28/08/2026
የቻግኒ ከተማ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ የተቋማት ክትትልና ቁጥጥር ስራ ዛሬም እንደቀጠለ ነው///////////////////////////////////////
ነሀሴ 22/2018ዓ/ም የቻ/ከተማ ምክር ቤት ጽ/ቤት
የቻግኒ ከተማ ምክር ቤት የኢኮኖሚ ልማት በጀት ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤትን የ2018 በጀት የ4ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም ክትትልና ቁጥጥር አደረገ።
የቻግኒ ከተማ አስተዳደር ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤትም ቋሚ ኮሚቴ ባዘጋጀው ቼክሊስት መሠረት የ2018 በጀት የ4ኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀማቸውን ሪፖርት በቻግኒ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት በአቶ ገበየሁ አልማው በኩል እንዲቀርብ ተደርጓል።
በቀረበው ሪፖርት ላይ በቋሚ ኮሚቴዎች በኩል ማብራሪያ እንዲሁም ምላሽ የሚሹ ጥያቄዎች እንደሚከተሉት አንስተዋል
1. የኮሪደር ልማት ስራው በህብረተሰብ ተሳትፎ እንዲደገፍ በወቅቱና በጥራት ተሰርቶ እንዲጠናቀቅ የተቋሙ የክትትል ስራ ምን እንደሚመስል?
2.የከተማችን ደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ሰርዓት እንዲይዝ እና ከተማችን ጽዱ እንድትሆን እየተሰራ ያለ ስራ ምን ይመሰላል?
3.በከተማችን የሚሰሩ መሠረተ ልማቶች በጥራት እንዲሰሩ ክትትልና ቁጥጥር ምን ይመስላል ? የሚሉና ሌሎች ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ በተነሱ ጥያቄዎችና ሀሳቦች ላይ በማኔጅመንቱና በጽ/ቤት ኃላፊ በኩል በቂ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጧባቸው የክትትልና ቁጥጥር ስራ በተሳካ መንገድ ተጠናቋል።