Gamo Zone Tourism Department

Gamo Zone Tourism Department የጋሞ ዞን ባህል ታሪክ ቅርስ ቋንቋ ስነ ጥበብ ዕደ ጥበብና የተፈጥሮ መስህብ ተጠብቆ ለምቶና ተዋውቆ ለኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዲውል እንሰራለን።
(1)

አዳዲስ የኢኮ ቱሪዝም ስፍራዎችን ማስተዋወቅ ለዘርፉ ዕድገት የጎላ ፋይዳ እንዳለዉ ተጠቆመ ማህበረሰብ ተኮር የሆኑ አዳዲስ የኢኮ ቱሪዝም ስፍራዎችን የማስተዋወቅ መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ዩኒ...
07/04/2026

አዳዲስ የኢኮ ቱሪዝም ስፍራዎችን ማስተዋወቅ ለዘርፉ ዕድገት የጎላ ፋይዳ እንዳለዉ ተጠቆመ

ማህበረሰብ ተኮር የሆኑ አዳዲስ የኢኮ ቱሪዝም ስፍራዎችን የማስተዋወቅ መርሃ ግብር በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጫሞ ካምፖስ ተካሂዷል።
በመድረኩ በቋንቋና ባህል ላይ መሰረት ያደረገ "ኢኮ ቱሪዝም" የማስተዋወቅ ፕሮጀክት ቀርቧል።

የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ተስፋዬ ሀብተማሪያም በወቅቱ እንዳሉት፣ ተቋሙ ለማህበረሰብ ተኮር ስራዎችን ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል።

የዱቡሻ ስርዓትን በዩነስኮ ለማስመዝገብ በአምስት ቋንቋዎች ላይ መሰረት ያደረገ ጥናትና ምርምር እያካሄደ መሆኑን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
በዞኑና አከባቢዉ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን ለጎብኚዎች በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል የ"ማፕ ዴስቴሽን አፕሊከሽን" ስራ በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።

የአከባቢዉን የቱሪዝም መዳረሻነት እና አቅም ይበልጥ ለማሳደግ የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ዶ/ር ተስፋዬ አሳስበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ የቱሪዝም መስህብ ጥናት ልማትና ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብርሃም አለሙ በበኩላቸዉ፣ በክልሉ ያሉ ባህላዊ ዕሴቶችን በማልማት ፣በመጠበቅና በማስተዋወቅ ረገድ ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ ነዉ ብለዋል።

ለህብረተሰቡ ወቅቱ የሚፈልገዉን አገልግሎት ለመስጠት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ቅርሶቻችን ካሉባቸው ችግር ለማዉጣት ሳይንሳዊ አሰራሮች መከተል እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል።

በጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ የቱሪስት መስህቦች አገልግሎቶች ልማት አስተባባሪ አቶ ገመቹ ቡልቡላ ፕሮጀክቱ በስፋት ያልተዳሰሱ የቱሪስት ቦታዎች ለማስተዋወቅና ለማልማት ያግዛል ብለዋል፡፡

የአከባቢዉ ማህበረሰብና ወጣቶች የኢኮኖሚ አቅማ ለማሳደግና ለስራ ዕድል ፕሮጀክቱ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው አመላክተዋል፡፡
በተለያየ መንገድ ፕሮጀክቱን እየደገፈ ያለዉን አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲም አመስግነዋል፡፡

አክለዉም በዞኑ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን ማልማትና ማስተዋወቅ የሁሉንም ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዳመነ ቦጋለ እንደገለጹት፣ ዞኑ በርካታ የቱሪስት ስፍራዎች ያሉት መሆኑን ጠቁመዉ፣ ፕሮጀክቱ ቱሪዝም ዘርፍ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል ነዉ ብለዋል።
አርባ ምንጭ፡- መጋቢት 29/2018 ዓ.ም(ጋሞ ቴሌቪዥን)

የጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ሞናዬ ሞሶሌ እና ባለሙያዎች በዞናችን  በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሕይወት መጥፋትና መፈናቀል የተሰማቸውን መሪሪ ሀዘን ገልጸዋል፡፡መምሪያው በዚህ ...
13/03/2026

የጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ሞናዬ ሞሶሌ እና ባለሙያዎች በዞናችን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሕይወት መጥፋትና መፈናቀል የተሰማቸውን መሪሪ ሀዘን ገልጸዋል፡፡

መምሪያው በዚህ አሰቃቂ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች እና ዘመድ ወዳጆች ሁሉ መጽናናጽትን ተመኝተዋል፡፡ በአደጋው ምክንያት ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ወገኖችን ለማቋቋም ለሚደረገው ጥረት 18,400 ብር እና የአልባሳት ድጋፍ አድርገዋል፡፡

አርባምንጭ፣ መጋቢት 4/2018 ዓ.ም ( ጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ)

በጋሞ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን በካርታ የማመላከት (Mapping) ስራ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ተገመገመ​አርባ ምንጭ፣ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ )​የደቡብ ኢትዮ...
08/03/2026

በጋሞ ዞን የቱሪስት መዳረሻዎችን በካርታ የማመላከት (Mapping) ስራ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ተገመገመ
​አርባ ምንጭ፣ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ )
​የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በተገኙበት፣ የጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ከ“እስታዲያ” (Stadia) አማካሪ ድርጅት ጋር በመቀናጀት እያከናወነ ያለውን የቱሪስት መዳረሻዎችን በካርታ የማመላከት (Mapping) ስራ የደረሰበት ደረጃ ዛሬ ገምግሟል።
​በመድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ እንደገለጹት የክልሉ መንግስት የቱሪዝም ዘርፉን የኢኮኖሚ ምንጭ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው አማካሪ ድርጅቱ የሄደበት እርቀት አበረታች ነው ብለዋል።
በጋሞ ዞን የሚከናወነው የማፒንግ ስራ የዞኑን ብሎም የክልሉን የቱሪስት መስህቦች በሳይንሳዊ መንገድ ለዓለም ለማስተዋወቅና የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በዕቅድ ለመምራት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አፅንዖት ሰጥተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም ጋሞ ዞን ለቱሪስት ምቹ የሆኑ በርካታ ያልተነኩ መስህቦች ያሉት መሆኑን ገልጸው በተለይም የዞኑን ልዩ የአመጋገብ ባህል፣ የአለባበስ ስርዓት፣ እንዲሁም የአገር በቀል እውቀቶች ውጤት የሆኑትን የእርቅ፣ የለቅሶና የሰርግ ስነስርዓቶች ትልቅ የቱሪስት መስህብ በመሆናቸው በካርታው ውስጥ የማካቱ ስራ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል።
በዞኑ ውስጥ በርካታ የቱሪስት መስህቦች መኖራቸውንና አካታችነት ላይ ትኩረት እንዲደረግም ርዕሰ መስተዳድሩ አስገንዝበዋል።
​የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ በበኩላቸው ዞኑ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም ሀብቶች ባለቤት ቢሆንም እነዚህን ፀጋዎች በበቂ ሁኔታ የማስተዋወቅና ለልማት የማዋል ስራ ውስንነቶች እንደነበሩበት ጠቁመዋል።
አሁን እየተከናወነ ያለው የማፒንግ ስራ እነዚህን ክፍተቶች በመሙላት፣ የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል።
​የጥናት ስራውን እያከናወነ የሚገኘው የአማካሪ ድርጅቱ ተወካይ ባቀረቡት ሪፖርት መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ለስራቸው ስኬታማነት ትልቅ አቅም መሆኑን ጠቅሰዋል።
​ይህ የማፒንግ ስራ በዋናነት ስድስት የቱሪዝም ምሶሶዎችን (6 A's) ማዕከል ያደረገ መሆኑም ተገልጿል።
​አትራክሽን (Attraction) የመስህብ ስፍራዎችን ለይቶ ማውጣት፣​ አክሰስ (Access)፣ የመንገድና የመጓጓዣ ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣​ አኮሞዴሽን (Accommodation) የማረፊያና የእንግዳ ተቀባይነት አገልግሎትን ማሳደግ፣​ አዌርነስ (Awareness)፣ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን መስራት፣​አክቲቪቲ (Activities)፣ ጎብኚዎች የሚሳተፉባቸውን ኩነቶች ማዘጋጀትና​አሜኒቲስ (Amenities) አስፈላጊ የሆኑ መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማሟላት ላይ ያተኮረ መሆኑም ተጠቁሟል።
​በሂደቱም በዞኑ በስፋት የሚታወቁ የቱሪስት መዳረሻዎችን ደረጃቸውን ከማሳደግ ባለፈ፣ እስካሁን ትኩረት ሳያገኙ የቆዩ ድብቅ የቱሪስት መዳረሻዎችም ለጎብኚዎች ክፍት ለማድረግና በስፋት ለማስተዋወቅ እንደሚረዳ ተመላክቷል።
በግምገማ መድረኩ ላይ የተሳተፉት የሥራ ኃላፊዎች እንደገለጹት የካርታ ሥራ (Mapping) ዋና ዓላማ በጋሞ ዞን የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስተዋወቅ ነው።
ይህም የቱሪስት ፍሰቱን ከማሳደግ ባለፈ፣ ጎብኚዎች በቆይታቸው በቂ አገልግሎትና እርካታ አግኝተው የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ ለማስቻል ያለመ ነው።
​በተለይም በማፒንግ ሥራው የተካተቱት እንደ ማዜ ብሔራዊ ፓርክ ያሉ የአድቬንቸር (Adventure) ቱሪዝም መዳረሻዎች፣ የጉጌ ተራራ እና ለዓይን ማራኪ የሆኑት ጥቅጥቅ ያሉ የጀን ደኖች የዞኑን የተፈጥሮ ሀብት በግልጽ የሚያሳዩ መሆናቸው ተመላክቷል።
እነዚህን እምቅ ሀብቶች ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማዋል ቀሪ የልማት ስራዎች በትኩረት እና በቅንጅት መሰራት እንዳለባቸው የሥራ ኃላፊዎቹ አሳስበዋል።

