Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት Official page of Gamo Zone People's Council Office

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው።ነሐ 27/2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግ...
02/09/2026

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው።

ነሐ 27/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግብር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው።

በዚህም የገረሴ ከተማ አስተዳደር መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ፕሬዚደንት ክቡር አቶ አሪፈ አረጋ የፍርድ ቤቱን 2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተደርጓል።

የዳኝነት አገልግሎት ዕቅድ አፈጻጸምን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ 663 ውሳኔ ለመስጠት ታቅዶ 474 መዛግብት ውሳኔ የተሰጠ ሲሆን ይህም 71.4% አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።

የተገልጋይ እርካታን ማሳደግን በተመለከተ የተገልጋይ እርካታን ወደ 96% ለማሳደግ ከታቀደው 56% አፈጻጸም መመዝገቡም በሪፖርቱ ተካቷል።

በሕጻናትና ሴቶች የሚደርሱ የወንጀል ጥቃቶችን መከላከል ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራባቸው መስኮች አንዱ ሲሆን 95 ውሳኔ ያገኘ መሆኑንም ሪፖርቱ ያመላክታል።

የቴክኖሎጂ አቅርቦትና የመረጃ አደረጃጀትን ለማቀላጠፍ በበጀት አመቱ ጥረት ብደረግም የኮምፒዩተር እና የፕሪንተር እጥረት ቢኖርም በስታስቲክስ ባለሙያዎች በተገቢው ሁኔታ መረጃን ማደራጀት ተችሏል ሲሉም የፍ/ቤቱ ፕሬዚዳንት በሪፖርቱ አስገንዝበዋል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

ሁለተኛ ቀን በያዘው የም/ቤት ጉባኤ የገረሴ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት 2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ሪፖርት ቀርቦ ውይዬት እየተደረገበት ይገኛል።ነሐ 27/201...
02/09/2026

ሁለተኛ ቀን በያዘው የም/ቤት ጉባኤ የገረሴ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት 2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ሪፖርት ቀርቦ ውይዬት እየተደረገበት ይገኛል።

ነሐ 27/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግብር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው።

በዚህም የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ አዝጌ ካሳ የገረሴ ከተማ አስተዳደር ም/ቤት 2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ሪፖርት አቅርበው ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።

በቀረበው ሪፖርት መነሻ ምክር ቤት አባላት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶችን ያነሱት ሲሆን፣በተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ዙሪያ የሚመለከታቸው የመስሪያ ቤት ኃላፊዎች እና ከንቲባው ማብራሪያና ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ።

በ2019 በጀት ዓመት የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት፣ በጤና፣ በግብርና፣በትምህርት፣በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በሌሎች ዘርፎች ላይ በልዩ ትኩረት እንደሚሰሩም ከንቲባው በሪፖርቱ አካቷል።

የኮሪዴር ልማትን ጨምሮ ልማት ተኮር ተግባራት አበረታች መሆኑ የተገለጸ ሲሆን መብራትን ጨምሮ መሠረተ ልማትን ለማማሟላት የሚደረገው ጥረት አበረታች እንደሆነም ተጠቁሟል።

የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም በእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ የሚታየውን ድክመት ወደ ውጤት በመቀየር የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነትንና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ይገባልም ተብሏል።

ከጊዜ ወደ ጊዜ የልማት እንቅስቃሴው ተጠናክሮ እንዲቀጥልና በ2019 በጀት ዓመት ይህንን ውጤታማ ጉዞን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሁሉም በትኩረት ይሰራልም ብለዋል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የጉባኤ ጥሪ‎‎የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ሞክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ-ግብር 1ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ነሐሴ 28-29/2018 ዓ.ም ያካሂዳል።‎‎ነሐሴ 26/ 2018 ዓ.ም...
01/09/2026

የጉባኤ ጥሪ

‎የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ሞክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ-ግብር 1ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ነሐሴ 28-29/2018 ዓ.ም ያካሂዳል።

‎ነሐሴ 26/ 2018 ዓ.ም

‎የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ሞክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አምሳሉ ሳማ የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ሞክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ-ግብር 1ኛ አመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤ ነሐሴ 28-29/2018 ዓ.ም እንደሚያካሂድ ገልፀዋል።

