Gammo Zone Dita Woreda Government Communication Affairs Office

Gammo Zone Dita Woreda Government Communication  Affairs Office ዲታ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት/Dita Woreda Government Communication Service Office

"ጠንካራ መንግሥትና ውጤታማ የፓርቲ አመራር ለመገንባት በዕውቀትና በክህሎት የታነፀ አባል ማፍራት ያስፈልጋል" - አቶ ገዛኸኝ ጋሞ ዛዳ፣ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም(ዲታ ወረዳ መ/ኮሚዩኒኬሽን) ...
04/09/2026

"ጠንካራ መንግሥትና ውጤታማ የፓርቲ አመራር ለመገንባት በዕውቀትና በክህሎት የታነፀ አባል ማፍራት ያስፈልጋል" - አቶ ገዛኸኝ ጋሞ

ዛዳ፣ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም(ዲታ ወረዳ መ/ኮሚዩኒኬሽን)

የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ሀሳቦችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ከመድረክ በመስጠት ተጠናቋል።

በመድረኩ በበጀት ዓመቱ የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም፣ የተመዘገቡ ጥንካሬዎች፣ የታዩ ክፍተቶችና በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ምክክር ተካሂዷል።

የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ጋሞ እንደገለጹት፣ በ2018 በጀት ዓመት የተገኙ ውጤቶች በመዋቅሮች መካከል በተደረገ የተቀናጀ ስራ የተመዘገቡ ናቸው ብለዋል።

ጠንካራ መንግሥትና ውጤታማ የፓርቲ አመራር ለመገንባት በዕውቀትና በክህሎት የታነፀ አባል ማፍራት ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል።

በተለይም ሀገራዊ ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን በማንሳት ለዚህ ውጤት አስተዋጽኦ ያደረጉ አመራሮችና የፓርቲ መዋቅሮችን አቶ ገዛኸኝ አመስግነዋል።

የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ ጽ/ቤት ፖለቲካ እና ርዕዮተ - ዓለም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ተመስገን እዩኤል በበኩላቸው፣ ዕቅዶችን ለማሳካት አፈጻጸምን በየጊዜው መገምገም፣ የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን ማስቀጠል እና ዝቅተኛ አፈጻጸም የታየባቸው ስራዎችን በቀጣይ ዕቅድ በመከለስ መስራት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

በተለይ የፓርቲ አደረጃጀቶችን ማጠናከር ፣ ጠንካራ አባል መፍጠር፣ በፓርቲ ገቢ አሰባሰብ ላይ በትኩረት መሰራት ፣ በፓርቲ በሚሰሩ እና በሌሎች ዘርፎች ላይም ትኩረት ያስፈልጋል ብለዋል።

የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አዲሱ ግርማ በምርጫው ወቅት የታየውን የቅንጅት አሰራር በቀጣይ ስራዎች በማስቀጠል የታቀዱ ግቦችን ማሳካት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በአንዳንድ መዋቅሮች የሚታዩ የመረጃ አያያዝ ክፍተቶች ሊታረሙ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በውይይቱ ሀሳብና አስተያየት የሰጡ ተሳታፊዎች የሀገራዊ ምርጫ ስኬት በዞኑ የተቀናጀ ስራ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

ተግባራትን በተሻለ አቅም ለመፈጸም መስራት እንደሚጠይቅም አመላክተዋል።

በመድረኩ በተነሱ ሀሳቦችና አስተያየቶች ላይ ማብራሪያ በመስጠት ፣ የ2018 በጀት ዓመት ግምገማ የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን በማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም ቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከስምምነት ተደርሷል።

በመጨረሻም የውል ስምምነት በመፈራረም መድረኩ ተጠናቋል ።

ከዞኑ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የማቅረብ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል - የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ(ዶ/ር)ዛዳ፣ ነሀሴ  29/2018 ዓ.ም.(ዲታ ወረዳ መ/ኮ)የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ...
04/09/2026