ዥሎ ጥብቅ ደን⩩ ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ከገረሴ ከተማ 15 ኪ.ሜ፣ ከአርባምንጭ  81 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በስተ ሰሜን ፉዳሌ ፤በስተ ደቡብ ኮይራ ሙኩላ  በስተ ምሥራቅ ዛጋ ፤ በስተ ምዕራብ ድማሌ ...
18/02/2026

ዥሎ ጥብቅ ደን
⩩ ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ከገረሴ ከተማ 15 ኪ.ሜ፣ ከአርባምንጭ 81 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በስተ ሰሜን ፉዳሌ ፤በስተ ደቡብ ኮይራ ሙኩላ በስተ ምሥራቅ ዛጋ ፤ በስተ ምዕራብ ድማሌ ፉሴ ቀበሌያት አዋሳኝ ላይ ይገኛል

⩩ ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ ሲሆን አጠቃላይ 64 ሄ/ር ስፋት ያለው

⩩ ወይና ደጋ አየር ሁኔታ እና ተራራማ የመልክዓ ምድር አቀማመጥ ያለው

⩩ በመንግስትና በህዝብ እየተጠበቀ ያለ

⩩ የተለያዩ ብዝኃ ሕይወት መኖሪያ

⩩ በውስጡ የዛርጉላ ካዎዎች መካነመቃብር ትክል ድንጋዮች ያሉበት

⩩ በአቅራቢያዉ የሱባና ወንዝና ምንጮች ይገኛሉ

⩩ ደኑ የአካባቢውን አየር ንብረት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለኢኮ- ቱሪዝም አመቺ በመሆኑ መልማት የሚችል ነው

በጋሞ ዞን በቱሪዝም ዘርፍ ለሰለጠኑ አስጎብኝዎች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጠ​አርባ ምንጭ፤ የካቲት 09/2018 (ጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ)​ያሬድ የፌደራል አስጎብኝ ድርጅት ከጋሞ ዞን ቱ...
16/02/2026

በጋሞ ዞን በቱሪዝም ዘርፍ ለሰለጠኑ አስጎብኝዎች የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተሰጠ

​አርባ ምንጭ፤ የካቲት 09/2018 (ጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ)

​ያሬድ የፌደራል አስጎብኝ ድርጅት ከጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር፣ ከዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ አስጎብኝዎች ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቋል ።

​የጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ሞናዬ ሞሶሌ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት ስልጠናው ሰልጣኞች ስለ ዞኑ ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ መስህቦች ያላቸውን እውቀት ከማሳደጉም ባለፈ፣ እንግዶችን በባለሙያ ስነ-ምግባር የመቀበልና የማስተናገድ ብቃታቸውን የሚያጎለብት መሆኑን ተናግረዋል ።

ኃላፊው አክለውም ዛሬ የተሰጠው የምስክር ወረቀት ሰልጣኞቹ በዘርፉ በህጋዊ መንገድ ተሰማርተው ውጤታማ ስራ እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

​በቀጣይም የቱሪስት መዳረሻዎችን የማስፋፋትና የመሰረተ ልማት የማመቻቸት ስራዎችን ከወረዳዎች ጋር በቅንጅት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሙናዬ፤ ጋጮ ባባ ወረዳ ለቱሪዝም ዘርፍ እድገት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት በህዝቡ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

​የያሬድ አስጎብኝ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ጌትነት ስዩም በበኩላቸው በአካባቢው የሚገኙ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ የቱሪስት መስህቦችን፣ በተለይም የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶችን እንዲሁም የዱቡሻ ስርዓትን ጨምሮ ያሉ እምቅ ሀብቶችን ለዓለም ለማስተዋወቅ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በቀጣይም አካባቢውን ቀዳሚ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

​የስልጠናው አሰልጣኝ አቶ ኮፖ ካልሳ በበኩላቸው ሰልጣኞቹ በቆይታቸው ያሳዩት ተነሳሽነት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው፤ በቀጣይም መዳረሻዎቹን በሚዲያ በማስተዋወቅና ቱሪስቶችን በጋሞ እንግዳ አቀባበል ባህል ባህል በመቀበል እንዲያስተናግዱና የአከባቢውን ታሪክ ጠንቅቆ በማወቅና በማሳወቅ ረገድ ግንባር ቀደም ሚና የመጫወት ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

​ተሳታፊዎቹ ከጋጮ ባባ እና ከቦንኬ ወረዳዎች የተወጣጡ ወጣቶች ሲሆኑ ከእያንዳንዱ ወረዳ 5 ተሳታፊዎች ተሳትፈዋል።

​ስልጠናው ለ5 ቀናት የቆየ የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሲሆን ጥልቅ የአካባቢ እውቀት፣ የቱሪስት አያያዝ፣ የዲጂታል ሚዲያ አጠቃቀም እና የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያተኮረ መሆኑንም ተመላክቷል።

​በስነ-ስርዓቱ ማጠቃለያ ላይ ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የዕውቅና የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ በይፋ ተሰማርተው የዞኑን የቱሪዝም ሀብት በባለሙያነት እንዲያስተዋውቁ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ተመላክቷል።
መ/ኮሙኒኬሽን

ጌዣ ጥብቅ ደንበገረሴ ከተማ አስተዳደር  በዛዝኤና ጎራቴ ቀበሌ ከአርባምንጭ ከተማ 56 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ የተፈጥሮ ጥብቅ ደን ነው።መስህቡ ከባህር ጠለል በላይ 3000 ሜትር ከፍታ ላይ...
01/02/2026

ጌዣ ጥብቅ ደን
በገረሴ ከተማ አስተዳደር በዛዝኤና ጎራቴ ቀበሌ ከአርባምንጭ ከተማ 56 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ የተፈጥሮ ጥብቅ ደን ነው።

መስህቡ ከባህር ጠለል በላይ 3000 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን አጠቃላይ 394 ሄ/ር ሽፋን አለወ። ደኑ ስያሜውን ያገኘው አቋርጦት ከሚያለፈው ከጌዣ ወንዝ ሲሆን በደኑ ማዕከላዊ ስፍራ የሲሶቴ ፏፏቴ ይገኛል ።

ጌዣ ለተለያዩ እንስሳትና አዕዋፋት መኖሪያ ከመሆን በዘለለ የአካባቢ አየር ንብረት ለውጥ ሚዛንን ከማስጠበቅ አንፃር ከፍተኛ ሚና አለው።

በተጨማሪም ለኢኮ-ቱሪዝም እንቅስቃሴ አመቺ ሆኖ ቢለማ ከፍተኛ ጥቅም ሊያስገኝ የሚችል እና አሁን ባለበት ሁኔታ ለጉብኝት ምቹ በመሆኑ እንዲጎበኙ ተጋብዘዋል።

ሚሽራ ሹቻ (የሙሽራ ዲንጋይ)ሚሽራ ሹቻ (የሙሽራ ዲንጋይ) በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ጋርሳ ሐኒቃ ቀበሌ ሶሞ ንዑስ ይገኛል፡፡ ዲንጋዩ አርካና ማራ ፓላሃ ተብሎ በሚጠራ የዘር ሀረግ የተቀመ...
30/01/2026

ሚሽራ ሹቻ (የሙሽራ ዲንጋይ)

ሚሽራ ሹቻ (የሙሽራ ዲንጋይ) በጋሞ ዞን ካምባ ዙሪያ ወረዳ ጋርሳ ሐኒቃ ቀበሌ ሶሞ ንዑስ ይገኛል፡፡ ዲንጋዩ አርካና ማራ ፓላሃ ተብሎ በሚጠራ የዘር ሀረግ የተቀመጠ ሲሆን ባህላዊ ሹመት የሚቀበሉ ንጉስ/ ካዎ/ እና ሐለቃ ብቻ የሚቀመጡበት ስፍራ ነው፡፡

ለሌላ ማንኛውም ሰው መቀመጥ አይፈቀድም፡፡ ከተቀመጠ ጎሜ ይሆንበታል ተብሎ ስለሚታሰብ በግ መስዋዕት ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡

ከማዜ ወንዝ መልስ እስከ ታኬኖ ወንዝ ድረስ አርካና ማራ ፓላሃ ተብሎ የሚጠራው የዘር ሀረግ አባል የሆኑ ሹመት ተቀብሎ የሰጎን ላባ / ጉቼ/ አናታቸው ላይ ለማሰር (ስለ መሾማቸው የሚገልጽ ምልክት) ወደ ሻጋና (ሹመት ወደ ሚሰጠው ሰው) ቤት ከመሄዳቸው አስቀድሞ እዚህ ዲንጋይ ላይ ይቀመጣሉ፡፡

ሹመቱን ከተቀበሉ በኋላ ስለ መሾማቸው የሚገልጽ ምልክት የሰጎን ላባ/ ጉቼ/ ጭንቅላታቸው ላይ አስረው ካዎ/ ንጉስ/ አሌ ቦርቻ ደጃፍን ዘልቀው ካዎ ዜማና ፄራ ዙሎ ገበያን ዞረው ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡

ዲንጋዩ ላይ በቀኝ በኩል ንጉሱና የንጉሱ ባለቤት ሲቀመጡ በግራ በኩል ሀለቃ እና የሀለቃ ባለቤት ይቀመጣሉ፡፡

የጥምቀት በዓል በአርባ ምንጭ እየተከበረ ነውአርባምንጭ፣ ጥር 11/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ)የጥምቀት በዓል በአርባ ምንጭ ከተማ  በፈለገ ዮርዳኖስ የአምስቱ አድባራት የመስ...
19/01/2026

