Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

አስደሳች ዜና ለዓይን ህሙማን በሙሉ!‎‎በዓይነቱ ልዩ የሆነ የዓይን ምርመራ እና የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ሕክምና ከነሐሴ 18/2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም ከሂሊያን ካትራክት...
14/08/2026

አስደሳች ዜና ለዓይን ህሙማን በሙሉ!

‎በዓይነቱ ልዩ የሆነ የዓይን ምርመራ እና የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ሕክምና ከነሐሴ 18/2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም ከሂሊያን ካትራክት ፕሮጀክት ጋር ከአሜሪካን ሀገር በሚመጡ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው የዓይን ስፔሻሊስት ሐኪሞች በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በነፃ ይሰጣል ።

‎ከጋሞ ዞን ፣ አጎራባች ዞኖችና ክልሎች ለሚመጡ ሕሙማን ሕክምናው በነጻ ይሰጣል። ስለሆነም መላው ማህበረሰብ የሕክምናው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ተላልፏል።

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ወር የሚቆይ ነፃ የሕክምና ፣ ምርምራ እና የምክር አገልግሎት መስጠት ጀመረ‎‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎በአርባ ምን...
13/08/2026

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአንድ ወር የሚቆይ ነፃ የሕክምና ፣ ምርምራ እና የምክር አገልግሎት መስጠት ጀመረ

‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" መሪ ቃል የተዘጋጀውና ለአንድ ወር የሚቆየው ነፃ የሕክምና ምርመራ እና የምክር አገልግሎት በዛሬው ዕለት ሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ተጀምሯል።

‎በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ኢንጂነር አብደላ ከማል፣ የዩኒቨርሲቲው ምክትል ፕሬዝደንቶች እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ነፃ የሕክምና አገልግሎቱን በይፋ አስጀምረዋል።

‎ፕሬዝደንቱ በመክፈቻ ንግግራቸው ሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መሆኑን ገልጸው፤ ይህንን እጅግ አስፈላጊ የሆነ ነፃ የሕክምና አገልግሎት መርሐ ግብር አስተባብረው ላዘጋጁ የሆስፒታሉ አመራሮች እና የሕክምና ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል። አክለውም ማኅበረሰቡ በሆስፒታሉ በአካል በመገኘት የነፃ ሕክምናው ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

‎የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ደስታ ጋልቻ እንደገለጹት ነፃ አገልግሎቱ የስኳር እና የደም ግፊት የቅድመ ምርመራ፣ የክትትል እና የባለሙያ ምክርን፣ የልዩ ልዩ የቆዳ በሽታዎች እና የአለርጂ ምርመራን፣ የዓይን ጤና ምርመራ እንዲሁም የሥነ-አእምሮ የምርመራ እና የሥነ-ልቦና የምክር አገልግሎትን ያካትታል። በተጨማሪም የኤች.አይ.ቪ (HIV)፣ የጉበት/ሄፓታይቲስ (Hepatitis)፣ የቲቢ (TB) እና የሲፊሊስ (Syphilis) ተላላፊ በሽታዎች ምርመራዎችን እንዲሁም የጡት እና የማህፀን በር ቅድመ ካንሰር ምርመራ (Screening) አገልግሎቶችን የሚሸፍን ይሆናል።

‎በመርሐ ግብሩ የደም ልገሳ መርሐ ግብር እየተካሔደ ሲሆን የዩኒቨርሲቲው አመራሮች የሆስፒታሉን የሥራ እንቅስቀሴ ተዛዙረው ጎብኝተዋል።

የመንግስት ሐብት አጠባበቅና ብክነትን በመከላከል የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።‎‎የክልሉ ጤና ቢሮ ከፋይናንስ ቢሮ የኢንስፔክሽንና የውስጥ ኦዲት ቁጥጥር...
12/08/2026

የመንግስት ሐብት አጠባበቅና ብክነትን በመከላከል የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

‎የክልሉ ጤና ቢሮ ከፋይናንስ ቢሮ የኢንስፔክሽንና የውስጥ ኦዲት ቁጥጥር አገልግሎት ጋር በመቀናጀት ያደረገውን ፋይናንሻል ኦዲት ሪፖርት ግብረመልስ ዙሪያ መክረዋል።

‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊና ጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ የፋይናንስ አሠራር ስርዓት ፍትሐዊነትን ማጠናከር እንደሚገባም አስታወቁ።

