Gamo Zone Government Communication Affairs Department

Gamo Zone  Government Communication Affairs Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo Zone Government Communication Affairs Department, Government Organization, Arba Minch'.

Permanently closed.
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ የ10ኛ ሳምንት ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀመጡ   ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብ...
01/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ የ10ኛ ሳምንት ተግባራትን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎች አስቀመጡ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ክልላዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ ለማብሰር በመንግስት እና ፓርቲ አመራር በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በመከናወን ላይ የሚገኙ የ10ኛ ሳምንት ተግባራት ያሉበት ደረጃን በበይነ መረብ በመገምገም ለታለመው ግብ ስኬት ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡

በስብሰባው የክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ወገኔ ቡዙነህ፤ በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ሳምንታዊ አፈጻጸም የተመለከተ ዝርዝር ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በውይይቱ፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብርና ሉዓላዊነት በመሸጋገር በክልሉ በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች በመከናወን ላይ ባሉ ተግባራት የ10ኛ ሳምንት አፈጻጸም መሻሻሎች መኖራቸውን ገልፀው ፤ ዕቅዱን ለማሳካት ከተቀመጠው የጊዜ ሰለዳ እና በክልሉ ካለው አቅም አንጻር አሁንም በየመዋቅሩ ብዙ መስራት እንደሚገባ በአጽንኦት ገልፀዋል፡፡

አመራሩ የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘው ሀገራዊና ክልላዊ ግብ፤ አንገብጋቢና የማይቀር የሉአላዊነት ጉዳይ መሆኑን በውል ተገንዝቦ የተጀመሩ ተግባራትን ብዝኃ ታታሪነትን ተላብሶ በሙሉ ትኩረት በቁርጠኝነት በመምራት ከግብ ማድረስ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በክልሉ በራስ አቅም የሰብዓዊ ድጋፍ መሸፈን የሚያስችል አቅም ለመገንባት በመደረግ ላይ ያለው ርብርብ የሚያግዝ የተሻሻለ የአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ ደንብ ማፅደቁን ያስታወሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ደንቡን በሁሉም ደረጃ በአግባቡ ገቢራዊ በማድረግ ለውጤት ማብቃት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

ለዚህም ደንቡን ወደ ተግባር ለመቀየር በክልል ደረጃ የተጀመሩ የህብረተሰብ ውይይቶችን በየደረጃው ባሉ መዋቅሮች ተደራሽ በማድረግ፤ ለታለመው የአደጋ ጊዜ የመጠባበቂ ፈንድ የሚውል ገንዘብ በአፋጣኝ ከዚህ ወር ጀምሮ የማሰባሰብ ስራውን መጀመር እንደሚገባ አስምረዋል።

የሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ አጀንዳው የመላው ህዝብ የጋራ አጀንዳ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሀብት በማሰባሰቡ ሂደት አመራሩ፣ የመንግስት ሠራተኛው፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የልማት ድርጅቶች፤ የሀይማኖት ተቋማት፣ የንግዱ ህብረተሰብ፤ አርሶና አርብቶ አደሩን ጨምሮ ሁሉም የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ማድረግ በሚያስችል አግባብ ማስፈጸም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የተያዘው ግብ በየደረጃው ያለው አመራር የመምራት፤ የመፈፀምና የማስፈፀም አቅሙ የሚለካበት ጭምር መሆኑን ተረድቶ፤ ለስኬቱ በመፍጠንና መፍጠር መሪህ በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት መመራትና መፈፀም እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

የሰብዓዊ ድጋፍን ከማረጋገጥ ተግባራት ጎን ለጎን ከኢሊኖ ክሰተት ጋር ተያይዞ የአየር ንብረት ለውጥ በምርታማነት ላይ የደቀነውን ፈተና እና በሰውና በእንስሳት ጤና ላይ ልያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመከላከልና ለመቀነስ የሚያስችል የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን መስራት እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።

ከአየር መዛባት ችግር ጋር ተያይዞ በሁሉም አካባቢዎች በፍጥነት ለሚደርሱ ሰብሎች ትኩረት ሰጥቶ መስራት እና የመጠባበቂያ እህል ክምችት ስራዎችን በአግባቡ መምራት እንደሚገባም አክለዋል።

ተረጂዎችን ከማሻገር ጋር በተያያዘ በማህበረሰብና በቤተሰብ ደረጃ የጠራ የብዝነስ ዕቅድ ነድፎ ለአንድ ተጎጂ አንድ የስራ እድል የመፈጠር ግብን በማሳካት እና መሰረታዊ ችግሮችን በመፍታት ከችግር ለመሻገር መስራት እንደሚገባም ገልፀዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በመጨረሻም በክልሉ ተረጂነትን በማስቀረት የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም መሸፈን የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ለመገንባት በመከናወን ላይ ያሉ ተግባራት ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ ማስቀጠል እና ክፍተቶችን ለይቶ በትኩረት በመስራት ለማሳካት የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ ሃሳባቸውን አጠቃለዋል፡፡

የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ በበኩላቸው፤ የተረጂዎችን መረጃ ከማጥራት እና ከፋይዳ የዲጂታል መታወቂያ ጋር ከማስተሳሰር አኳያ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በሁሉም መዋቅሮች መቶ በመቶ በማጠናቀቅ ዜሮ ማድረስ መቻሉ አበረታች መሆኑን ተናግረዋል።

አክለው እንደ ክልል ለተያዘው ግብ ስኬት በየደረጃው ባለው አመራር የሚታዩ የወጥነትና የቁርጠኝነት ክፍተቶችን በፍጥነት በማረም፤ ተግባራትን በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት መምራትና ለላቀ ውጤት መትጋት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ርዕሰመስተዳድርጽቤት

01/09/2026

"ጳጉሜን ለትውልድ'' የኢኮኖሚ ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ያድርጉ!

ከጋሞ ልማት ማህበር አርባምንጭ  ከተማ ቅርንጫፍ የተላለፈ የድጋፍ ጥሪ!ህብረተሰባችን ለትምህርት ጥራት ያለው ከፍተኛ ጥማትና ጉጉት እውን ሊሆን የሚችለው ጥራት ያለው የትምህርት መሰረተ ልማት...
01/09/2026

ከጋሞ ልማት ማህበር አርባምንጭ ከተማ ቅርንጫፍ የተላለፈ የድጋፍ ጥሪ!

ህብረተሰባችን ለትምህርት ጥራት ያለው ከፍተኛ ጥማትና ጉጉት እውን ሊሆን የሚችለው ጥራት ያለው የትምህርት መሰረተ ልማት ሲገነባ ነው። የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ላይ የገጠመውን ስብራት ለመጠገንና ጥራትን ለማረጋገጥ ባስቀመጠው ሀገራዊ የትምህርት ሪፎርም አቅጣጫ መሠረት፣ የወደፊቱን ትውልድ ተወዳዳሪ የሚያደርጉ "ሞዴል ትምህርት ቤቶችን" ማስፋፋት ዋናው ምሰሶ ነው።

የጋሞ ልማት ማህበር አርባምንጭ ከተማ ቅርንጫፍ የላቀ ትምህርትን በከተማው ተደራሽ ለማድረግ በትምህርት ግንባታ፣ የተለያዩ ቁሳቁሶችን በማሟላት እንዲሁም የትምህርት ግብዓቶችን ተደራሽ በማድረግ በትምህርት ዘርፉ መንግሥትን በመደገፍ በቁርጠኝነት ሲሰራ ቆይቷል::

በአሁኑ ወቅት የልማት ማህበሩ ከአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ግንባታው የተጀመረውን "የአርባምንጭ ከተማ ባይራ መካከለኛ ደረጃ ሞዴል ትምህርት ቤት" በ2019 ዓ.ም ስራ ለማስጀመር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ይህ ሞዴል ትምህርት ቤት የነገዎቹን ሀገር ተረካቢዎችን የሚያፈራ ሲሆን፣ ግንባታውን አጠናቆ ለተማሪዎች ዝግጁ ለማድረግ የህብረተሰቡ፣ የባለሀብቱና የወገን ድጋፍ ወሳኝ ነው። የወደፊቱ ትውልድ ውጤታማነትና ተጠቃሚነት የሚረጋገጠው በምናደርገው የጋራ ህብረተሰባዊ ተሳትፎ ነው።

በመሆኑም የተጀመረውን የሞደል ትምህርት ቤት ግንባታ በማጠናቀቅ፣ ደረጃውን የጠበቀ ቁሳቁስና ግብዓት የማሟላት ስራዎችን ለማከናወን ህብረተሰቡ በገንዘብና በዓይነት ድጋፍ እንዲያደርግ የጋሞ ልማት ማህበር አርባምንጭ ከተማ ቅርንጫፍ ጥሪውን ያቀርባል ሲል የዘገበው የአርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን ነው።

ገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ፦
* የባንክ ስም፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
* የአካውንት ስም፦ ጋልማ አርባምንጭ ከተማ ቅርንጫፍ
* የአካውንት ቁጥር፦ 1000021462768

ለሚያደርጉት ድጋፍ ከወዲሁ የከበረ ምስጋናችንን እናቀርባለን! 🙏

የተማረ ዜጋ በመፍጠር የተሻለች ሃገር እንገንባ!

ትምህርትን መደገፍ የህልውና ጉዳይ ነው!

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን የሥርዓተ ምሕዳር አገልግሎቶችን ለማጠናከር እና የብዝኃ ሕይወት ሀብትን ዘላቂነት ባለው መልኩ ለመጠበቅ የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ።​አርባ ምንጭ (ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም...
01/09/2026

በጋሞ ዞን የሥርዓተ ምሕዳር አገልግሎቶችን ለማጠናከር እና የብዝኃ ሕይወት ሀብትን ዘላቂነት ባለው መልኩ ለመጠበቅ የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ።

​አርባ ምንጭ (ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም - ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦

መድረኩ የሥርዓተ ምሕዳር አገልግሎት ክፍያ ስርዓትን ለመተግበር ያለመ ምክክር መሆኑም ተመላክቷል።

​በመድረኩ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን (EPA) ተወካዮች፣ የጋሞ ዞን አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ፣ የቱሪዝም መምሪያ፣ መስኖና ቆላማ፣ ገቢዎች ኢንቨስትመንት ፣ባህልና ስፖርት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል።

​በምክክር መድረኩ መልዕክት ያስተላለፉት የጋሞ ዞን አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዲኪሬ ድላሴ፣ የተፈጥሮ ሀብታችንን በዘላቂነት ለመጠበቅና ለመንከባከብ የሥርዓተ ምሕዳር አገልግሎት ክፍያ (PES) ፕሮግራምን መዘርጋት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለውም ተግባሩ ውጤታማ እንዲሆን ከኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን (EPA) ጀምሮ ከሚመለከታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

​ከኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን የመጡት የሥራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ ራሔል ለማ በበኩላቸው፣ የሥርዓተ ምሕዳር አገልግሎት ክፍያ ሥርዓት የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን ከኢኮኖሚያዊ ተፎካካሪነት ጋር በማቀናጀት ዘላቂ ጥቅም ለማስገኘት የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለውም የብዝኃ ሕይወት ሀብትን ለመጠበቅና ለማጎልበት የፌደራልና የዞን አካላት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ ሴክተሮች በትስስርና በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል።

​በመድረኩ አስተያየታቸውን የሰጡት አቶ ጋምቡራ ጋንታ እና ሌሎች የተሳተፉ ባለሙያዎች በበኩላቸው፣ የብዝኃ ሕይወትና የሥርዓተ ምሕዳር ጥበቃ ሥራዎችን ለማጎልበት ባለድርሻ አካላት በተቀናጀ መልኩ መስራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

​በውይይቱ ወቅት ለተግባሩ ስኬታማነት ቅድሚያ ለኅብረተሰቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መከናወን እንዳለባቸው ተመልክቷል።

በተለይም ከመስኖ ካናልና ከተፈጥሮ ሀብት የሚገኘውን አገልግሎት ከተጠቀመና ምርት ካመረተ በኋላ፣ ለአገልግሎቱ የሚከፍልበትን ግልጽ የአሠራር ሂደት በመዘርጋት ህዝቡን ያማከለ ግንዛቤ የማሳደግ ሥራ በሰፊው ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በስመኝ አክሊሉ

በዘይሴ አካባቢ የተፈጠረውን አለመግባባት በሰላማዊና በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት ሁሉም ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበየተጀመረው የእርቀ ሰላም ሂደት ከግብ እንዲደርስ የአካባቢው ነዋሪዎች ተባብረ...
01/09/2026

በዘይሴ አካባቢ የተፈጠረውን አለመግባባት በሰላማዊና በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት ሁሉም ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀረበ

የተጀመረው የእርቀ ሰላም ሂደት ከግብ እንዲደርስ የአካባቢው ነዋሪዎች ተባብረው እንደሚሠሩ ገልፀዋል

አርባ ምንጭ፣ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)

በዘይሴ አካባቢ የተፈጠረውን አለመግባባት በሰላማዊና በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

የዘይሴ ህዝብ በአካባቢው በተፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች በዘይሴ ደንብሌ ቀበሌ በመሰብሰብ የእርም ሥነ-ሥርዓት አከናውኗል።

የጋሞ ሽማግሌዎች፣ ከአጎራባች ዞኖች የተወጣጡ የባህል መሪዎችና የአካባቢው ምሁራን በዘይሴ ኤልጎ ቀበሌ በመገኘት ሀዘንተኞችንና የሟቾችን ቤተሰቦች አጽናንተዋል።

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የጋሞ ሽማግሌዎች እንደገለጹት፣ በግጭቱ ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው ለረጅም ጊዜ ሲሰደዱ የነበሩ ነዋሪዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ በማድረግ ውይይቶች መካሄዳቸው ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ጠቃሚ እርምጃ ነው።

በአካባቢው አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር የተጀመረው የእርቀ ሰላም ሂደት ከግብ እንዲደርስ ባህላዊ መሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አሳስበዋል።

ሽማግሌዎቹ አክለውም በጫካ የሚገኙ የአካባቢው ነዋሪዎች ትጥቃቸውን ፈትተው ወደ ቀያቸው በመመለስ ሰላማዊ ኑሮን እንዲመሩ ህብረተሰቡ ሊያሳምንና ሊመክር እንደሚገባ ገልጸዋል።

የዘይሴ ብሔረሰብ ባላባት ካት ተወካይ አዲሱ ፆና በበኩላቸው፣ የአካባቢውን ሰላም ወደቀድሞ ለመመለስና ነዋሪዎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ሁሉም ወገን በትብብር ሊሠራ ይገባል ብለዋል። ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ ባህላዊው የእርቅ ሂደት እንዲሳካ የጋራ ጥረት እንዲደረግም ጠይቀዋል።

የአካባቢው ምሁራን በበኩላቸው፣ የፖለቲካ ልዩነቶችን ለጊዜው በማስቀመጥ ሁሉንም የሚያግባባውን የሰላም ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት ነዋሪዎችን ከአስጊው ሁኔታ ማውጣት እንደሚገባ ገልጸዋል።

መሳሪያ ታጥቀው በጫካ የሚገኙ አካላትም ትጥቃቸውን በመተው ጥያቄዎቻቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ በውይይትና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ምሁራኑ አሳስበዋል።

የዘይሴ ደንብሌ ቀበሌ ነዋሪዎች በሰጡት አስተያየት፣ የተጀመረው የእርቀ ሰላም ሂደት ከግብ እንዲደርስና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን እንደሚተባበሩ ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ በተጨማሪም መንግስት በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከክልልና ከዞን የተወጣጡ የሀገር ሽማግሌዎችን በማሰባሰብ እያደረገ ላለው ጥረት ምስጋና አቅርበዋል።

ባለፉት ዓመታት በተከሰተው ግጭት የሰው ህይወት መጥፋቱን፣ ንብረት መውደሙንና ተቋማት መቃጠላቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ ይህም ከፍተኛ ማህበራዊ ቀውስ መፍጠሩን ጠቁመዋል።

ዳግም ተመሳሳይ ችግር እንዳይከሰትም ቂምና ቁርሾን በይቅርታ በማጠብ ለእርቀ ሰላሙ ቅድሚያ መስጠት እንደሚገባ ነዋሪዎቹ አሳስበዋል። መሳሪያ ታጥቀው በጫካ የሚገኙ የአካባቢው ነዋሪዎችም ወደ ህብረተሰቡ በመቀላቀል ለዘላቂ ሰላም የበኩላቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በማጽናኛ መርሃ ግብሩ የጋሞ ሽማግሌዎች፣ ከአጎራባች ዞኖች ጎፋ፣ ቡርጅ፣ ኮንሶና ኮሬ የተወጣጡ የባህል መሪዎችና የጋሞ ዞን አመራሮች ተገኝተዋል።

በኮሚንስት ታደሰ

በጋሞ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የፖሊስ አመራር አባላት የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል​አርባ ምንጭ፦ ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም  ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦ ​በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት...
01/09/2026

በጋሞ ዞን የ2018 በጀት ዓመት የፖሊስ አመራር አባላት የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

​አርባ ምንጭ፦ ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦

​በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት አስተላለፉት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ፤ ፖሊስ እንደ ሀገር፣ እንደ ክልልም ሆነ እንደ ዞን የአካባቢን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ከፍተኛ ሀላፊነት እንዳለበት አሳስበዋል።

​ህብረተሰቡን በማስተማርና ግንዛቤ በመፍጠር ወንጀልን ከመከላከል አኳያ ከፍተኛ ሥራ መሰራቱን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፤ ከሀገራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የተከናወኑ ተግባራት የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

​አክለውም አጠቃላይ የግምገማ መድረኩ በሥራ ላይ ትኩረት ያደረገ፣ ለቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመስራትና የህብረተሰቡን ደህንነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

​የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሃም ቡሄ በበኩላቸው፤ ባለፈው የበጀት ዓመት በመደበኛና በደራሽ ሥራዎች በርካታ የላቁ ተግባራት ሲከናወኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

​አልፎ አልፎ በሚከሰቱ የባለሙያዎችና የፖሊስ አባላት የስነ-ምግባር ጉድለቶች እንዲሁም ከህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት የተሄደበትን እርቀትና የተወሰዱ እርምጃዎችን በመለየት፣ በሳይንሳዊ አሰራር የተደገፈ የፖሊስ አገልግሎት በመስጠት በ2019 ዓ.ም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ አልሞ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑንም አዛዡ አብራርተዋል።

በመድረኩ ለግምገማው መነሻ የሚሆን ዝርዝር የውይይት ሰነድ እየቀረበ ሲሆን በቀጣይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል ።

​በመድረኩ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ፣ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የሥራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሀኪሜ አየለ፣ የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኢንስፔክተር አብረሃም ቡሄን ጨምሮ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የፖሊስ አዛዦችና የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል።

በስመኝ አክሊሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐምሌ እና ነሐሴ ወራት ያከናወኗቸው ቁልፍ ተግባራት - በምሥል
01/09/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐምሌ እና ነሐሴ ወራት ያከናወኗቸው ቁልፍ ተግባራት - በምሥል

በጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ አዘጋጅነት "ጤናማ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ለሰላምና አንድነት" በሚል ርዕስ ለማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ባለድርሻ አካላት በሰላምበር ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስል...
01/09/2026

በጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ አዘጋጅነት "ጤናማ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ለሰላምና አንድነት" በሚል ርዕስ ለማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ባለድርሻ አካላት በሰላምበር ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው

​አርባምንጭ ፣ ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙዩኒኬሽን)

​ማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ገጽታ ግንባታና ለልማት ማዋል እንደሚገባ የጋሞ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ አበዛሽ አይሳሮ ገለጹ። ኃላፊዋ ጤናማ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን በማጎልበት የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የሚያስከትሉትን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

​የሰላምበር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ደርዛ ደምሴ በበኩላቸው፤ ማህበራዊ ሚዲያን በኃላፊነት በመጠቀም የህዝቦችን አንድነት ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸው ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

​የስልጠናውን ሰነድ በዞኑ ፍትሕ መምሪያ የሕግ ባለሙያ ሀብታሙ ኃይሌ አማካኝነት ለተሳታፊዎች እየቀረበ ይገኛል።
​በመድረኩ የዞኑና የ7ቱ አጎራባች ወረዳዎች ፍትህ ጽሕፈት ቤት አመራሮች፣ ዓቃቢያነ ሕግ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ምንጭ ፦ሰላምበር ከተማ መ/ኮሙኒኬሽን

በጋሞ ዞን የአርሶ አደሮች የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አፈጻጸም ተገመገመ​አርባ ምንጭ፦ ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም  ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦ በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ቀበሌያትን መሰ...
01/09/2026

በጋሞ ዞን የአርሶ አደሮች የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ አፈጻጸም ተገመገመ

​አርባ ምንጭ፦ ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)፦

በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ቀበሌያትን መሰረት ያደረገ የአርሶ አደሮች የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ የምዝገባና የአክሲዮን ግዥ አፈጻጸም ያለበትን ደረጃ ለመገምገም እና በቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ ለመምከር ያለመ የግምገማ መድረክ ተካሄደ።

​የጋሞ ዞን አስተዳደር ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንሳይቲትዩት (ATI) ጋር በመተባበር በዞኑ የተለያዩ አምራች የግብርና ልማት ፕሮጀክቶችን በስፋት እየተገበረ ይገኛል።

የዚሁ ጥረት አካል የሆነውን የሁለተኛው ምዕራፍ የአግሪካልቸራል ኮሜርሻላይዜሽን ክላስተር (ACC Phase II) ፕሮጀክት የማስተዋወቂያ መድረኮች ከተካሄዱ በኋላ ሙሉ በሙሉ ወደ ትግበራ ተገብቷል።

​ይህም አርሶ አደሩን በሁሉም አቅጣጫዎች ባለቤትና ተሳታፊ በማድረግ ገቢውን ለማሳደግና በዘመናዊ መልኩ ራሱን የሚያስተዳድርበትን የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ ለመመስረት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

​በመድረኩ የተገኙት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በግብርናው ዘርፍ ያለውን ሰፊ አቅም ወደ ተሻለ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመቀየር የኢንዱስትሪዎች መኖርና መስፋፋት ለአርሶ አደሩ ምርት ተጨማሪ እሴት እንደሚፈጥር ተናግረዋል።

አርሶ አደሩ የወደፊት እጣፋንታው ባለቤት የሚሆንበትን ኩባንያ እንዲገነባና የካፒታል አቅሙ እንዲጎልብት የአክሲዮን ግዥውን አጠናክሮ መፈጸም እንዳለበት አሳስበዋል።

​አክለውም የዞኑ መለያና ብራንድ የሆነውን የአርባ ምንጭ ሙዝ የገበያ ተወዳዳሪነትና መልካም ስም አስጠብቆ ዘላቂ ለማድረግ የተቀናጀ ጥረት እንደሚጠይቅ ገልጸው፣ ሂደቱ በየጊዜው በውጤት ላይ ተመስርቶ እንደሚገመገም አስምረውበታል።

​በውይይቱ ማጠቃለያም የተጀመረው የአርሶ አደሮች የአክሲዮን ምዝገባ አፈጻጸም ፈጣንና ስኬታማ እንዲሆን፣ እንዲሁም ኩባንያው ወደ ሙሉ ስራ ገብቶ አርሶ አደሩን የገበያ ተጠቃሚ እንዲያደርግ የየደረጃው አመራርና ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ድጋፍ እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተቀምጧል።

​በስመኝ አክሊሉ

01/09/2026

"የተጠበቀ መሬት የሀብት ምንጭ ፤ ያልተጠበቀ መሬት የአደጋ ምንጭ በመሆኑ ተራራን በማልማት፣ ፀጋችንን በመንከባከብና በመጠበቅ መሬትን ወደ ኢኮኖሚ ምንጭነት ለመቀየር በተቀናጀ አግባብ መምራት ይገባል" ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Address

Arba Minch'
NEW

Telephone

+251468812386

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Government Communication Affairs Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gamo Zone Government Communication Affairs Department:

Shortcuts

Share