የጥምቀት በዓል በአርባ ምንጭ እየተከበረ ነው

አርባምንጭ፣ ጥር 11/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ)

የጥምቀት በዓል በአርባ ምንጭ ከተማ በፈለገ ዮርዳኖስ የአምስቱ አድባራት የመስቀል ደመራና የጥምቀት ስርዓት ማክበሪያ ቦታ ጥምቀት ባህር ላይ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡

በአከባባር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ፣የሀገረ ስብከቱ ሰበካ ጉባኤ ማደረጃ መምሪያ ኃላፊ መላከ ገነት አባ ወልደ ማሪያም ደምለው፣ መላከሐይል ቆሞስ አባስባት ገብረማሪያም የደብረሐይል ቅዱስ ገብርኤልና የደብረ መንከራት ቅዱስ ሚካኤል አብያቴ ክርስትያናት ዋና አስተዳዳሪ፣ሊቃውንተ ቤተክርስትያን ካህናትና ዲያቆናት፣የእምነቱ ተከታዮችና ሌሎችም የበዓሉ ታዳሚያን ተገኝተዋል።

በዓሉ በልዩ ሁኔታ እየተከበረ በሚገኝበት በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀት ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ቱሪስቶችና በርካታ ምዕመናን ተሳትፈዋል።

አሁን ላይ በዓሉ በተለያዩ ኃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ጥምቀት ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን የእዳ ደብዳቤ ለመቅደድ በዮርዳኖስ የመጠመቁ መታሰቢያ በዓል ነው፡፡
መ/ኮሚዩኒኬሽን

የጊዲቾ ደሴት* በብርብር ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ከአርባምንጭ 53 ኪ.ሜ ርቀት እና  ሁለት ሰዓት የሞተር ጀልባ ጉዞ  ያለው * በአባያ ሐይቅ ከሚገኙ ዘጠኙ ደሴቶች አንዱ ሲሆን...
16/01/2026

የጊዲቾ ደሴት
* በብርብር ከተማ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ከአርባምንጭ 53 ኪ.ሜ ርቀት እና ሁለት ሰዓት የሞተር ጀልባ ጉዞ ያለው
* በአባያ ሐይቅ ከሚገኙ ዘጠኙ ደሴቶች አንዱ ሲሆን ሰዎች የሚኖሩበት ብቸኛው ደሴት ነው
በደሴቱ ሐሮ፣ ሽግማ እና ባይሶ ተባሉ መንደሮች አሉ
* በዞኑ ከሚገኙ ሶስት ነባር ብሔረሰቦች አንዱ የሆነው የጊዲቾ ብሔረሰብ መገኛ እና መኖሪያ ነው
* ብሔረሰቡ ባይሶ የሚባል የኩሸቲክ ቤተሰብ ቋንቋ ተናጋሪ ነው
* ኢኮኖሚያቸው የተመሰረተው በእንስሳት እርባታ፣ በዓሳ ማስገር፣ ንብ በማነብና በሰብል ምርት ነው
* በአካባቢው መጠሪያ ዎላቦ የተሰኘውን ባህላዊ ጀልባ ለባህር ላይ ትራንስፖርት ይጠቀሙታል
* በአካባቢው መጠሪያ ስሲቦሊ የኖራ ድንጋይ እና የድንጋይ ላይ ቅርጻቅርጽ(በተፈጥሮ ተስለው የሚገኙ የዛፍ ቅርንጫፍ መሳይ ምስሎች በድንጋዮቹ ውስጣዊና ውጫዊ ገጽታቸው ላይ የሚታይ) እና ሀቦስ ተክል /ተፈጥሯዊ የንብ ቀፎ/ ደሴቱ ተፈጥሯዊ መስህቦች ናቸው

Address

SNNPR
Arba Mintch

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251468810004

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Tourism Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gamo Zone Tourism Department:

Share