Gamo Zone Prosperity Party - የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ

Gamo Zone Prosperity Party - የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጤና ይስጥልን! ይህ የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው፡፡

"የክልሉ ቤተ መንግስት መላው የክልላችንን ህዝብ ሊወክል እና ሊመጥን በሚችል መልኩ ተገንብቷል"-  ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደጳጉሜን 02/2018 ዓ.ምግንባታው በዘጠኝ ወራት ዉስጥ የተጠ...
07/09/2026

"የክልሉ ቤተ መንግስት መላው የክልላችንን ህዝብ ሊወክል እና ሊመጥን በሚችል መልኩ ተገንብቷል"- ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም

ግንባታው በዘጠኝ ወራት ዉስጥ የተጠናቀቀው የክልሉ መንግስት ቤተ-መንግስት ተመርቆ በክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተጎብኝቷል።

በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የቤተ መንግስት ግንባታው መላው የክልሉን ህዝብ ሊወክል እና ሊመጥን በሚችል እንዲሁም ባህላዊን ከዘመናዊ ዲዛይን ባጣመረ መንገድ ተግንብቶ መጠናቀቁን ተናግረዋል።

የክልሉ መንግስት የተቋማት የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ መጠናቀቅ ክልሉን በፅኑ መሠረት ላይ ከማኖር ባለፈ፤ በስድስቱም ክላስተር ማዕከላት የተቋማት ህንፃ ግንባታዎችን በማስጀመር ግንባታቸው በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ በትኩረት መስራት ይገባል ብለዋል።

ግንባታው በዘጠኝ ወር ተጠናቆ ለዚህ እንዲበቃ የብዙዎች እጅ ያረፈበት መሆኑን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ ለአንጆ ኑስ ኮንስትራክሽን ፣ ለክልሉ ግንባታ እና ዲዛይን ቁጥጥር ባለስልጣን፣ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን እንዲሁም እገዛ ላደረጉ አካላት በሙሉ የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

በመጨረሻም የቤተ መንግስቱን ምረቃ ምክንያት በማድረግ ለክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ ከወላይታ ዞን እና ከወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር የክብር ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።


ባመረ መልኩ በተጠናቀቀው የክልሉ ቤተ-መንግስት የጉብኝት እና የእራት መረሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛልበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ የክልል ተቋማት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት አካል በፍጥነትና በጥራ...
07/09/2026

ባመረ መልኩ በተጠናቀቀው የክልሉ ቤተ-መንግስት የጉብኝት እና የእራት መረሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፤ የክልል ተቋማት ህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት አካል በፍጥነትና በጥራት ተገንብቶ ባማረ መልኩ በተጠናቀቀው የክልሉ ቤተ-መንግስት ለክልሉ አመራሮች የተዘጋጀ የጉብኝት እና የእራት መርሃ ግብር በቤተ-መንግስት ቅጥር ግቢ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

የክልሉ መንግስት የተቋማት የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ መጠናቀቅ ክልሉን በፅኑ መሠረት ላይ ከማኖር ባለፈ ካለው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አኳያ፤ በስድስቱም ክላስተር ማዕከላት የተቋማት ህንፃ ግንባታዎችን በማስጀመር ግንባታቸው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆኑ በትኩረት በመስራት ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የተጀመሩ የህንፃ ግንባታዎች በፍጥነት መጠናቀቅ የክልሉን ተቋማት ተቋማዊ አቅም በማጠናከር፤ የተጀመረውን የማንሰራራት ስኬታማ ጉዞ በተሻለ አገልግሎት እንዲሁም የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም ክልላዊና ሀገራዊ የዘላቂ ልማት ግቦችንና የሁለንተናዊ ብልጽግና ትልሞችን ከግብ በማድረስ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናቸው ከፍተኛ ነው፡፡

የዚሁ አካል በወላይታ ሶዶ ማዕከል በግንባታ ላይ ከነበሩ የተቋማት የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የክልሉ ቤተ-መንግስት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ተገንብቶ በስኬት የተጠናቀቀ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት የክልሉ መንግስት የ2018 ዓ.ም የከፍተኛ አመራሮች የማጠቃለያ መድረክ መጠናቀቁን ተከትሎ የጉብኝትና የእራት መርሃ ግብር መዘጋጀቱ ታውቋል፡፡

መርሃ ግብሩ በኃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የጸሎትና ምርቃት በይፋ የሚጀመር ሲሆን፤ ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩም በመርሃ ግብሩ መልዕክት ያስተላልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም የጉብኝትና የእራት ግብዣን ጨምሮ ስለ ቤተ-መንግስት ህንፃ ፕሮጀክቱ እና ስለግንባታው ሂደት ማብራሪያ በማቅረብ ሌሎች በግንባታ ላይ ያሉ የክልል ተቋማት ህንፃ ግንባታዎችን በፍጥነትና በጥራት ገንብቶ ለማጠናቀቅ ተሞክሮ ይወሰድበታል ተብሎም ይጠበቃል፡፡

በመርሃ ግብሩ ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ገ/መስቀል ጫላ፤ የክልሉ አስተባባሪ አካላት፤ አፈ ጉባዓዎች፤ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፤ የዞንና የፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከፍተኛ አመራሮች፤ የረ/ፖ/ከተማ ከንቲቦችን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡


እንኳን ደስ ያለን!!ዞናችን በ2018 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ኢንሸትቪ አፈጻጸም ከ12 ዞኖች 2ኛ ወጥተናል። የዋንጫ የመኪናና ላፕቶፕ ሽልማት ከክቡር ፕሬዚዳንታችን ከክቡር አቶ ጥላሁን እጅ ...
07/09/2026

እንኳን ደስ ያለን!!

ዞናችን በ2018 በጀት ዓመት የአጠቃላይ ኢንሸትቪ አፈጻጸም ከ12 ዞኖች 2ኛ ወጥተናል። የዋንጫ የመኪናና ላፕቶፕ ሽልማት ከክቡር ፕሬዚዳንታችን ከክቡር አቶ ጥላሁን እጅ ተቀብለናል። ከተማችን አርባምንጭም ከሦሥቱ ሪጂዮ ፖሊ ከተሞች አንደኛ ወጥቷል። የሥራ ውጤትን መዝኖ መሸለም ለበለጠ ስራ ያነሳሳናል እናመሠግናለን።

ለዚሁም ስኬት ያበቃን የሁሉ ፈጣሪ የሆነውን እግዚአብሔር አመሠግናለሁ!

በመቀጠልም የዞናችን እንዲሁም በወረዳና ከተማ አስተዳደር የምትገኙ አመራሮች ሰራተኞችና የህዝባችን የጋራ ቅንጅትና ትብብር በመቀባበል ተደምረን በመሥራታችን የተመዘገበ ውጤት በመሆኑ እንኳን ደስ ያለን!!

ዶ/ር ደምሴ አድማሱ
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ


በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የስራ አፈፃፀሞ ያስመዘገቡ ተቋማት ፣ ዞኖች እና የሪጂዮ ፖሊስ ከናተሞች  እውቅናና ሽልማት ተሰጣቸውበክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኢኒሼቲቮች...
07/09/2026

በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የስራ አፈፃፀሞ ያስመዘገቡ ተቋማት ፣ ዞኖች እና የሪጂዮ ፖሊስ ከናተሞች እውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው

በክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኢኒሼቲቮች ተሻለ የተግባር አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት መድረኩ ዕውቅና ተሰጥቷል።

* የክልሉ ገቢዎች ቢሮ እና የወላይታ ፣ ጋሞ እና ጌዴኦ ዞኖች በላቀ አፈፃፀም የሚኪና ተሸላሚ ሆነዋል።

* ከክልል ቢሮዎች ከፍተኛ አፈፃፀም የስመዘገቡ
የክልሉ ፍትህ ቢሮ፣ ፋይናንስ ቢሮ፣ ፕላን ቢሮ ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ ጤና ቢሮ፣ መስኖና ቆላማ ቢሮ፣ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ፣

* ከዞን መዋቅሮች:- ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ የመኪና እና ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የተሸልመዋል ፡- 1ኛ ወላይታ ዞን 2ኛ ጋሞ ዞን 3ኛ ጌዴኦ ዞን፣ ተሸላሚ ሆነዋል።

*ከሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች ፡- ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ የሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች 1ኛ- አርባምንጭ ከተማ 2ኛ- ወላይታ ሶዶ ከተማ 3ኛ ዲላ ከተማ አስተዳደር ተሻላሚ ሆነዋል ።

* እንዲሁም ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ጎፋ ፣ አሪ ፣ ደቡብ ኦሞ ፣ ኮንሶ፣ ባስኬቶ እና ጋርዱላ ዞን አስተዳደር ተሸላሚ ሆኖዋል።

በመድረኩ ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም ጅምር አፈፃፀም ላስመዘገቡ አሌ ፣ ኮሬ እና ቡርጂ ዞን ተሸልመዋል።

የእውቅናው መስፈርት በግብርና ልማት ፣ ከተማና መሰረተ ልማት ፣ ትምህርት ልማት ፣ ጤና ልማት፣ ቱሪዝም ልማት፣ ንግድ ኢንደስትሪ ልማት ፣ ገቢ ንቅናቄ፣ ስራና ክህሎት እንዲሁም የዲጂታላይዘሽን ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ኢኒሼቲቮችን ትኩረት ያደረገ መሆኑን የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ ቦሻ ቦንቤ ( ዶ/ር ) የምዘና መስፈርቱን ባብራሩበት ወቅት ገልፀዋል።

መድረኩ ተቋማት ከክቡር ርዕሰ መስነዳድሩ ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረምም ተጠናቋል።


" ቃርቻ " ዘመናትን የተሻገረ ቱባ ባህል፣ የኃላፊነትና የትውልድ ቅብብሎሽ ማሳያቃርቻ በጋሞ ዞን ቆጎታ ወረዳ በየዓመቱ በወርሃ መስከረም የዮ ማስቃላ የዘመን መለወጫ በዓል መቃረቡን ተከትሎ ...
07/09/2026

" ቃርቻ " ዘመናትን የተሻገረ ቱባ ባህል፣ የኃላፊነትና የትውልድ ቅብብሎሽ ማሳያ

ቃርቻ በጋሞ ዞን ቆጎታ ወረዳ በየዓመቱ በወርሃ መስከረም የዮ ማስቃላ የዘመን መለወጫ በዓል መቃረቡን ተከትሎ የሚከበር ከዘመናት የተሻገረ ቱባ ባህላዊ ኩነት ነው።

በዚህ ክብረ በዓል ዘጠኝ ያላገቡ ወንድ ታዳጊዎች፣ የዶርቦ ካሎ ልጆች፣ ዮ ማስቃላ መድረሱን ለማብሰር ረዥም ርቀት ተጉዘው ይመለሳሉ። በነብር ለምድ፣ በድንጉዛና በኩታ አጊጠው፣ ረጃጅም የቀርከሃ አመልማሎችን ይዘው በየአካባቢው በመዞር የዮ ማስቃላ መድረሱን ያበስራሉ።

ይህ ሂደት በዓልን ብቻ ማብሰር ሳይሆን፣ ባህልን ከአንድ ትውልድ ወደሚቀጥለው የማስተላለፍ፣ የኃላፊነትን ስሜት ከልጅነት ጀምሮ የማሳደግና የጋራ እሴትን የማጠናከር ማህበራዊ ሥርዓት ነው።

ከለጋ ዕድሜያቸው ጀምሮ የአካባቢያቸውን ወግ፣ ሥርዓት፣ ባህልና ትውፊት ተምረው የሚያድጉት የካሎ ልጆች፣ በቃርቻ ዕለት ባህላዊ ኃላፊነታቸውን ተወጥተው ዮ ማስቃላ መቃረቡን ለሚጠባበቀው ማህበረሰብ የምስራች ያበስራሉ።

የቃርቻ ልዩነቱ የሚገለጠው በባህላዊ ውበቱ ብቻ ሳይሆን፣ በውስጡ በተደራጀ መልኩ የተቀመጠው የኃላፊነት ክፍፍልና የመሪነት ሥርዓት ጭምር ነው።

1. ኡንዱሮ (Undduro) ለአንድ ልጅ ብቻ የሚሰጥ ማዕረግ ሲሆን፣ ኃላፊነቱ ኡንዱሮውን በክብር መጠበቅ ነው። ይህ ማዕረግ በትዳር መያዝ ያበቃል። በዚህም የኃላፊነት ጊዜያዊነትና ሥልጣን የግል ንብረት እንዳልሆነ የሚያሳይ ጠንካራ ባህላዊ መርህ ይታያል።

2. ካሶ (Kaaso) ለሁለት ልጆች ብቻ የሚሰጥ ማዕረግ ሲሆን፣ ባይራ ካሶ እና ካሎ ካሶ በመባል ይጠራሉ። የአገልግሎት ጊዜያቸውም ሁለት ዓመት ነው። ይህም ኃላፊነት በጊዜ የሚመዘን፣ በተራ የሚሸጋገርና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ መሆኑን ያሳያል።

3. ወጾሎ (Woxolo) የሚባሉት ስድስት የዶርቦ ካሎ ልጆች ሲሆኑ፣ የአገልግሎት ዘመናቸው አንድ ዓመት ነው። ገብስ ማሰባሰብ፣ በሬ መጠበቅና ባይራዎችን ማስተባበር የሥራ ድርሻቸው ነው። እዚህ ላይ የሚታየው የግል ጥቅም ሳይሆን ለማህበረሰብ የመስራት፣ የመተባበርና የተሰጠንን ኃላፊነት በታማኝነት የመወጣት እሴት ነው።

ስለዚህ ቃርቻ ባህል የሚያሳየው ዮ ማስቃላ መድረሱን ማሳወቅ ብቻ ሳይሆን፣ ኃላፊነትን መረከብ፣ በተራ ማስተላለፍ፣ ማህበረሰብን ማገልገልና ትውልድን ማስተማር የሚሉ እሴቶችን በተግባር የሚያሳይ ቱባ ባህላዊ ተቋም ነው።

ዛሬ በልማትና በሰላም ግንባታ የምንፈልጋቸው የጋራ ኃላፊነት፣ የትውልድ ቅብብሎሽ፣ የመሪነት ተጠያቂነትና የማህበረሰብ ትብብር መርሆች በባህላችን ውስጥ ከዘመናት ጀምሮ መኖራቸውን ቃርቻ ያስተምረናል።

ቃርቻ የዮ ማስቃላን መድረስ የሚያበስር ብቻ አይደለም፤ ባህል ከትውልድ ወደ ትውልድ፣ ኃላፊነት ከአንድ ትከሻ ወደ ሌላ ትከሻ የሚሸጋገርበት የጋሞ ህዝብ ቱባ ባህላዊ መድረክ ነው።




07/09/2026
ኢትዮጵያ ትፈርሳለች፤ ክልሉ ይፈርሳል የሚሉ ሟርተኞች እና ሀሜቶች ራሳቸው ይፈርሳሉ እንጂ በፅኑ መሰረት ላይ ቆመን፤ ከህዝባችን ጋር በጋራ ተግተን ሰርተን፤ ደቡብ ኢትዮጵያንም ሆነ ሀገራችንን...
07/09/2026

ኢትዮጵያ ትፈርሳለች፤ ክልሉ ይፈርሳል የሚሉ ሟርተኞች እና ሀሜቶች ራሳቸው ይፈርሳሉ እንጂ በፅኑ መሰረት ላይ ቆመን፤ ከህዝባችን ጋር በጋራ ተግተን ሰርተን፤ ደቡብ ኢትዮጵያንም ሆነ ሀገራችንን የምናሻግር የብልፅግና አመራሮች ስላለን የሚፈርስ ሀገርም ክልልም አይኖርም።" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ



''የመጀመርያው አለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ የጋራ ብልፅግና፣ ፍትህና ርትዕ የተረጋገጠበት ዓለም ለመፍጠር አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው'' ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ...
07/09/2026

''የመጀመርያው አለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ የጋራ ብልፅግና፣ ፍትህና ርትዕ የተረጋገጠበት ዓለም ለመፍጠር አዲስ ምዕራፍ ከፋች ነው'' ክቡር አቶ አደም ፋራህ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና ዋና ፅ/ቤት ኃላፊ

የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ በሴኡል ደቡብ ኮሪያ በመካሄድ ላይ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች (ICDPP) የምክክር መድረክ ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

ይህ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክክር (ICDPP) ከኤሺያ፣ ከአፍሪካ፣ ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ የተወጣጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና መሪዎችን የሚያገናኝ መድረክ ነው።

የመድረኩ ዋነኛ ዓላማ በልዩ ልዩ የፖለቲካ ባህሎች መካከል የእርስ በእርስ ግንዛቤን ማሳደግ፣ እምነትን ማጠናከር፣ በጋራ ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ መለዋወጥ እና ቀጣይነት ያለው አለም አቀፍ ትብብር የሚደረግባቸውን መንገዶችን ማመላከት ነው።

በመድረኩ እየተሳተፉ የሚገኙት የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር አቶ አደም ፋራህ፣ የምክክር መድረኩ ሊኖረው ስለሚገባው ተልዕኮ በተለይም በዓለም አቀፍ ደረጃ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዲፕሎማሲ ሚና፣ አወቃቀር፣ ሊከተላቸው የሚገቡ መርሆዎች እና በብልፅግና ፓርቲ የመደመር እሳቤ ተሞክሮዎች ዙሪያ ንግግር አድርገዋል።

ክቡር አቶ አደም በንግግራቸው፣ የምክክር መድረኩ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕዝብን ፍላጎት የሚያንፀባርቁ መሪዎችን የሚያፈሩና ፖሊሲዎችን የሚቀርፁ መሆናቸውን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበት አንስተዋል።

መድረኩም በመንግስታት መደበኛ ዲፕሎማሲ እና በሕዝቦች መካከል ባለው ግንኙነት መካከል ያለውን ክፍተት የሚሞላ ወሳኝ የጋራ መድረክ ሊሆን እንደሚገባ ገልፀዋል።

በተለይም ዋና ትኩረቱ እምነትን መገንባት፣ የርዕዮተ-ዓለም ውጥረትን መቀነስ፣ ተቋማዊ ልምድ ልውውጥን ማጠናከር፣ ኃላፊነት የሚሰማቸው መሪዎች ማፍራት ላይ መተባበር፣ ግጭቶችን መከላከል እና ዓለም አቀፍ ትብብርን ማጠናከር መሆን እንዳለበት አብራርተዋል።

በተጨማሪም የሃሳብ ብዝሃነት፣ ሉዓላዊ እኩልነት፣ አካታችነት፣ ተቋማዊነት እና ተጨባጭ ትብብር መርሆዎች ሊመራ እንደሚገባም አክለዋል።

የምክክር መድረኩ በዋናነት ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባቸውም ዋና ዋና ጉዳዮች ሶስት መሆናቸውንም አንስተዋል።

የመጀመሪያው ዲሞክራሲያዊና ተቋማዊ ጥንካሬ ማረጋገጥ ሲሆን በዚህም ሰላማዊ
ምርጫን፣ የህግ የበላይነትን እና ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ማተኮር አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

ሁለተኛው አካታች ልማትና ኢኮኖሚያዊ ትራንስፎርሜሽን ማምጣት ሲሆን ከዚህ አኳያ ብልፅግና ፓርቲ የሚመራበት የመደመር እሳቤ መሰረት በማድረግ፣ ሁሉንም አቅሞች ተጨማሪ እሴትና አቅም በሚፈጥር አኳኃን ደምሮ በመጠቀም በማጎልበት የምግብ ሉዓላዊነትን፣ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን እና ዘርፈ ብዙ ምርታማነትን ማረጋገጥ እንደሚቻል አንስተዋል።

ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል በሶስተኛነት ያነሱት ሰላም ግንባታና ቅድመ-ግጭት መከላከልን ማጠናከር ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የፖለቲካ ፓርቲዎች ግጭትንና ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች ለመከላከል የሚያስችሉ ምክክሮች ላይ ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው ገልፀዋል።

በአጠቃለይ ክቡር አቶ አደም፣ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክክር መድረክ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መርህን መሰረት ያደረገና በተግባር ላይ ያተኮረ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ካስቻለ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት፣ የጋራ ብልፅግና፣ ፍትህና ርትዕ የተረጋገጠበት ዓለም ለመፍጠር አዲስ ምዕራፍ እንደሚከፍት እምነታቸው መሆኑን አንስተዋል።


07/09/2026
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልላዊ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛልርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልል አቀፍ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በወላይታ ...
07/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልላዊ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልል አቀፍ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ በመካሄድ ላይ ሲሆን፤ መድረኩ በዋናነት በክልሉ መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ አፈጻጸም፤ በ2019 መሪ ዕቅድ እንዲሁም የቀጣይ 5 ዓመት ጠቋሚ ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያ የሚመክር ይሆናል፡፡

የ2018 ዓ.ም ማጠቃለያ የሆነው ይሄው የአመራሮች መድረክ፤ የክልሉ መንግስት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለክልላዊ እና ሀገራዊ የሰላም፤ የልማትና የብልጽግና ራዕይ ስኬት ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት የተመዘገቡ ውጤቶችን በመገምገም፤ ለ2019 የላቀ አፈጻጸም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

መድረኩ የዞን፤ የረጂዮ ፖሊስ ከተሞች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት የበጀት ዓመቱን አጠቃላይ የተግባራት አፈጻጸም መሠረት ያደረገ የምዘና ውጤት ዙሪያም የሚወያይ ሲሆን፤ ይህም በክልሉ በየደረጃው ያሉ መዋቅሮችና አስፈጻሚ ተቋማት የማስፈጸም አቅም በማጎልበት ለተሻለ ውጤት ለማብቃት የጎላ ፋይዳ የሚኖረው ይሆናል፡፡

በተጨማሪም መድረኩ የክልሉን የብልጽግና ፍኖቴ ካርታ፤ ሀገራዊ የዘላቂ ልማት ግቦችንና የሁለንተናዊ ብልጽግና ራዕይ ማዕከል አድርጎ በተዘጋጀ የክልሉ መንግስት የቀጣይ 5 ዓመት ጠቋሚ ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያም የሚመክር ከመሆኑም በላይ የክልሉ አስፈጻሚ ተቋማት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የግብ ስምምነት የሚፈራረሙ ይሆናል፡፡

በመድረኩ የተገኙት ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በተለይ የክልሉ መንግስት የትኩረት አቅጣጫ በሆኑ ቁልፍ የልማት ዘርፎችና ሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች የውጤት ዘላቂነትን ከማረጋገጥ ባሻገር በላቀ አፈጻጸም የክልሉን ሕዝብ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ ለአመራሩ ስምሪት የሚሰጡ ይሆናል፡፡

በዚህም መድረኩ የአመራሩን የዓላማ፤ የአመለካከትና የተግባር አንድነት በማጠናከር ለቀጣይ የዘላቂ ሰላምና ልማት ተልዕኮ ያዘጋጃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የክልሉ መንግስት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ ህዝብ ግንባር ቀደም ተሳትፎ በሁሉም የልማት አውታሮች ዘርፍ ብዙ ውጤታማ የሰላም፤ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በመስራት አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ይታወቃል፡፡

በክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት፤ በተሻለ የተግባር አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት መድረኩ ዕውቅና ይሰጣል ተብሎም ይጠበቃል፡፡

በመድረኩ ከክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ገ/መስቀል ጫላ፤ የክልሉ አስተባባሪ አካላት፤ አፈ ጉባዓዎች፤ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፤ የዞንና የፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከፍተኛ አመራሮች፤ የረ/ፖ/ከተማ ከንቲቦችን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡

#ርዕሰመስተዳድርጽቤት

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Prosperity Party - የጋሞ ዞን ብልፅግና ፓርቲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share