‎በፋይናንስ ቢሮ የኢንስፔክሽንና የውስጥ ኦዲት ቁጥጥር አገልግሎት ዋና ኃላፊ አቶ ታመነ ታምርሶ በመድረኩ እንደተናገሩት የኦዲት አሠራር ስርዓት የውስጥ፣ የውጪ እና ልዩ ኦዲት የሂሳብ ምርመራዎች እንደሚካሄዱ ተናግረዋል።

‎የኢንስፔክሽንና የውስጥ ኦዲት ቁጥጥር አገልግሎት የተሰራው የፋይናንሻል ኦዲት ሪፖርት ግብረ መልስ ለጤና ቢሮ ማናጅመንት ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

‎ለተነሱ ጥያቄዎች የፋይናንስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና አስተዳደርና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነቢዩ ቤዛ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

‎የሂሳብ ምዝገባ ደጋፊ ሰነዶችን አሟልቶ በመመዝገብ ጥራት ያለው የፋይናንስ ስርዓት መተግበር እንደሚገባ ግብረኃይሉ አስታውቋል፡፡

‎የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት፣ የመንግስት ኃብት አጠቃቀም፣ ግንባታ ሂደትና ጥራት ቁጥጥር እንዲጠናከር ኦዲት ግብረኃይሉ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ አመላክተዋል።

‎ትክክለኛ የሂሳብ ሥራ ሪፖርት በማደራጀት፣ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል፣ ስህተቶችን በማረም እና ሀብት ለታለመለት አላማ እያዋሉ መሆኑን ምክትል ጤና ቢሮ ኃላፊና ጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ አስታውቀዋል።

‎የሂሣብ ምዝገባ፣ ወርሃዊ የሂሳብ ሪፖርት አቀናጅቶ የጋራ አድርጎ መላክ፣ በቂ የኦዲት ባለሙያ ምደባና የሰው ኃይል ማሟላት እንደሚገባ በፋይናንስ ቢሮ የኢንስፔክሽንና የውስጥ ኦዲት ቁጥጥር አገልግሎት ዋና ኃላፊ አቶ ታመነ ታምርሶ አሳስበዋል።

በክልሉ ባሉ ወረዳዎች የተቋቋመው የIMS ማዕከላት በሚያደርጉት ድንገተኛ በሽታዎች ቁጥጥር ውጤት መታየቱ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡‎‎የ31ኛ ሣምንት 3ኛ ቀን የድንገተኛ አደጋዎች በሽታ ቁጥጥርና ...
12/08/2026

በክልሉ ባሉ ወረዳዎች የተቋቋመው የIMS ማዕከላት በሚያደርጉት ድንገተኛ በሽታዎች ቁጥጥር ውጤት መታየቱ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

‎የ31ኛ ሣምንት 3ኛ ቀን የድንገተኛ አደጋዎች በሽታ ቁጥጥርና መከላከያ ተግባርን በበይኔ-መረብ ገምግመዋል፡፡

‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎በሣምንቱ የተደረጉ የወባ በሽታ ቁጥጥርና መከላከል ዘመቻው ውጤት እያመጣ መሆኑን የሕብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡

‎በሣምንቱ 3ኛ ቀን በተደረገ ግምገማ የጤና ተግባራን ለማጠናከር በየደረጃው የተቋቋመው IMS ማዕከላትን በማጠናከርና የዜጎችን ጤና ለማሻሻል የተሰሩ ሣምንታዊ የወባና ሥርዓተ ምግብ አለመመጣጠን ችግር ሥራ ሪፖርት በወ/ሮ ምስጋና ማቱሳላ ቀርቧል፡፡

‎በክልሉ በሁሉም አከባቢዎች እየተካሄደ ያለው የክረምት በጎ ተግባራት ሪፖርት በምክትል ቢሮ ኃላፊና ህክምና አገልግሎት ዘርፍ ኃላፊ በአቶ ናፍቆት ብርሃኑ ለውይይት ቀርቧል፡፡

‎ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ልየታና ህክምና፣ ደም ማሰባሰብና ህክምና፣ የማህፃን ጫፍ ካንሰር ልየታ፣ ምርመራና ህክምና፣ አቅመ ደካማ ቤት ግንባታና ጥገና ሥራዎች በሣምንቱ ትኩረት ያገኙ በጎ ተግባራት ናቸው ሲል አቶ ናፍቆት አብራርተል፡፡