‎በጉባኤው፦
‎➡የክልልና የዞን ምክር ቤት አባላት
‎➡የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር አስተባባሪ አካላትና ካቢኔ አባላት
‎➡የቦረዳ ወረዳ አስተባባሪ አካላት
‎➡የቦረዳ ወረዳ ህ/ም/ቤት ዋናና ምክትል አፌ ጉባኤዎች
‎➡የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ፕረዚዳንት
‎➡ የዘፍኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሥራአስኪያጅ
‎➡የ5ቱ ቀጠናዎች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤዎች እና ሊቀመናብርት
‎➡ሲቪክ ማህበራት
‎➡ጋሞ ልማት ማኅበር ቦረዳ ቅ/ሥራአስኪያጅ
‎➡የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አባላት
‎‎➡የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ፓሊስ አዛዥ
‎➡የሐይማኖት ተቋማት መሪዎች እና ተጋባዥ እንግዶች ‎በዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ካዎ ጋሮ አዳራሽ ከጧቱ 2:30 ላይ እንድገኙ ጥሪ አድርገዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ አዝጌ ካሳ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛሉነሐሴ 26/2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር ...
01/09/2026

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ አዝጌ ካሳ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛሉ

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግብር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 8ኛ መደበኛ ጉባኤ እንደቀጠለ ነው።

በዚህም ጉባኤ የህዝብ ም/ቤት 2018 በጀት አመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ እቅ ቀርቦ በመወያየትና አስተያየት በመስጠት በም/ቤቱ አባላት በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።

የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አዝጌ ካሳ የ2018 በጀት አመት አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛሉ።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ሕዝብ ምክር ቤት 8ኛውን መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ ነሐ 26/2018 ዓ.ም በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግብር፣ 5...
01/09/2026

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ሕዝብ ምክር ቤት 8ኛውን መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀመረ

ነሐ 26/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግብር፣ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 8ኛ መደበኛ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በጉባኤውም የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከተማው ሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ገዛኸኝ ካንኮ ጉባኤው 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ስኬታማ ሆኖ በተጠናቀቀበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

አክለውም በዛሬው ጉባኤ ለከተማ አስተዳደሩ ሁለንተናዊ እድገትና ልማት ወሳኝ አጀንዳዎች ላይ የምንወያይበትና ውሳኔ የምናሳልፍበት በመሆኑ ሁሉም እስከ ፍጻሜው በትኩረት እንዲከታተልም ለጉባኤው መልዕክት አስተላልፈዋል።

የገረሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ም/ቤት የ2018 አፈጻጸም ሪፖርት የም/ቤቱ ም/አፌ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ መድሃኒት ከተማ እያቀረቡ ይገኛሉ።

በጉባኤው የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል ።

በጉባኤው የከተማው ሕዝብ ም/ቤት አባላት፤ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የተቋማት ኋላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ እንደሆነ ከስፍራው ያገኘነው መረጃ ያረጋግጣል፡፡
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

በጋሞ ዞን የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት የሴት ተመራጭ ኮከስ አባላት ውይይት አካሄዱ።ነሐሴ 21/2018 ዓ.ምበጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት የሴት ተመራጭ ኮከስ አባላት ውይይት አካሂ...
27/08/2026

በጋሞ ዞን የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት የሴት ተመራጭ ኮከስ አባላት ውይይት አካሄዱ።

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት የሴት ተመራጭ ኮከስ አባላት ውይይት አካሂደዋል።

በዉይይት መድረኩ የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት ምክትል አፌ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ወንቴ ሳይዳ አባላቱ በ7ኛው ዙር ሀገራዊና ክልላዊ ጠቅላላ ምርጫ ፍፁም ዴሞክራሲ ፍትሃዊ እና በህዝባችን ዘንድ ቅቡልነት ያለው በመሆን እንዲሁም በብልፅግና ፓርቲ አሸናፊነት በተጠናቀቀ ማግስት መካሄዱ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

ውይይቱ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ የተወያየ ሲሆን፥አጀንዳ ማቅረብና ማጽደቅ፣ የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ክንውን ማጠቃለያ ሪፖርት መገምገምና ማጽደቅ እና የ2019 ዓ.ም ጠቋሚ ዕቅድ በማጽደቅ እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች በመግባባት መሆኑን ክብርት ምክትል አፌ-ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

‎ሴቶች በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በሌሎችም ዘርፎች ላይ ሁለተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለማረጋገጥ የሴቶች ኮከስ አደረጃጀት ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።

‎በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራት አበረታች መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ወንቴ ጠቅሰው በቀጣይም ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።

‎የሴቶች ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትምህርት በጤና እንዲሁም በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች ላይም ቅንጅታዊ አሰራር በማጠናከር መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

‎የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሴት ምክር ቤት አባላትና የኮኮሱ ሰብሳቢዎች በተገቢው መስራት እንዳለባቸው አመላክተዋል።

‎የሴቶች ኮከስ አባላት በስልጠናው እንዳሉት የሴት ኮከስ አባላት የሴቶች ሁለተናዊ ተሳትፊነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ፋይዳው ትልቅ ነው።

