16/08/2026
የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢንሸቲቭ" ተብሎ የተጀመረው ወጣቶች ላሳዩት ከፍተኛ ፍላጎትና ስኬት ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማፋጠን ግቡ ወደ 7 ሚሊየን አድጓል።
ኤዞ፦10/12/2018 ዓ.ም (የቆጎታ ወረዳ ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ
ይህ የ7 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ኢንሸቲቭ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች መንግሥት መካከል በተደረገ ስትራቴጂካዊ ሁለተናዊ ትብብር የተጀመረ ነፃ የመስመር ላይ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥልጠና ፕሮግራም ነው።
መጀመሪያ ላይ "የ5 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደሮች ኢንሸቲቭ" ተብሎ የተጀመረ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ላሳዩት ከፍተኛ ፍላጎትና ስኬት ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማፋጠን ግቡ ወደ 7 ሚሊየን አድጓል።
የሚሰጡ ነፃ የሥልጠና ዘርፎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቀው Udacity ፕላትፎርም አማካኝነት የሚሰጡ ሲሆን አራት ዋና ዋና ዘርፎችን የኮዲንግ እና የፕሮግራሚንግ መሠረታዊ እውቀቶች ፣የመረጃ ትንተና ስታቲስቲክስ እና ዳታ ሳይንስ ፣ የሰው ሠራሽ አስተውሎት መሠረታዊ ፅንሰ ሐሳቦች እና የሞባይል መተግበሪያዎች ልማትን ያካተቱ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች አሏቸው።
ፍላጎቱ ያለው ማንኛውም ሰው በይፋዊው ድረ-ገጽ ethiocoders.et በመግባት በቀላሉ መመዝገብ እና ሥልጠናውን ወዲያውኑ መጀመር ይችላል።