ዞን የማቻክል ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በአማኑኤል ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የክረምት የበጎ ፈቃድ ማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጠ መሆኑን አስታውቋል።

የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ካሳ ደመቀ ‎የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑ ተማሪዎችን እውቀት ለማዳበር እና የነገውን ስኬታቸውን ለማገዝ የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ተግባር መርሃ ግብር አካል የሆነው የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን በመግለጽ‎ከተጀመረው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ጎን ለጎን፥ አቅም የሌላቸውና ረዳት የሌላቸው ሕፃናት በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከገበታው እንዳይቀሩ ለማድረግ የደብተርና ሌሎች የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶችን የማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

Address

Amanuel, East Gojjam
Amanu'el

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Machakel Woreda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Machakel Woreda Government Communication Affairs Office:

Shortcuts

Share