‎ከዚህም ባሻገር የሴቶች የኢኮኖሚ አቅም ለማሳደግና የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ በመደገፍ በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።

‎በተለይም የሴት ኮከስ አባላት ተሳትፎ በማጠናከር የውሳኔ ሰጪነት አቅማቸውን ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ631 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀነሀሴ 20/2018  ዓ.ምበጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙ...
27/08/2026

የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈፀሚያ ከ631 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀ

ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም

በጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ- ግብር 13ኛ ዓመት ሥራ ዘመን 36ኛ መደበኛ ጉባኤ አካሂዷል።

በጉባኤው የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት የቀድሞ መደበኛ እና አስቸኳይ ምክር ቤት ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ ፀድቋል።

እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የሕዝብ ምክር ቤት ሥራ አፈፃፀም እና ቀጣይ ጠቋሚ ዕቅድ ለምክር ቤቱ አባላት ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ ፀድቋል።

ለምክር ቤቱ የ2018 በጀት ዓመት የወረዳው አስተዳዳራዊ ምክር ቤት ተግባራት አፈፃፀም እና ቀጣይ ጠቋሚ ዕቅድ በወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አሸናፊ ኦይዳ (ዶ/ር) በኩል ለጉባኤው ቀርቧል።

የህዝብ ምክር ቤት አባላት የቀረቡ ሪፖርቶችን በጥልቀት በመገመገም፣ ጥያቄዎች ካነሱ በኋል ተገቢ ምላሽ አግንተው በሙሉ ድምፅ አፅድቀዋል።

በተመሳሳይ የወረዳው ፍርድ ቤት 2018 በጀት ዓመት ተግባራት አፈፃፀም እና ቀጣይ ጠቋሚ ዕቅድ ቀርቦ በጉባኤ ተገምግሞ ፀድቋል።

የወረዳው የ2019 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድ ማስፈፀሚያ 631 ሚሊዮን 490 ሺህ 277 ብር ረቂቅ በጀት መሆኑን ለጉባኤው በዝርዝር ቀርቧል።

በጀቱ ከወረዳው ከሚሰበሰብ ገቢና ከዞን መንግስት የሚሸፈን መሆኑን ከተመላከተ በኋላ ምክር ቤቱ በረቂቅ በጀቱ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል ።

ጉባኤው የወረዳው ምክር ቤት አባላት፣ የወረዳ አመራሮች፣ የመንግስት መሰሪያ ቤት ማናጅመንት አባላት፣ የቀበሌ ህዝብ ምክር ቤት ዋና እና ምክትል አፈ-ጉባኤዎች፣ የቀበሌ አስተዳዳሪዎችና ሥራ አስኪያጂዎችን ጨምሮ ሀገር ሽማግለዎች እና የሀይማኖት መሪዎች ደምቀው በተሳተፉበት ሁኔታ ተጠናቋል።

በጋሞ ዞን የቆጎታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት በ17ኛ በመደበኛ ጉባኤ የወረዳውን የ2019  ዓ.ም በጀት  321,106,326 ብር በማጽደቅ አጠናቀቀ።ነሐሴ 20/2018 ዓ.ምየቆጎታ ወረዳ ህዝብ ...
26/08/2026

በጋሞ ዞን የቆጎታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት በ17ኛ በመደበኛ ጉባኤ የወረዳውን የ2019 ዓ.ም በጀት 321,106,326 ብር በማጽደቅ አጠናቀቀ።

ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም

የቆጎታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ ግብር 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ጉባኤ የወረዳውን የ2019 ዓ.ም በጀት 321,106,326 ብር በማጽደቅ አጠናቅቋል።

በጉባኤው የወረዳው የልማትና የአገልግሎት ስራዎች አፈፃፀም በስፋት ተመላክተዋል።

በተለይም በግብርና ምርታማነት፣ በገቢ አሰባሰብ፣ በከተማ ልማት፣በጤና ፣በትምህርት ፣ በስራ ዕድል ፈጠራና በሌሎችም ዘርፎች የተከናወኑ ስራዎች አፈፃፀም ሪፖርትን የቆጎታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አየለ ቱንጄ አቅርበዋል።

በቀረበው ሪፖርት ከምክር ቤት አባላት ጥያቄና አስተያዬት የቀረበ ሲሆን በቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች አስተዳዳሪው ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በዚህም በከተማ ልማት የመንገድ፣መብራት እና በሌሎችም መሠረተ ልማት ስራዎች ጥሩ አፈፃፀም የተመዘገበባቸው መሆኑን ገልፀዋል።

በግብርና ዘርፍ ምርታማነትን ለማሳደግ የተወሰዱ ርምጃዎችና የአርሶ አደሩን የምርት አቅም ለማሳደግ የተደረጉ ጥረቶች እንደ ጥሩ ውጤት የሚወሰዱ ናቸው ብለዋል።

