Tilahun Kebede

Tilahun Kebede President of South Ethiopia Regional State https://t.me/tilahunkebede
(5)

01/06/2026

የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-

• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤

በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡

ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።

Uummanni Itoophiyaa dinqisiisaafi ajaa'ibsiisaadha! Uumaa malee uummata keenya guutummaan beekuufi gamaaggamuu kan danda'u eenyu? Aadaa gabbataa, uummata biyya jaallatuufi fedhiisaa waloo eeguu danda'u ta'uusaa filannoo baranaatiin irradeebiidhaan addunyaatti agarsiiseera. Guyyaa seena-qabeessa har'aatiin:
- Qorriifi dukkanni halkani kan isaani hin sodaachifne,
- Aduun saafaafi bokkaan tasaa kan isaan jilbeenfachiifne,
- Cidhi, gaddi, da'umsiifi taateewwan hawaasummaa kanbiroon kan isaan dhorkine,
- Hiriironni dhedheeroon kan isaan hin nuffisiifne,
- Qaama miidhamtummaan sagalee kennuuf kan isaan hin daangessine,
- Dhukkubniifi dullumni abdii biyyaa arguuf kan isaan hin dhowwine,
- Daa'imasaanii kichuu bor biyya dhaalu baatanii filuun kan isaan hin dadhabsiifne
- Hundumaa caalaa lammiilee iyyiifi sodaachiifni diinaa isaan hin dhaabsifne,
Ciminni bu'aa bayii hedduu keessatti agarsiiftan gatii diimokraasiifi jiraachuu biyyatiif kanfalame waan ta'eef galata guddaatu malaafi.

Uummata kana tajaajiluun carroomuu waan ta'eef filatamtoonni warra isin kabajan kabajjanii uummata sirna diimookraasiif gatii baase kana qulqullummadhaan tajaajiluuf isin haa gahu.

The people of Ethiopia are an extraordinary and remarkable people. Other than the Creator, who can truly know and assess our people in their entirety? Through this year’s election, Ethiopians have once again shown the world that they are a people with a rich culture, deep patriotism, and the ability to safeguard the common good.

On this historic day:

* Citizens who were not intimidated by the cold and darkness of the night,
* Who were not deterred by the midday sun or sudden rain,
* Whom weddings, funerals, childbirth, and other social obligations did not prevent from participating,
* Who were not wearied by long lines,
* Whose physical disabilities did not stop them from casting their vote,
* Those whose illness and old age did not prevent from witnessing the hope of their country,
* Who were not exhausted by carrying their infant children; the future inheritors of the nation,
* And above all, whom the shouting and threats of enemies could not intimidate or stop;

The perseverance you demonstrated amid many challenges and hardships, against all odds, was a contribution made for democracy and for the very survival of the nation. For this, you deserve heartfelt gratitude.

It is a privilege to serve such a people. Therefore, may those who have been elected honor the trust placed in them and serve this people, with integrity and sincerity! A people who have paid a great price for the democratic system. May you be worthy of that responsibility.

27/05/2026
እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!መልካም በዓል
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!
መልካም በዓል

26/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!

ስለዒድ አል-አድሐ “ዐረፋ” በዓል ስናስብ ሦስት ነገሮች ቀድመው ይታወሱናል። መስዕዋትነት፣ መታዘዝ እና መተጋገዝ። አባት ልጁን ለመስዕዋት ያቀረበበት፤ ልጅ የአባቱን ትዕዛዝ የፈጸመበት፤ ሙስሊሞች የመተጋገዝን እሴት ለዓለም የገለጡበት በዓል ስለሆነ “ዐረፋ” በሕዝበ-ሙስሊሙ ዘንድ ትልቅ ትርጉም አለው።

እስማኤል ለነብዩ ኢብራሂም የመጀመሪያ እና ተወዳጅ ልጃቸው ነው። አላህ (ሱ.ወ.) ይሄን ተወዳጅና የመጀመሪያ ልጅ እንዲሠዉለት ሲጠይቃቸው ታዘዙ እንጂ ወደኋላ አላሉም። ለመታዘዝ የሞከሩት ነገሩ ቀላል ሆኖ አይደለም። ልጅን ያህል ነገር መስዕዋት ማድረግ ምኑ ይቀላል? የአባትነት ስሜት ይተናነቃል። የሰይጣን ሹክሹክታ ይፈታተናል። የቤተዘመድን ወቀሳ እና የጎረቤትን አስተያየት መቋቋምም ይከብዳል። ነብዩ ኢብራሒም፥ በዚህ ሁሉ አጣብቂኝ ውስጥ አንድ ሐቅ ተገልጦላቸዋል። ከራስ ስሜት፣ ከሰው ሐሜት እና ከወዳጅ ፍላጎት የሚልቅ ታላቅ ዓላማ እንዳለ አምነዋል። ስለዚህም በፈተና ውስጥ ጸንተው ቆሙ፤ ቆራጥነታቸውም በተግባር ታየ።

ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው። የሚወዱትን ነገር እንኳን ሳይቀር ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት ሀገር ትበረታለች። እስማኤላቸውን ለመስጠት የማያመነቱ ዜጎች የሞሉባት ሀገር ጽኑ ናት።

የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም “ሀገርነት እና ሉአላዊነት” ይሰኛል። ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው። ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል ነው።

የእውነት ኢትዮጵያ ሲያልፍላት ማየት የምንሻ ከሆነ ምኞታችን በተግባር ይገለጥ። የሀገር ኩስመና ካሳሰበን ለግዝፈቷ እንድከም። ያጎበጣትን የድህነት ቋጥኝ ለመሸከም ትከሻችንን እናመቻች። ጎተራዋ እንዲሞላ እጃችን አፈር ይንካ። የጠየመ ገጽዋ እንዲፈካ በሥራ ሌት-ተቀን እንሰለፍ። የተቀማ ክብሯ እስኪመለስ ድርሻችንን እንወጣ። ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዕዋት ለመሆን አናመንታ።

የዐረፋ በዓል የመታዘዝና የመስዕዋት ብቻ ሳይሆን የመደጋገፍና የመተጋገዝ በዓል ጭምር ነው። በዐረፋ ከሚከናወነው እርድ አንድ ሦስተኛው ለምስኪኖች እንዲሰጥ የእስልምና አስተምህሮ ያዛል። በዐረፋ ሕዝበ-ሙስሊሙ ደስታና ሐዘኑን እየተጋራ በዓሉን ያከብራል። የዐረፋ እለት አንድም ሰው ተከፍቶ አያሳልፍም፤ በዐረፋ ሰሞን ማንም ሰው ተርቦና ተጠምቶ አያድርም። በዓሉ ትርጉም የሚሰጠው ሕዝበ-ሙስሊሙ ያለውን ተካፍሎ ሲያከብረው ነው። ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታን የሚሻገሩበት መፍትሄው መተሳሰብና መተጋገዝ እንደሆነ ከዐረፋ እንማራለን። ሀገርም ከፈተናዎችዋ በላይ እንድትሆን እኒህ እሴቶች ወሳኝ ናቸው።

ዐረፋ ማኅበረሰባዊ በዓል የሚባለው ለዚህ ነው። ሰዎች በግላቸው የሚያከብሩት አይደለም። ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ሠፈሩ፣ ከተማው የሚያከብረው በዓል ነው። ያላቸውና የሌላቸው፤ የሚችሉና የማይችሉ፤ ታላላቆችና ታናናሾች፤ ባለ ሥልጣናትና ተራ ዜጎች፣ በአንድነት የሚያከብሩት በዓል ነው። ሰው የሚኖረው በቤቱ ውስጥ አይደለም። በማኅበረሰቡ ውስጥ ነው።

ማኅበረሰባዊ ትሥሥርና ትብብር ለዜጎች እና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ናቸው። ማኅበረሰባዊ ትሥሥር ስለሌሎች እንድናስብ፣ ስለሌሎች እንድንሠራ እና ስለ ሌሎች ዋጋ እንድንከፍል ያደርገናል። ራሳችንን በሌሎች ጫማ ላይ አቁመን እንድናይ ያስችለናል። የሁላችንም ሰላም፣ የሁላችንም ደኅንነት እና የሁላችንም ጥቅም ካልተከበረ በቀር የግላችንን ብቻ ልናስከብር እንደማንችል ያስገነዝበናል። ስለዚህም ማኅበራዊ ግዴታን እንደ ዜግነት ግዴታ ወስደን እንድንሠራ ያደርገናል።

ምርጫ ማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታዎችን ከምንወጣባቸው የዴሞክራሲ መገንቢያ መሳሪያዎች መካከል ዋነኛው ነው። ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም። የዴሞክራሲያችን መሰረት ጥንካሬው የሚለካው በተሳትፎአችን መጠን ነው።

የዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓታችን የሚጠነክርበት መሰረት ነው። የዴሞክራሲ ልምምዳችን አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት፤ የቀጣይ ዓመታት የሀገራችንን እጣ-ፈንታ የምንበይንበት፤ ከምንም በላይ ብዝሃ-ድምጽ የሚሰማበት የሕግ መወሰኛ ምክርቤት የምንመሰርትበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው። በመሆኑም በዓሉን ስናከብር ዜግነታዊ ግዴታችንን ለመወጣት ብቻ ሳይሆን በካርዳችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በድጋሚ መልካም የዐረፋ በዓል እንዲሆን እመኛለሁ!
ዒድ ሙባረክ!!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ግንቦት 18፣ 2018 ዓ.ም

በክልላችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያችን ብልፅግና በሁሉም ምርጫ ክልሎች ሲያደርግ የቆየውን የምረጡኝ የምርጫ ቅስቀሳ በዛሬው ዕለት በሁሉም መዋቅሮች በሕዝባዊ ማዕበል ታጅቦ በተደረጉ ደማቅ...
26/05/2026

በክልላችን ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲያችን ብልፅግና በሁሉም ምርጫ ክልሎች ሲያደርግ የቆየውን የምረጡኝ የምርጫ ቅስቀሳ በዛሬው ዕለት በሁሉም መዋቅሮች በሕዝባዊ ማዕበል ታጅቦ በተደረጉ ደማቅ የማጠቃለያ ቅስቀሳ እና ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በስኬት ማጠናቀቅ ችለናል፡፡

በመርሃ ግብሮቹ ፓርቲያችን በጠራ ራዕይ እየተመራ፤ ሉዓላዊነቷ በሙላት የተከበረ፤ ሁለንተናዊ ብልፅግናዋ የተረጋገጠ ተምሳሌታዊ ሀገር ለማሻገር የሰነቃቸውን ፕሮግራሞች በሰፊው ለሕዝባችን አስተዋውቀናል።
ፓርቲያችን ባለፉት ስምንት ዓመታት በተጨባጭ ቃልን በተግባር እያረጋገጠ የመጣ፤ የኢትዮጵያን የብልፅግና ጉዞ በማይቀለበስ መሠረት ላይ ያነፀ፤ በርካታ የልማት ስኬቶችን በክልላችን ያስመዘገበና የህዝብ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ መሆኑን የተረዳው ሕዝባችን ባካሄዳቸው ደማቅ የአደባባይ ሰልፎች ድጋፉን ገልፆልናል፡፡

በሁሉም የክልላችን አካባቢዎች ላካሄድናቸው ደማቅ የምርጫ ቅስቀሳ መርሃ ግብሮች ስኬት የጎላ አስትዋጽኦ ለባረከታችሁ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም በታላቅ ሕዝባዊ ማዕበል ድጋፋችሁን ለገለጻችሁልን የክልላችን ሕዝቦች በራሴና በፓርቲያችን ስም ልባዊ ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ጉዟችንን የምናፀናበት ሲሆን፤ ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፤ ፍትሃዊ፤ ነፃና ሁለንተናዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ እየጠየኩ፤ ሕዝባችን የጀመርነውን የብልፅግና ጉዞ ለማስቀጠል፤ የአንድነት የኅብረት እና የመደጋገፍ ምሳሌ የሆነውን የስንዴ ነዶን በመምረጥ የተጀመሩ ሀገር የሚያሻግሩ የልማት ተግባራት እናስቀጥል ስል ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

በክልላችን ከፍተኛ ሰብል አምራች ከሆኑ ዞኖች አንዱ በሆነው ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ በዘንድሮ በልግ በአርሶ አደሮቻችን በመልማት ላይ የሚገኝ የጤፍ ሰብል ኩታ ገጠም እርሻ።  በግብርና ልማት ዘ...
25/05/2026

በክልላችን ከፍተኛ ሰብል አምራች ከሆኑ ዞኖች አንዱ በሆነው ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ በዘንድሮ በልግ በአርሶ አደሮቻችን በመልማት ላይ የሚገኝ የጤፍ ሰብል ኩታ ገጠም እርሻ።

በግብርና ልማት ዘርፍ የታታሪ አርሶ አደሮቻችንን የቴክኖሎጂና የግብዓት አጠቃቀም በማሻሻል እና በኩታ ገጠም የማረስ ልምድን በማስፋት ምርታማነትን ከማሳደግና የምግብ ሉዓላዊነትን ከማረጋገጥ ባለፈ ግብርናን ለማሻገር ያለው ጥረት በእጅጉ ውጤታማ እየሆነ ነው፡፡
በዚህ ተግባር የተሳተፉ የትጋትና የጽናት ተምሳሌት ለሆኑ አርሶአደሮቻችን፣ በብቃት በሙያቸዉ ለደገፉ ባለሙያዎች እንዲሁም በቅርበት ለተከታተሉ እና ላስተባበሩ አመራሮች የላቀ ምስጋና ይገባችኋል።

ዘንድሮ በልግ እርሻ በክልላችን ኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ በታታሪ አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም የለማ የማሽላ ሰብል። በታታሪነታቸዉ ታዋቂ ለሆኑ የኮንሶ አርሶአደሮች፣ ያለስስት በብቃት የሙያ...
17/05/2026

ዘንድሮ በልግ እርሻ በክልላችን ኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ በታታሪ አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም የለማ የማሽላ ሰብል።

በታታሪነታቸዉ ታዋቂ ለሆኑ የኮንሶ አርሶአደሮች፣ ያለስስት በብቃት የሙያ ድጋፍ ለሰጡ ባለሙያዎች እና በትጋት ዉጤታማ ድጋፍ ለሰጡ አመራሮች ምስጋና ይገባችኋል።

Address

Hawassa
Arba Minch'
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tilahun Kebede posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Tilahun Kebede:

Share