‎የጤና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ከዞን ጤና መምሪያ ጋር ያለው የሥራ ሰንሰሌትን በማጠናከር መረጃ ቅብብሎንና ስርጭትን ማዘመን፣ መረጃ ወቅታዊነትን መጠበቅ፣ ዕቅድ አፈፃፀምና ሪፖርት አደራረግ፣ ሚዲያ ጥቆማ፣ የተገዛ የሚዲያ አየር ሰዓት አጠቃቀም እና የሚዲያ ፕሮቶኮል ዙሪያ ግንዛቤ ሰነድ በህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በሠራዊት ዲባባ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

‎በቀረቡ ሣምንታዊ ሪፖርቶችና ኮሚኒኬሽን ሰነድ ዙሪያ የበይኔ መረብ ተሳታፊዎች ሀሳብ አስተያየት በመስጠት ሰፊ ውይይት አካሂደዋል፡፡

‎ወባ በሣምንቱ መቀነሱን ያስገመገመው ሪፖርቱ በየወረዳው የተቋቋው የክስተት አስተዳደር ስርዓት ግብረኃይሉ አጠናክሮ እንዲያስቀጥል የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ አሳስበዋል፡፡

‎ከህክምናና ጤና ቁጥጥር ተግባራት አንፃር አበረታች ተግባራት መከናወናቸውን የገለፁት ዋና ዳሬክተር አቶ አጉኔ፤ በጤና ቁጥጥር እርምጃ ብቻ ሣይሆን በግል የህክምና ተቋማት የተገኙ የወባና በንጥሬ ነገር የበለፀጉ ምግቦች ማን? ከየት? እንዳመጣ በህግ አግባብ ተጠያቂ የማድረግ ሥራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

‎የክልል ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ በበላቸው ሥርዓተ ምግብ አለመመጣጠን በሽታን ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ሲሆን በዘርፉ የሚከሰቱ ችግሮችን በጋራ መከላከል ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

‎የተመዘገበው የወባ ቁጥጥርና መከላከል ውጤትን በማጠናከር ውስንነቶች የሚስተዋልባቸው አከባቢዎች ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚገባም አቶ መና አሳስበዋል፡፡

‎የክረምት በጎ ተግባር ሥራው ውጤታማ የሰብዓዊ ተግባራት መገለጫ በመሆናቸው ተግራሩን ማጠናከር እንደሚገባም በመጠቆም፡፡

‎የቀረበው የሚዲያና ኮሚኒኬሽን የአሠራር ሥርዓትን ተግባራዊ በማድረግ እንደ ዞን የህዝብ ግንኑነት ሥራን በማጠናከር ለህብረተሰቡ አስፈላጊውን መረጃ ተደራሽ ለማድረግ መሥራት እንደሚገባ ምክትል ቢሮ ኃላፊና ጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ መክረዋል፡፡

የወባ በሽታን ለመከላከል ቤት ለቤት የምደረገው የጉብኝትና የአሰሳ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል አስታወቀ።‎‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/20...
12/08/2026

የወባ በሽታን ለመከላከል ቤት ለቤት የምደረገው የጉብኝትና የአሰሳ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር ማዕከል አስታወቀ።

‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የወባና ስርዓተ ምግብ አለመመጣጠን በሽታ ቁጥጥር ወረዳዎች በተቋቋመው የIMS ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ አስታወቁ።

‎ከአከባቢ ቁጥጥር አንጻር ወባ በየአከባቢው ጥሩ አፈጻጸም የተመዘገበ ሲሆን፤ አንዳንድ ወረዳዎችን በመደገፍ የዜጎችን ጤና ማጠናከር እንደሚገባ አቶ አብርሃም ሞጋ ወቅታዊ ሪፖርት ተደምጧል።

‎የወባን በሽታን መርምሮ ከማግኘት አንጻር ያለውን ምጣኔ ለማሳደግ የላቦራቶሪ ጥራት ስራ አጠናክሮ መሰራት እንዳለበት የህክምና አገልግሎት ከፍተኛ ባለሙያ ዶ/ር አካሉ አደፋ ተናግረዋል።

‎ተጠያቂነትን በማስፋት እና የቁጥጥር ስራን በማጠናከር የሰው ልጆችን ጤና ልጎዱ ከሚችሉ መዲሃኒቶች የህብረተሰቡን ጤና እንዳይጎዱ ተባብሮ መስራት እንደሚገባ የህክምና ጥራት ቁጥጥር ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ፍሳኔ ፍርዳ ናቸው።

‎የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ አሳምነው አይዛ በበኩላቸው የንቅናቄው ስራ እስከ ማህበረሰቡ በማድረስ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይገባል ብለዋል።

‎በሽታ መከላከልና ጤና ማጎልበት ዳይሬክተር አቶ መልካሙ ተንቼ ወባ እና የስርዓተ ምግብ አለመመጣጠን በሽታን ለመከላከል እተሰራ ያለውን ስራ አበረታች በመሆኑ ክትትሉን ማጠናከር እንደምገባ ጠቁመዋል።

‎የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ በበኩላቸው በሳምንት እና በየቀኑ የሚመጡ ጤና መረጃዎች በማደራጀት ለህብረተሰብ ጤና ክልላዊ የጤና ተግባራትን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

‎የሥርዐ‍ተ ምግብ አገልግሎት በሽታ ችግር ያለባቸው የህፃናት ህክምና ማዕከል የሌላቸው ዞኖች በቀጣይ ተግባዊ እንዲያደርጉ አቶ አጉኔ አሳስበዋል።

‎የህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ ጨምረው የወባ ቁጥጥር ተግባሩ በታቀደው መሠረት ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን አስታውቀዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ለአርባ ምንጭ አካል ጉዳተኞ ተሃድሶ ማዕከል የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ ‎‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የደቡብ ኢትዮ...
12/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ለአርባ ምንጭ አካል ጉዳተኞ ተሃድሶ ማዕከል የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ

‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 6/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ለአርባ ምንጭ አካል ጉዳተኞ ተሃድሶ ማዕከል የተሽከርካሪ ድጋፍ አደረገ።

‎ድጋፉን በማዕከሉ ተገኝተው ያስረከቡት የቢሮው ምክትል ኃላፊና የምግብና መድሃኒት ጤናና ጤና ነክ ጉዳዮች ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ሶንቆ ናቸው።

‎ማዕከሉ በክልሉ ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ከተለያዩ አካባቢዎች ለሚመጡ የአካል ጉዳተኞች የሚሰጠው ድጋፍ የሚበረታታ ነው ብለዋል።

‎ቢሮው ተቋሙ የሚሰውን አገልግሎት ለማጠናከር ድጋፉን ማድረጉን ጠቅሰው ተናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ዮሴፍ አስታውቀዋል።

‎የማዕከሉ ሠራተኞች አንድነታቸውን በማጠናከር የሚሰጡትን ሙያዊ አገልግሎት ይበልጥ እንዲያሻሽሉ አሳስበዋል።

‎የአርባ ምንጭ አካል ጉዳተኞ ተሃድሶ ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳበሮ ዳልጮ በበኩላቸው ማዕከሉ በ2018 ከ5 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች አገልግሎት መስጠቱን ገልጸዋል።

‎አገልግሎቱን የደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ አጎራባች ኦሮሚያ እና ሌሎች ክልሎችን ጨምሮ ከአዲስ አበባ እንዲሁም ከመላው ኢትዮጵያ ለመጡት መሰጠቱን አመልክተዋል።

‎የተፈጥሮ ጉዳትን ጨምሮ የአካል ጉዳት ህክምና ሰው ሰራሽ አካልና ሌችንም እንደሚያካትት የጠቀሱት አቶ ዳበሮ ድጋፉ እንደሚጠናክር ጠቅሰዋል።

‎ቢሮው ላደረገው ድጋፍ አቶ ዳበሮ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎አንዳንድ የማዕከሉ ሰራተኞች በበኩላቸው የተሽከርካሪ ድጋፉ በሎጅስቲክስ እጥረት የተገደበውን አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ማድገረግ እንደሚያስችል ጠቅሰዋል።

‎ቢሮው ለማዕከሉ ድዳፍ ያደረገው ተሽከርካሪ ማዕከሉ በተለይ አስቸጋሪ በሆኑ የሀገሪቱ ገጠራማ ክፍሎች የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደሚያጠናክር በወቅቱተጠቅሷል።

አስደሳች ዜና  ለጋሞና አካባቢዋ ዞኖች በሙሉ!‎‎በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የላንቃና የከንፌር መሰንጠቅ ነፃ ቀዶ ህክምና ከነሐሴ 15-17/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 03 ቀን የሚቆይ ዘ...
12/08/2026

አስደሳች ዜና ለጋሞና አካባቢዋ ዞኖች በሙሉ!

‎በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የላንቃና የከንፌር መሰንጠቅ ነፃ ቀዶ ህክምና ከነሐሴ 15-17/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 03 ቀን የሚቆይ ዘመቻ ለማካሄድ ተዘጋጅቷል።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ፣ ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እንዲሁም ከትረስት በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር የላንቃና ከንፌር መሰንጠቅ ነፃ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጀ ስለሆነ፣

‎ሁሉም ባለድርሻ አካላት የከንፌርና ላንቃ መሰንጠቅ ጤና ችግር ያለባቸው በማንኛውም ዕድሜ ክልል ያሉ ዜጎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማሳወቅና የመቀስቀስ ሥራ እንድትሰሩ የአክብሮት ጥሪ እያስተላለፍን ፣

‎ልብ ይበሉ❤❤!!

‎ማንኛውም የችግሩ ተጋላጭ ወገኖች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ጤና ተቋማት መረጃውን በማድረስ እና ወደ አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በመምጣት በነፃ መታከም የሚትችሉ መሆኑን የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በአክብሮት ጥሪውን ያስተላፋል፡፡

‎ #እንዳያመልጥዎ!

‎ማሳሰቢያ ፤ ለታካሚዎች የሕክምና ፤የትራንስፖርት፤ የምግብ እና የአልጋ ወጪ በድርጅቱ ይሸፈናል፡፡
‎ሼር ሼር በማድረግ አዳርሱልን+++
‎ለበለጠ መረጃ
‎· 0926104204 ወይንም
‎· 0926427383 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡

የወባ በሽታ ስርጭትን ለመግታት እየተደረገ የሚገኘው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ፤‎‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የዞኑ ድንገተኛ ክስተት አስ...
11/08/2026

የወባ በሽታ ስርጭትን ለመግታት እየተደረገ የሚገኘው ጥረት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተባለ፤

‎አርባ ምንጭ፡- ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የዞኑ ድንገተኛ ክስተት አስተዳደር ስርዓት ቡድን የወባ በሽታ እና ከስርዓተ ምግብ አለመጣጣም በሽታ አኳያ በ31ኛ ሳምንት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን በበይነ-መረብ በመታገዝ ገምግሟል።

‎የወባ በሽታ ስርጭት አሁንም በዞኑ ከፍተኛ ሲሆን የበሽታው ስርጭት በዳራማሎ፣ ዋጫ ከተማ፣ ጋርዳ ማርታ እና ቁጫ ወረዳዎች ከፍተኛ መሆኑ ተገምግሟል።

‎ወባን የመመርመር እና የማከም አቅማን ከፍ ለማድረግ በዞኑ በሁሉም መዋቅሮች ለጤና ባለሙያዎች እና ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ባሳለፍነው ሳምንት በወባ በሽታ ህክምን ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መሰጠቱ ተጠቁሟል። ስልጠናው በወባ በሽታ ህክምና አሰጣጥ ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶችን እንደሚሞላ ይጠበቃል።

‎በተጨማሪም ከስርዓተ ምግብ አለመጣጣም በሽታ አኳያ የልየታው ስራ በሁሉም አከባቢዎች በትኩረትና ቅንጅት ሊሰራ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

09/08/2026
የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 25ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ‎‎​አርባ ምንጭ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ጤና ሙምሪያ)‎‎​የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሃግብር፣ 13ኛ...
09/08/2026

የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 25ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

‎​አርባ ምንጭ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ጤና ሙምሪያ)

‎​የጋሞ ዞን ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሃግብር፣ 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።

‎​ምክር ቤቱ በጉባኤው በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣ በ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ እና በረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ለዞኑ ሁለንተናዊ ዕድገትና ልማት አስፈላጊ በሆኑ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

‎​በጋሞ ባህል ምርምርና ኮንፍረንስ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ባለው በዚህ ጉባኤ ከምክር ቤቱ አባላት በተጨማሪ የዞኑ የተለያዩ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ኃላፊዎች፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች፣ የፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች፣ አፈ-ጉባኤዎች፣ በአርባ ምንጭ ማዕከል የሚገኙ የፌደራልና የክልል ተቋማት ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share