በገቢ አሰባሰብም የገቢ መሠረትን ማስፋትና የሚሰበሰበውን ገቢ ማሳደግ ረገድ መሻሻሎች መኖራቸው ገልፀው የገቢ ስራን ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት መስራት የሚያስፈልግ መሆኑን አስገንዝበዋል።

በትምህርት ዘርፍ የተማሪዎችን ተሳትፎና የትምህርት ጥራት ለማሻሻል የተደረጉ ስራዎች አበረታች ውጤት የተመዘገበባቸው እንደሆነ በመጠቆም በተማሪ መጠነ መድገም ሁሉም የጋራ ኃላፊነትን መወጣት የሚገባ መሆኑን አሳስበዋል።

በጤና ዘርፍ የማህበረሰብ ፋርማሲ ግንባታና አገልግሎት ማስጀመር ፣የእናቶች ማቆያ እና ሌሎችም ተግባራት የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበባቸው መሆኑን አመላክተዋል
በስራ ዕድል ፈጠራም ወጣቶችን ወደ ስራና ምርታማነት ለማስገባት የተወሰዱ ተግባራት ለውጥ የታዬባቸው ሲሆን በቀጣይም ወጣቶችን በተለያዩ ዘርፎች ውጤታማ ለማድረግ የሚሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በማጠቃለያቸውም የግብርና ምርታማነትን ይበልጥ ማሳደግ፣ የገቢ አሰባሰብን ማጠናከር፣ የከተማ ልማት ስራዎችን በዕቅድና በጥራት ማስፈፀም፣ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል እና የስራ ዕድል ፈጠራን በማስፋት ወጣቶችን በተሻለ ሁኔታ ተጠቃሚ ማድረግ እና በሌሎች ዘርፎችም የተያዙ ዕቅዶች በተግባር እንዲፈፀሙ ፣የህዝብ ተሳትፎ እንዲጠናከርና የልማት ስራዎች በቁርጠኝነት ለመፈፀም የሚሰራ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የቆጎታ ወረዳ ፍርድ ቤት የ2018 አፈፃፀምና የ2019 በጀት ዕቅድ ቀርቦ ሀሳብ አስተያዬት ተሰጥቶበታል።

በተጨማሪም የቆጎታ ወረዳ 2019 ረቂቅ በጀት በቆጎታ ወረዳ ኢኮኖሚ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ በሆኑት በአቶ ተምበሮ ቴሮ የቀረበ ሲሆን 321,106,326 ብር ሆኖ ለምክር ቤቱ ቀርቧል።

የቀረበውን ረቂቅ በጀት ለተቋማት በተሸነሸነው በጀት ዝርዝር መነሻ የቆጎታ ወረዳ ም/ አስተዳዳሪና ፋይናንስና ፕላን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ደስታ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በዚህም የ2019 የወረዳው በጀት 321,106,326 ብር በምክር ቤት አባላት ፀድቆ ጉባኤው ተጠናቅቋል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

በጋሞ ዞን የቆጎታ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም.የቆጎታ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ-ግብር፣ 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 17ኛ መደ...
26/08/2026

በጋሞ ዞን የቆጎታ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም.

የቆጎታ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት 4ኛ ዙር መርሐ-ግብር፣ 13ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 17ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

የቆጎታ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባዔ የተከበሩ አቶ አሰፋ አየለ የጉባኤውን የመክፈቻ ንግግር አድርገው፣ 17ኛውን መደበኛ ጉባኤ በይፋ አስጀምረዋል።

በጉባኤ ማስጀመሪያው የቆጎታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት የማህበራዊ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ አባል ለነበሩት እና በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩ ለሃለቃ ያማ ፊኖ የህሊና ፀሎት ተደርጓላቸዋል።

ጉባኤው ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

እየተካሄደ በሚገኘው የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤው የምክር ቤቱ የቀድሞ መደበኛ እና አስቸኳይ ምክር ቤት ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ ፀድቋል።እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የሕዝብ ምክር...
26/08/2026

እየተካሄደ በሚገኘው የዲታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤው የምክር ቤቱ የቀድሞ መደበኛ እና አስቸኳይ ምክር ቤት ጉባኤ ቃለ-ጉባኤ ፀድቋል።

እንዲሁም የ2018 በጀት ዓመት የሕዝብ ምክር ቤት ሥራ አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ለምክር ቤቱ አባላት ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ ፀድቋል።

በተጨማሪም ለምክር ቤቱ የዲታ ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት ሥራ አፈፃፀም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በወረዳው ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ ዶ/ር አሸናፊ ኦይዳ በኩል እየቀረበ ይገኛል።
Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት

Address

Secha
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone People's Council Office - የጋሞ ዞን ህዝብ ምክር ቤት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share