ከዞኑ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የማቅረብ ስራ ትኩረት ተሰጥቶታል - የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ(ዶ/ር)

ዛዳ፣ ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም.(ዲታ ወረዳ መ/ኮ)

የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ የቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም. አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም. ምርት ዘመን የህገ-ወጥ ቡና ምርት ግብይት ቁጥጥር ግብረ-ኃይል የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ(ዶ/ር) በመድረኩ እንደገለፁት፣ የቡናና ቅመማቅመም ምርት ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።

በዞኑ ከማሳ እስከ ግብይት ጥራት ያለውን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ከማቅረብ አኳያ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በመሆኑም ዘርፉን በማሻሻል ትልቅ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

አርሶ አደሮች በኩታ ገጠም የእርሻ ሥራ እንዲሰሩ በማድረግ እና የቡና ችግኝ ከማዘጋጀት ጀምሮ በትኩረት የተሠራ መሆኑን የተናገሩት ደምሴ አደሰማሱ(ዶ/ር) ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አብራርተዋል።

በሌላ በኩል ህገ-ወጥ የቡና ግብይት የመቆጣጠር ሥራ ይጠናከራል ብለዋል።

ቡና ማቀነባበር እና የማጠብ ሥራ ከወረዳ አስከ ቀበሌ በተቀናጀ ሁኔታ ይሰራል ሲሉም አክለዋል።

የጋሞ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ማገሶ ማሾሌ በበኩላቸው፣ ቡና በሀገር ኢኮኖሚ እያበረከተ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

አክለውም ለኢሊኖ ክስተት የማይበገር ሥነ-ምህዳር በመፍጠር የቡና ምርታማነት ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

በዞን በ2017 ምርት ዘመን 24,993 ሄክታር የነበረው የቡና ማሳ ሽፋን በ2018 ምርት ዘመን 28,274 ሄክታር ማድረስ መቻሉን ተናግረዋል።

በምርት ዘመኑም 3,281 ሄክታር መሬት ላይ አዲስ የቡና ተከላ ታቅዶ ሙሉ በሙሉ ማከናወን መቻሉን አብራርተዋል።

በመምሪያው የቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሻምበል ቦኩ ለቡናና ቅመማ ቅመም ምርት በተሰጠው ትኩረት የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

በመድረኩ የዞን እና ወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

04/09/2026

ጋሞ ዞን በዲታ ወረዳ የ2018 ዓ.ም ስኬቶችን በከፍል እናስታዉስ፦

በብልፅግና ፓርቲ የጋሞ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት “በላቀ ትጋት ለላቀ ስኬት” በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የ2019 ዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ ማካሄድ ጀመረዛ...
04/09/2026

በብልፅግና ፓርቲ የጋሞ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት “በላቀ ትጋት ለላቀ ስኬት” በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የ2019 ዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ ማካሄድ ጀመረ

ዛዳ፣ ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም(ዲታ ወረዳ መ/ኮ )

በብልፅግና ፓርቲ የጋሞ ዞን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት “በለቀ ትጋት ለላቀ ስኬት” በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማና የ2019 ዕቅድ ኦሬንቴሽን መድረክ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

መድረኩ በ2018 ዓ.ም በፓርቲው የተከናወኑ የፖለቲካ፣ የአደረጃጀትና የሕዝብ ተሳትፎ ሥራዎችን በጥንካሬና በጉድለት አጣጥሞ ለመገምገም፣ የተገኙ ስኬቶችን ለማጠናከር እና በቀጣይ የሥራ ዘመን ሊሻሻሉ የሚገባቸውን አቅጣጫዎች ለመለየት ያለመ ነው።

በግምገማው መድረክ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም በመረጃና በማስረጃ ላይ በመመስረት የሚፈተሽ ሲሆን፣ በተለይም የፓርቲ አደረጃጀትን ማጠናከር፣ የአባላትንና የደጋፊዎችን ተሳትፎ ማሳደግ፣ ከሕዝብ ጋር ያለውን ትስስር ማጠናከር እና የተሰጡ የፖለቲካ አቅጣጫዎችን በተግባር ማስፈጸም ዙሪያ ትኩረት ይደረጋል።

በተጨማሪም የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ኦሬንቴሽን በ2018 ዓ.ም ከተገኙ ልምዶችና ውጤቶች በመነሳት የቀጣዩን ዓመት የፖለቲካና የአደረጃጀት ሥራዎች በግልጽ ቅድሚያና በተግባር ተኮር አቅጣጫ ለመምራት የሚያስችል የሥራ መርሃ ግብር ይቀመጥበታል።

“በላቀ ትጋት ለላቀ ስኬት” የሚለው መሪ ቃልም የተገኙ ውጤቶችን በማስጠበቅ በቀጣይ የሥራ ዘመን የበለጠ ተጨባጭ፣ ውጤታማና ተጠያቂነት ያለው የፓርቲ ሥራ ለማስፈን የሚያስችል የትጋት እና የስኬት አቅጣጫን ያመላክታል።

መድረኩ በ2018 ዓ.ም የተገኙ ውጤቶችን የሚያጠናክር፣ የአፈጻጸም ክፍተቶችን የሚያርም እና የ2019 ዓ.ም የፓርቲ ሥራን ወደ የተሻለ ውጤት ለማሸጋገር በተግባር የሚውሉ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀመጥ ይጠበቃል።

በመድረኩ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምስ አድማሱ፣ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ ጋሞ፣ አቶ ሃኪሜ አየለ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ምክትል አስተዳዳሪና የዞኑ የሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ፣ አቶ ተመስገን ኢዩኤል የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ፣ አቶ አዲሱ ግርማ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊን ጨምሮ የዞን ማዕከል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አመራሮች የወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ፓርቲ አመራሮች ተገኝተዋል።

04/09/2026
በሰንበት ገበያ ተመጣጣኝ ዋጋ!የጋራ ተጠቃሚነት ለተሻለ ኑሮና ለገበያ እርጋታ!ዛዳ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም(ዲታ ወረዳ መ/ኮ)፦ ጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ በዛዳ ከተማ ለዓመት በዓል የሚህን ነጭ ...
04/09/2026

በሰንበት ገበያ ተመጣጣኝ ዋጋ!
የጋራ ተጠቃሚነት ለተሻለ ኑሮና ለገበያ እርጋታ!

ዛዳ፣ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም(ዲታ ወረዳ መ/ኮ)፦

ጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ በዛዳ ከተማ ለዓመት በዓል የሚህን ነጭ እና ቀይ ሽንኩርት በሰንበት ገበያ በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ ይገኛል።

ሰንበት ገበያ የሸማቹን አቅም በማገናዘብ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ ከማህበረሰቡ ጋር የሚያገናኝ፣ የኑሮ ውድነትን ለማቅለል የጋራ መፍትሄ የሚፈጥር ተግባር ነው።

በብልፅግና እሳቤ የሚንገነባው ልማት የአንዱን ብቻ ተጠቃሚነት ሳይሆን፣ አምራቹ፣ ነጋዴው እና ሸማቹ በጋራ የሚያተርፉበትን የጋራ ተጠቃሚነት ያለመ ነው።

ሰንበት ገበያም ይህንን እሳቤ በተግባር በማሳየት፣ የገበያ ትስስርን በማጠናከር፣ ተመጣጣኝ ዋጋን በማስፋፋት እና የሸማቹን አቅም በመጠበቅ የተሻለ የኑሮ ሁኔታን ለመፍጠር ያግዛል።

ስለሆነም ኑ በተመጣጣኝ ዋጋ ይግዙ የአንድ ኪሎ ዋጋ ከ80 እስከ 100 መቶ ብር በየጥራቱ ደረጃ ነው።

አድራሻ፦ ለፍት

ሰንበት ገበያ ተመጣጣኝ ዋጋ፣ የጋራ ተጠቃሚነት፣ የተሻለ ኑሮ።

"የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የጳጉሜን ወር አከባበር ላይ የጋሞ ዞን አጠቃላይ አመራሮች ተወያዩዛዳ: ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም (ዲታ ወረዳ መ/ኮሙኒኬሽን)የጋሞ ዞን ማዕከል አጠቃላ...
03/09/2026

"የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የጳጉሜን ወር አከባበር ላይ የጋሞ ዞን አጠቃላይ አመራሮች ተወያዩ

ዛዳ: ነሀሴ 28/2018 ዓ.ም (ዲታ ወረዳ መ/ኮሙኒኬሽን)

የጋሞ ዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራሮች የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ወር አከባበርን አስመልክተው የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

በውይይቱ የዘንድሮው የጳጉሜን ወር “የኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ-ግብሮች በድምቀት እንዲከበር የተዘጋጀው የማስፈጸሚያ ዕቅድ ቀርቦ የአፈጻጸም አቅጣጫዎች ላይ ውይይት ተደርጓል።

ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት የሚያሻግር የሽግግር ወቅት በመሆኑ፣ ያለፈውን ዓመት ሥራና ውጤት ለመገምገም፣ የተገኙ ስኬቶችን ለማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን ለማረምና ለቀጣዩ ዓመት የተሻለ የሥራ አቅጣጫ ለመቀመጥ ወሳኝ መድረክ መሆኑ ተገልጿል።

በውይይቱ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት በተለያዩ ዘርፎች ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች በመዘከር፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በጽናት፣ በፈጠራና በተቀናጀ ጥረት በመሻገር ወደ ማንሰራራት ምዕራፍ እየተሸጋገረች መሆኗ ተጠቁሟል።

የዘንድሮው የጳጉሜን አከባበርም ያሉ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል፣ የታዩ ክፍተቶችን በማረም፣ የፈጠራ ሥራዎችን በማበረታታትና የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ በመጠቀም የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስታወስና አዳዲስ ብሥራቶችን ለማብሰር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይም የ2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ በማተኮር እንደሚከበር በቀረበው የማስፈጸሚያ ዕቅድ ተመላክቷል።

በዚህም መሠረት፦

• ጳጉሜን 1 – የእምርታ ቀን

• ጳጉሜን 2 – የማንሰራራት ቀን

• ጳጉሜን 3 – የጽናት ቀን

• ጳጉሜን 4 – የኅብር ቀን

• ጳጉሜን 5 – የነገ ቀን

በሚሉ የተለያዩ መርሃ-ግብሮች የጳጉሜን ቀናት በልዩ ሁነቶችና በማንቀሳቀስ መርሃ-ግብሮች እንደሚከበሩ ተገልጿል።

በመድረኩ የተሳተፉት የጋሞ ዞን አጠቃላይ አመራሮችም የጳጉሜን ወር መርሃ-ግብሮች የሀገራዊ ማንሰራራት መልዕክትን በማጠናከር፣ የህዝብ ተሳትፎን በማሳደግና የተመዘገቡ ስኬቶችን ወደ ተጨባጭ ተስፋ በመቀየር እንዲከናወኑ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

“የኢትዮጵያ ማንሰራራት” የሚለው መሪ ቃልም ያለፈውን ለመዘከር ብቻ ሳይሆን፣ የተገኙ ውጤቶችን በማስቀጠል የተሻለ ነገን ለመገንባት የሚያነሳሳ የሀገራዊ ተስፋ፣ የጽናትና የትብብር መልዕክት መሆኑ ተጠቁሟል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን 5ቱ የጳጕሜን ቀናት በተለያዩ የመንግሥትና የሕዝብ መርሐ ግብሮች በድምቀት ይከበራሉዛዳ፦ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ዲታ ወረዳ መ/ ኮሙኒኬሽን)​የቀናቱን አከ...
03/09/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን 5ቱ የጳጕሜን ቀናት በተለያዩ የመንግሥትና የሕዝብ መርሐ ግብሮች በድምቀት ይከበራሉ

ዛዳ፦ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም (ዲታ ወረዳ መ/ ኮሙኒኬሽን)

​የቀናቱን አከባበር አስመልክቶ የጋሞ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት ቦዳ መግለጫ ሰጥተዋል።

​የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

​ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶችን በፅናት በመሻገር በአሁኑ ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ።

​ዞናችን ጋሞም ባለፉት ዓመታት ውስጥ ሁለንተናዊ ለውጦችን በማስመዝገብ በዚህ የማንሠራራት ምዕራፍ ውስጥ ግንባር ቀደም ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡

​የጳጕሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር ውስጥ ወደ አዲስ ዓመት የምንሸጋገርበት ድልድይ እንደመሆኑ መጠን፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ አንኳር ስኬቶችን በመዘከር የምንደምርበት፣ ክፍተቶችን ደግሞ በማረም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋን የምንሰንቅበት መለያችን ነው፡፡

​የ2018 ዓ.ም የጳጕሜን ቀናት አከባበር ሀገራችን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ይሁንታ ያገኘው ፓርቲ መንግሥት የሚመሠርትበት፣ የተመረጠው መንግሥት የተጣለበትን አደራ ለመወጣት በሚዘጋጅበት፣ እንዲሁም ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ውጤቶችን ወደ ትግበራ ለማስገባት ጠንካራ ዝግጅት በሚደረግበት ታሪካዊ ወቅት የሚከበር በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

​ይህንን ታላቅ ሀገራዊና ዞናዊ ንቅናቄ በብቃት ለመምራት በዞን ደረጃ ዐቢይና ንዑሳን ኮሚቴዎች ተደራጅተው ወደ ሙሉ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተገብቷል።

​የጳጕሜን ቀናትን በዞናችን በታቀደው መሠረት በንቅናቄ ለማክበር የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ እስከ ታችኛው የመንግሥትና የወረዳ መዋቅር የወረደ ሲሆን አምስቱም ቀናት በተሰጣቸው ልዩ ስያሜዎችና መሪ መልእክቶች መሠረት እንደሚከተለው የሚከበሩ ይሆናል።

​ጳጕሜን 1 “የእምርታ ቀን” በዞናችንና በየደረጃው በሚገኙ መዋቅሮች የተመዘገቡ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ስኬቶች፣ የምግብ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ረገድ የተመዘገቡ ድሎች እና የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ውጤቶች ይጎላሉ፡፡ ሀገራችንና ዞናችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያደረጉት ያለውን መዋቅራዊ ሽግግር የሚያመላክቱ ሥራዎች በግንባር ቀደምትነት ይከወናሉ፡፡

​ጳጕሜን 2 “የማንሠራራት ቀን”፦ በየደረጃው የተመዘገቡ የልማትና የመሠረተ ልማት ውጤቶች በዜጎች ዕለታዊ ሕይወት ላይ ያመጡትን አዎንታዊ ለውጦች ማሳየትና የኢትዮጵያንና የጋሞ ዞንን የማንሠራራት ዘመን የሚያበስሩ የይዘት ሥራዎች ትኩረት ይሰጣቸዋል፡፡

​ጳጕሜን 3 “የጽናት ቀን”፦ የፀጥታ መዋቅራችንን ዘመናዊ ቁመና፣ በሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ ያደገበትን አቅም ማሳየትና ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ለሕዝብ ሰላም የተከፈለውን የጀግኖች መስዋዕትነት በመዘከር ይከበራል።

​ጳጕሜን 4 “የኅብር ቀን”፦ በለውጡ ዓመታት በተደረጉ ሪፎርሞች የተገኙ የብዙኃን አካታችነት ስኬቶች፣ ሀገር በቀል እሴቶች፣ የወል ትርክት ግንባታ ሂደቶች እንዲሁም የጋሞ ህዝቦችን ህብረ-ብሔራዊ አንድነት፣ አብሮነትና በጎ አድራጎት የሚያጎሉ ሁነቶችና የሚዲያ ይዘቶች ይቀርባሉ፡፡

​ጳጕሜን 5 “የነገው ቀን”፦ የሀገራችንን የዲጂታላይዜሽን ጉዞ፣ የሳይበር ሉዓላዊነትን፣ የ“መሶብ” ለአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የ“5 ሚሊዮን ኢትዮ-ኮደርስ” ስኬቶችን በማሳየት፤ ዲጂታል ቴክኖሎጂ የነገዋን ከፍታ የሚወሰን ዋና አቅም መሆኑን የሚያመላክቱ ሥራዎች ይከናወናሉ፡፡

​መላው የጋሞ ዞን ሕዝቦች፣ ወጣቶች፣ የፀጥታ አካላትና የመንግሥት ሠራተኞች የጳጕሜን ቀናት አከባበርን የተቀደሱ እሴቶቻችንን በማጎልበት፣ አብሮነታችንን በማጠናከርና ለነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ በጋራ በመቆም በደማቅ ሁኔታ እንድታከብሩ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

​ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረትና ትጋት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!

​መልካም የጳጕሜን ቀናትና የአዲሱ ዓመት የመሸጋገር በዓል ይሁንልን!

​ወ/ሮ ሰላማዊት ቦዳ
​የጋሞ ዞን መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ

የጋሞ ዞን የልማት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት ዙሪያ የአማካሪ ቡድን ውይይት ተጀመረዛዳ፣ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (ዲታ ወረዳ መ/ኮሙኒኬሽን)የጋሞ ዞን የልማት ፍኖተ ካርታ ዝግጅትን በተመለከተ የአ...
02/09/2026

የጋሞ ዞን የልማት ፍኖተ ካርታ ዝግጅት ዙሪያ የአማካሪ ቡድን ውይይት ተጀመረ

ዛዳ፣ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (ዲታ ወረዳ መ/ኮሙኒኬሽን)

የጋሞ ዞን የልማት ፍኖተ ካርታ ዝግጅትን በተመለከተ የአማካሪ ቡድን የመጀመሪያ ዙር ውይይት እያኳሄደ ይገኛል።

ውይይቱ የክልል፣ የጋሞ ዞንና የአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዞኑ ምሁራንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄደ ነው።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ የውይይት መድረኩን በከፈቱበት ወቅት የጋሞ ዞንን የልማት አቅም በሚገባ በመለየትና በማስተባበር የዞኑን እንዲሁም የአርባ ምንጭ ከተማን የልማት ደረጃ ለማሳደግና የሕዝቡን ተጠቃሚነት በየደረጃው ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ተገልጿል።

በውይይቱ ላይ የዞኑ ምሁራን እውቀትና ሙያዊ ልምድ በማቀናጀት ለዞኑ ዘላቂ የልማት አቅጣጫ መቀመጥ እንደሚገባ ተመልክቷል።

የሚዘጋጀው የልማት ፍኖተ ካርታ የጋሞ ዞንን የልማት አቅም በመጠቀም ዘላቂ የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚያግዝ ሲሆን፣ ለሚቀጥሉት 25 ዓመታት የዞኑን የልማት አቅጣጫ የሚያሳይ ሰነድ እንደሚሆን ዶ/ር ደምሴ ገልፀዋል።

በዚህም የዞኑን ሀብትና አቅም በሙሉ በመጠቀም፣ የልማት እንቅፋቶችን በመለየትና ተገቢ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የተቀናጀና ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ ለማዘጋጀት እንደሚሠራ ተመልክቷል።

ጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ገቢ አሰባሰብና ደረሰኝ ቁጥጥር፣ ጤናማ የንግድ ሥርዓት እና ፍትሃዊ የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ ዙሪያ ከባለድርሻዎች ጋር ውይይት አካሄደ።ዛዳ፣ ነሐሴ 27...
02/09/2026

ጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ገቢ አሰባሰብና ደረሰኝ ቁጥጥር፣ ጤናማ የንግድ ሥርዓት እና ፍትሃዊ የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ ዙሪያ ከባለድርሻዎች ጋር ውይይት አካሄደ።

ዛዳ፣ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም(ዲታ ወረዳ መ/ኮ)፦

በጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ገቢ አሰባሰብና ደረሰኝ ቁጥጥር፣ለጤናማ የንግድ ሥርዓት እና ለፍትሃዊ የታክስ አወሳሰንና አሰባሰብ ዙሪያ ከባለድርሻዎች ጋር ውይይት አካሂዷል።

‎በውይይት መድረኩ የዲታ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ቦጋለ እንደገለጹት ግብር ከፋዮች ለሚያከናውኑት ማንኛውም ግብይት ሕጋዊ ደረሰኝ መስጠት ግዴታ ከመሆኑ ባሻገር፣ ለፍትሐዊ የንግድ ውድድርና ለአገራዊ ልማት የሚደረግ አስተዋፅዖ መሆኑን ተረድተው ደረሰኝ እንዲቀሳሸሱ አሳስበዋል።

ደረሰኝ ክፊያን የሚያረጋግጥ ሕጋዊ ማስረጃ ከመሆኑም በላይ ግልጽነትን ለማስፈንና የግብር ገቢ በትክክል እንዲመዘገብ የሚያግዝ ነው ብለዋል።

‎ህብረተሰቡም ደረሰኝ በመስጠት፣ በመቀበል እና ያለደረሰኝ ወይም በሐሰተኛ ደረሰኝ የሚካሄዱ ሕገ-ወጥ ግብይቶችን በመከላከልና በመጠቆም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርግም
ተጠቁሟል።

‌‎በየደረጃው የሚገኙ የገቢ ተቋማትም ደረሰኝ በማይሰጡ አካላት ላይ ጥብቅ ክትትል በማድረግ በሕግ መሠረት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስዱ ተቀምጧል።

የዲታ ወረዳ ዛዳ ከተማ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ ኢንጂነር በቀለ መዝገቡ በበኩላቸው ማዘጋጃ ቤቶች ለህዝቡ የሚታይ ለውጥ ለማምጣት በተናበበ መልኩ በገቢ አሰባሰብ ላይ በልዩ ትኩረት መስራት፣ የተሰበሰበውን ገቢና በጀት ለታለመለት ዓላማ በብቃት መጠቀም እንዲሁም ህዝብን ያማከለና በአካባቢው የሚታይ ልማት ለማምጣት ቁርጠኛ ሆነው መስራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

‎አክለውም የከተማ መሬትን በሊዝ በመስጠት የከተሞችን የልማት አቅም ማሳደግና አካባቢዎችን ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ ማድረግ ላይ ልዩ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎ጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢያሱ አፃ እንዲሁም የደረሰኝ አሰጣጥና አቀባበል ሥርዓትን ለማስጠበቅ ክትትሉ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል አስቀምጠው፣ ቀደም ሲል ግንዛቤ ከተሰጠ በኋላ ደረሰኝ የማይቆርጡ አካላት ላይም በሕጉ መሠረት እርምጃ እንደሚወሰድ አመልክተዋል።

‎በተጨማሪም፣ ለእያንዳንዱ ሽያጭ ተገቢው ደረሰኝ መቆረጥ እንዳለበት በመጠቆም፣ ህብረተሰቡ ደረሰኝ ሳይቀበል ክፍያ እንዳይፈጽም አስገንዝቦ የከተማ ቦታ የ2019 ግብር የመጠናቀቀው እስከ ጳጉሜ ድረስ መሆኑን ከተማ ነዋሪዎች አውቆያለ ቅጣት እንድከፊሉ አሳስበዋል።

‎በመድረኩ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የዲታ ወሰዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ባለሙያዎች ተሳትፈዋል ።

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gammo Zone Dita Woreda Government Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gammo Zone Dita Woreda Government Communication Affairs Office:

Shortcuts

Share