South Ethiopia Region Revenue Bureau /የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ/

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Mintch
  • South Ethiopia Region Revenue Bureau /የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ/

South Ethiopia Region Revenue Bureau /የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ/ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from South Ethiopia Region Revenue Bureau /የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ/, Public & Government Service, Limat, Arba Mintch.

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉውድ የቢሯችን አመራሮች፣ መላው የገቢዎች ባለሙያዎች እና የክልላችን ግብር ከፋዮች! ...
07/09/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ውድ የቢሯችን አመራሮች፣ መላው የገቢዎች ባለሙያዎች እና የክልላችን ግብር ከፋዮች!

በመጀመሪያ በ2018 በጀት ዓመት በተለያዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ኢኒሼቲቮች በተደረገው ከፍተኛ እንቅስቃሴና በተመዘገበው የላቀ የሥራ አፈጻጸም፣ ተቋማችን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የክልሉ ከፍተኛ የእውቅና ሽልማትና የመኪና ተሸላሚ በመሆኑ የተሰማኝን ወሰን የሌለው ደስታና ኩራት ለመግለጽ እወዳለሁ።

ይህ ድል በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን፣ የመላው የተቋማችን ሰራተኞች እና አመራሮች የቀን ከሌሊት የጽናት፣ የትጋትና የተቀናጀ ሥራ ግልጽ ጥረት ውጤት ነው። በየደረጃው የሚገኙ የመዋቅራችን አባላት ያለመታከት ያሳያችሁት የባለቤትነት ስሜት፣ ከፍተኛ የሙያ ሥነ-ምግባር እና ለአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ያደረጋችሁት ያልተቆጠበ ጥረት ለዚህ ታላቅ ስኬት አብቅቶናል።

በተጨማሪም የዚህ ታላቅ ስኬት ባለቤቶች የሆናችሁ፦

👉 ታማኝ ግብር ከፋዮቻችን የክልላችንን ልማትና እድገት በመደገፍ ግብራችሁን በወቅቱና በትክክል በመክፈል የዜግነት ግዴታችሁን ስለተወጣችሁ ፤

👉 ባለድርሻ አካላትና የክልሉ ስለተወጣች ለተቋማችን ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ስላደረጋችሁልን፤

ላቀረባችሁልን ድጋፍና ላሳያችሁት አጋርነት በቢሮዬ እና በራሴ ስም የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

ውድ የሥራ ባልደረቦቼ!

ይህ የተሰጠንም ከፍተኛ እውቅና እና የሽልማት ተሽከርካሪ ያለፉ ስኬቶቻችን ማክበሪያ ብቻ ሳይሆን፣ ለቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የበለጠ እንድንሰራ፣ የተቀመጡ የገቢ እቅዶችን አበልጽገን እንድናