Arba Minch City Gov't Communication Affairs Office

Arba Minch City  Gov't Communication Affairs  Office Where ever you are; we deliver actual information concerning to Arba Minch City.

የታሪክ፣ የሕግ እና የፍትሕ በር፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም 130 ሚሊዮን ሕዝብ መተንፈሻዉን በጎረቤት አገራት ፈቃድ ላይ አንጠልጥሎ ሊቀጥል ይችላልን? የባሕር ...
06/08/2026

የታሪክ፣ የሕግ እና የፍትሕ በር፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ

ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም

130 ሚሊዮን ሕዝብ መተንፈሻዉን በጎረቤት አገራት ፈቃድ ላይ አንጠልጥሎ ሊቀጥል ይችላልን? የባሕር በር አልባነት የተፈጥሮ ዕጣ ፈንታ ነው ወይስ ሉዓላዊነትን የሚጎዳ የማይታይ የጂኦፖለቲካ ማዕቀብ?

የዓለም አቀፉን የሕግ ማዕቀፍ እና የጂኦፖለቲካዊ አሠራር ስንመለከተዉ የተባበሩት መንግሥታት የባሕር ሕግ ኮንቬንሽን (UNCLOS) በክፍል 10 ስር ለባሕር በር አልባ አገራት የሰጠውን መብት በሰፊው ያትታል። በተለይም አንቀጽ 125(1) እነዚህ አገራት የዓለምን ውቅያኖሶች ሀብት ለመጋራት እና መብታቸውን ለማስከበር "ወደ ባሕር የመድረስ መብት እና የመተላለፊያ ነፃነት" እንዳላቸው የማያሻማ ድንጋጌ አስፍሯል።

ከዚህም ባሻገር አንቀጽ 127 በመተላለፊያ (ትራንዚት) አገራት ላይ ከሚጣል የጉምሩክ ቀረጥ ነፃ የመሆን እንዲሁም አንቀጽ 131 በማሪታይም ወደቦች ላይ የባሕር በር ካላቸው አገራት መርከቦች ጋር እኩል የመስተናገድ መብት ይሰጣቸዋል።

ይሁን እንጂ በተግባር የባሕር በር ባለቤት የሆኑ አገራት ጂኦግራፊያዊ ብልጫቸውን እንደ ፖለቲካዊ ጫና ማሳረፊያ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት የባሕር በር ባለቤት ያልሆኑ ሀገራት በከፍተኛ የትራንስፖርት ወጪ፣ በማያቋርጥ የዋጋ ግሽበት እና በኢኮኖሚያዊ ጥገኝነት ይሰቃያሉ።

የዓለም የውሃ ሀብት የሁሉንም አገራት ብልጽግና ማረጋገጥ ሲገባው ይህ መዋቅራዊ የፍትሕ መጓደል አዳጊ አገራትን ከዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዳይሆኑ ከማድረጉም ባሻገር፣ ብሔራዊ ደህንነታቸውን አደጋ ላይ ይጥላል።

የኢትዮጵያ የእስካሁኑ ጉዞ ይህንን ግዙፍ መዋቅራዊ ጫና በተሳሳተ ትርክት ሸፋፍኖ ማቆየት ነበር። ለዓመታት "ስለ ቀይ ባሕር መናገር ግጭት መጋበዝ ነው" በሚል ፍርሃት ሀገራችን ታሪካዊ፣ ጂኦግራፊያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ትስስር ያላትን የቀይ ባሕር መብት ጥያቄ እንደ ነውር ስትቆጥረው ቆይታለች።

ነገር ግን የሕዝብ ቁጥሯ 130 ሚሊዮን በደረሰበት በዚህ ዘመን፣ ይህ ግዙፍ ማኅበረሰብ በጂኦግራፊያዊ እስረኝነት ታፍኖ መኖር አይችልም፤ በተፈጥሯዊ ሂደትም መተንፈሻ መፈለጉ አይቀሬ ነው።

የሌሎች አገራት የሕልውና መሠረት የሆነው የዓባይ ወንዝ ጉዳይ የዓለም አጀንዳ ሆኖ ሳለ፣ የኢትዮጵያ የሕልውና መሠረት የሆነው የቀይ ባሕር ጉዳይ እንዳይነሳ የሚደረግበት የጂኦፖለቲካዊ ግብዝነት ዛሬ ላይ ፈጽሞ ተሰብሯል።

ይህ የኢትዮጵያ አዲስ የእይታ ለውጥ ወደብ ከመጠቀም ባለፈ በዓለም አቀፉ የባሕር ሕግ (UNCLOS) የተረጋገጠውን በማሪታይም የኢኮኖሚ ዕድሎች፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በቀጠናው የባሕር ደህንነት ላይ እኩል ተሳታፊ የመሆን ተፈጥሯዊ ሉዓላዊ መብትን የማስከበር ሐቀኛ ጉዞ ነው።

ስለሆነም ቀጣይ መሆን የሚገባው የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ እርምጃ፣ ይህንን ሕጋዊ ጥያቄ ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጋር በአዲስ የትብብር እና የጋራ ፋይናንስ ማዕቀፍ ማስተሳሰር ነው።

ኢትዮጵያ የባሕር በር የሌላቸው አገራት የሚያጋጥማቸውን ጫና ለመቀነስ በጋራ ኢንቨስትመንት ላይ የተመሠረተ "የማይበጠስ የጥቅም ውህደት" መፍጠር አለባት።

የባሕር በር ባለቤት መሆናችን ለጎረቤት አገራት ዋስትና እንጂ ስጋት አለመሆኑን በተግባር ለማሳየት፣ የውስጥ አንድነት ከምንም ነገር በላይ ወሳኝ ነው።

ስለዚህም አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር የውስጥ ፖለቲካዊ መግባባታችንን በማጽናት፣ ጂኦግራፊያዊ ዕጣ ፈንታችንን በሰላማዊ እና ምክንያታዊ ድርድር እንድንቀይር የሚያስችለን የጸና መሠረት ነው።

የባሕር በር ጥያቄያችን የማንም ችሮታ ሳይሆን፣ ትውልድ እንዳይታፈን በጋራ የምንከፍተው የታሪክ፣ የሕግ እና የፍትሕ በር ነው!

06/08/2026
"የዲጂታል ጉዞ ኢትዮጵያን በቴክኖሎጂ የበለጸገችና በራስ አቅም የምትተማመን ሀገር ለማድረግ ያለመ ስትራቴጂካዊ ርምጃ ነው።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
05/08/2026

"የዲጂታል ጉዞ ኢትዮጵያን በቴክኖሎጂ የበለጸገችና በራስ አቅም የምትተማመን ሀገር ለማድረግ ያለመ ስትራቴጂካዊ ርምጃ ነው።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ወጣቶች ያቀረቡት ጥሪ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ወጣቶች በዚህ የክረምት ወቅት በነጻ በቀረበው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ የስልጠና መር...
05/08/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ወጣቶች ያቀረቡት ጥሪ

ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ወጣቶች በዚህ የክረምት ወቅት በነጻ በቀረበው የ5 ሚሊዮን ኮደርስ የስልጠና መርኃ ግብር ላይ እንዲሳተፉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጥሪ አቀረቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለኢትዮጵያ ወጣቶች ባስተላለፉት መልእክት፣ ይህ ክረምት በከንቱ እንዲያልፍ ሊፈቀድለት የማይገባ ትልቅ ዕድል ይዞ መጥቷል ብለዋል።

የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኮርሶች በነጻ የሚገኙ መሆናቸውን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የሚሰጠው የምስክር ወረቀትም ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው መሆኑን ገልፀዋል።

5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ቀድመው ወስነዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ አሁን ደግሞ ተራው የእናንተ ነው ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ወጣቶች በዚህ የስልጠና መርኃ ግብር ላይ ለመሳተፍ በ ethiocoders.et ላይ መምዘገብ እንደሚችሉም ተመላክቷል፡፡

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የልማት ካፕ ውድድር ጉዳት ለደረሠበት ተጫዋች 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር)ድጋፍ አደረገአርባምንጭ፣ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬ...
05/08/2026

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የልማት ካፕ ውድድር ጉዳት ለደረሠበት ተጫዋች 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር)ድጋፍ አደረገ

አርባምንጭ፣ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን)

በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ልማት ካፕ ውድድር ላይ ኩልፎ 02 ከ ሼቻ ባደረጉት ጨዋታ ላይ ጉዳት ላስተናገደው የኩልፎ 02 ተጫዋች ለሆነው ፀጋአብ ማንያዘዋል የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር 200 ሺህ ብር ለህክምና ወጪ ድጋፍ አድርጓል።

በጨዋታ መካከል ላይ ጉዳት የደረሰው ጸጋአብ በአይኑ እና አይኑ ዙርያ ባሉ አጥንቶች ከፍተኛ የሚባል ጉዳትን አስተናግዷል።

የአፍሪካ ከንቲባዎች ሥራ አመራር ኢንሼቲቭ (AMALI) ዳይሬክተር ጄኒፌር ኮማሊ ለይፋዊ ሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ አርባምንጭ፣ ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒ...
05/08/2026

የአፍሪካ ከንቲባዎች ሥራ አመራር ኢንሼቲቭ (AMALI) ዳይሬክተር ጄኒፌር ኮማሊ ለይፋዊ ሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ

አርባምንጭ፣ ሀምሌ 29/2018 ዓ.ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን)

የአፍሪካ ከንቲባዎች ሥራ አመራር ኢንሼቲቭ (AMALI) ፕሮግራም ዳይሬክተር ጄኒፌር ኮማሊ ለይፋዊ ሥራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ

ጄኒፌር ኮማሊ አርባምንጭ አየር ማረፊያ ሲደርሱ የአርባምንጭ ከተማ አመራሮች አቀባበል አድርጎላቸዋል።

05/08/2026

ባለፀጋዋ ከተማ: አርባምንጭ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ 2018 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯልየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ 2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ...
05/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ 2018 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ መድረክ መካሄድ ጀምሯል

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ 2018 የበጀት ዓመት የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ግምገማ እና ምዘና መድረክ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩ ባለፉት ጊዜያት የተመዘገቡ ጥንካሬዎችን ለማስፋት፣ ተሞክሮዎችን ለመቀመር እንዲሁም የተስተዋሉ ድክመቶችን ለማረም ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በክልሉ በ 2018 የበጀት ዓመት በፓርቲ እና በመንግስት የተከናወኑ ተግባራትን በመፈተሽ አመራሩን ለቀጣይ ተልዕኮ የማዘጋጀት ዓላማ እንዳለዉም ተጠቁሟል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ የበጀት ዓመቱ በመንግስት እና በፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም ዉጤት የተገኘበት ነዉ ብለዋል።

ብልጽግና ፓርቲ በሀገር እና በክልል ደረጃ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በስነ-ምግባር፣ በአመለካከትና በተግባር የላቀ አፈፃፀም ያላቸዉን አመራሮች ለመፍጠር እየሠራ መሆኑንም ገልፀዋል።

የግምገማ መድረኩ በእዉነት ላይ በመቆም በበጀት ዓመቱ ሁለተኛ ግማሽ ዓመት በጥንካሬ የተለዩትን ይበልጥ ለማጠናከር፣ ጉድለት የታየባቸውን ደግሞ ለማረም ዓላማ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የ 2018 የበጀት ዓመት በምርጫው የተቀመጡ መንቲያ ግቦች የተሳኩበትና በመንግስት ስራዎች አፈፃፀም ረገድም አመርቂ ድሎች መመዝገባቸውን ጠቅሰዋል።

በተለይም በ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የተገኘው ስኬት "ከምርጫ ማግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው መድረክ በጥልቀት መገምገሙን አንስተዋል።

መድረኩ የተቀመጡ የምዘና መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ የሁለተኛ ግማሽ ዓመት የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አፈፃፀም እንዲሁም በ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የአመራር፣ አባላትና የሕዝቡ ሚና የሚፈትሽበት መሆኑን አስረድተዋል።

መድረኩ እስከ ታችኛው መዋቅሮች በመቀጠል ኃይል የሚሰባሰብበት ሲሆን ጠንካራ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበት መሆኑም ተመላክቷል።

በመድረኩ የክልሉ መንግስት አስተባባሪ አካላት፣ የክልል ማዕከል እንዲሁም የ 12ቱ ዞኖችና 3ቱ ሪጂዮ ፖሊሲ ከተሞች አስተባባሪ አካላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ እውነታዎችን መሠረት ያደረገው የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት አቋም**************ለኢትዮጵያም ሆነ ለማንኛውም ሀገር የባሕር በር ማግኘት ከመሠረተ ልማት በላ...
05/08/2026

ታሪካዊና መልክዓ ምድራዊ እውነታዎችን መሠረት ያደረገው የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት አቋም
**************

ለኢትዮጵያም ሆነ ለማንኛውም ሀገር የባሕር በር ማግኘት ከመሠረተ ልማት በላይ የሆነ የሁለንተናዊ ዕድገትና የኢኮኖሚ ልማት መስመር የሚወስን ታላቅ ሀገራዊ ሀብት ከመሆኑም በላይ ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር የሚደረግን ሁለገብ ግንኙነትና የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ የሚያጎለብት ስትራቴጂካዊ መሠረት ነው።

በዓለም ላይ አብዛኛው ንግድ በባሕር መጓጓዣ ስለሚከናወን የባሕር በር ያላቸው ሀገራት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት አላቸው።

በተቃራኒው ኢትዮጵያ በታሪካዊ አጋጣሚዎችና በፖለቲካዊ ሴራዎች ምክንያት የባሕር በሯን እንድታጣ መደረጓ ለከፍተኛ የወደብ ኪራይ ወጪ፣ ለምርት ዋጋ መጨመር እና ለብሔራዊ ደህንነት ስጋቶች ዳርጓታል።

ይሁን እንጂ ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትና በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የዕድገት ማዕከል የሆነችው ኢትዮጵያ ይህንን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ፍትህ የማጣት ሁኔታ በዘላቂነት ተሸክማ መቀጠል አትችልም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ተዘግታ እንደማትኖር ያነሱትን ሀሳብ ተከተሎ የመደመር መንግሥት ጉዳዩን የሀገራችን ዋና የጂኦፖለቲካዊና የህልውና አጀንዳ እንዲሆን አድርጎታል።

የኢትዮጵያ ጥያቄ ከታሪካዊ እውነታዎች፣ ከመልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ እና ከፍትሃዊ የንግድ መርሆዎች ጋር የተያያዘ ነው።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የባሕር በር ተጠቃሚነቷን በሰላማዊ ውይይት፣ በሰጥቶ መቀበል መርህ፣ በኢኮኖሚያዊ ትብብር እና በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ጥያቄዋን እያቀረበች ትገኛለች።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የዘመኑን ቴክኖሎጂ የታጠቀ መከላከያ ሠራዊት በመገንባት የሰላም ማስከበር ተልዕኮዋን በስኬት እየተወጣች በመሆኗ፣ የባሕር በር ባለቤት መሆኗ የቀጣናውን ሰላምና ደህንነት ለማስፈን የበለጠ አቅም ይፈጥራል።

በመሆኑም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የኢትዮጵያን ፍትሃዊ ጥያቄ በመደገፍ አወንታዊ ሚና ሊጫወት እንደሚገባው የሚታመን ሲሆን፣ መላው ኢትዮያውያንም ይህ ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅም እና የህልውና ጥያቄ ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ በአንድነት ሊቆሙ ይገባል።

የነገዋን ጠንካራ ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የምክክር መድረኩ ታሪካዊ መሰረት እየጣለ ነው፡- የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች************በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ ...
05/08/2026

የነገዋን ጠንካራ ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የምክክር መድረኩ ታሪካዊ መሰረት እየጣለ ነው፡- የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች
************

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር መድረክ ላይ የሚገኙ ተመካካሪዎች ወቅታዊው የምክክር ሂደት የነገዋን ጠንካራ፣ ሰላማዊ እና የበለጸገች ኢትዮጵያ ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ ታሪካዊ አጋጣሚን የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

ተመካካሪዎቹ እንደሚያስረዱት በየአካባቢው የሚነሱ ልዩ ልዩ የልማትና የማህበራዊ ጥያቄዎችን እንዲሁም ሀገራዊ አጀንዳዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ በነጻነት ለመመካከር የመድረኩ መዘጋጀት ወሳኝ እርምጃ ነው።

ይህን ታሪካዊ እድል ያገኙ ከ4 ሺህ በላይ ተሳታፊዎች በሀገር ጉዳይ ላይ ለመምከርና ለመወሰን መቻላቸው ትልቅ እድል መሆኑን ጠቅሰው፣ መድረኩ የልዩ ልዩ ባህሎችና ቋንቋዎች ባለቤቶች እንዲተዋወቁና እንዲዋሃዱ አወንታዊ አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ተመካካሪቹ "ማየት ማመን ነው" በማለት የመድረኩን ሂደት ያደነቁ ሲሆን፣ እናቶች፣ አባቶች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በትልቅ ሀገራዊ ተስፋ ሀሳባቸውን ሲያንሸራሽሩ ማየታቸው የወደፊቷን ዴሞክራሲያዊ እና እኩልነት የሰፈነባትን ኢትዮጵያ ለመገንባት ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ተናግረዋል።

የውይይት ሂደቱን በተመለከተ ተሳታፊዎቹ በመድረኩ በርካታና የተቀራረቡ ሀሳቦች የሚነሱበት፣ ጥልቅ ክርክር የሚደረግበትና የጋራ ስምምነት የሚደረስባቸው ሂደቶች መኖራቸውን ጠቁመዋል።

ውይይቱ ከ10 ሰዎች ጀምሮ ደረጃ በደረጃ ወደ 50፣ 250 እና አሁን ደግሞ ወደ 500 ተሳታፊዎች እያደገ የመጣና በየደረጃው ከህዝብ የመጡ ተወካዮች ጥልቅ ውይይት እያደረጉበት በመሆኑ አጠቃላይ ሂደቱ ለኢትዮጵያ የወደፊት በጎ እርምጃ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል።

ተመካካሪዎቹ እንደገለጹት እያንዳንዱ ተሳታፊ የራሱ የሆነ አመለካከትና ሀሳብ ቢኖረውም ውይይቱ ትኩረት የሚያደርገው ለአጠቃላይ የኢትዮጵያ አንድነትና ህብረት በሚጠቅሙ ዋና ዋና ሀሳቦች ላይ ነው።

በተለይም የጋራ የሆኑ እሴቶችንና ሀሳቦችን በመለየት፣ ኢትዮጵያ በቀጣይ ለአፍሪካም ሆነ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የእድገት፣ የብልጽግና እና የሰላም ማሳያ እንድትሆን የማድረግ ፍላጎትና ቁርጠኝነት እንዳላቸው አረጋግጠዋል።

Address

Minch District, Middle City
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arba Minch City Gov't Communication Affairs Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Arba Minch City Gov't Communication Affairs Office:

Shortcuts

Share