06/09/2026
8 የእግር ኳስ ቡድኖችን ያሳተፈው የጋንታ መይጨ ክላስተር የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የእግር ኳስ ውድድር ፍፃሜውን አገኘ።
አርባ ምንጭ፦ ጷጉሜ 1/2018 ዓ.ም (አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩንኬሽን አገልግሎት)፦
በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ባህል ቱሪዝም ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት በጋንታ መይጨ ክላስተር ስካሄድ የሰነበተው የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የእግር ኳስ ውድድር ፍፃሜውን አግኝቷል።
ዛሬ በተካሄደው የፍፃሜ የእግር ኳስ ጨዋታ መይጨ አንድነት ከ ኦርዛ ድቻ ተገናኝተዋል።
በጨዋታው መይጨ አንድነት ተጋጣሚውን ኦርዛ ድቻን 6 ለ 4 በሆነ ውጤት በመለያ ምት በማሸነፍ የ2018 ዓ.ም የክረምት ወራት የእግር ኳስ ውድድር የክላስተሩ ሻምፕዮን በመሆን የዋንጫ ሽልማት አግኝቷል።
እንዲሁም በውድድሩ ሁለተኛ ሆኖ ላጠናቀቀው ኦርዛ ድቻ እና በውድድሩ ለተሳተፉ የእግር ኳስ ቡድኖች፣ ኮከብ ተጨዋቾች፣ የጨዋታ ዳኞች እና ለውድድሩ ስኬት አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ አቶ ሀብታሙ በየነ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ሶፎንያስ ቲቶስ የወረዳው ባህል ቱሪዝም ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ ካሳሁን የወረዳው መንግስት ኮሙዩንኬሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊን ጨምሮ የቀበሌው ነዋሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል።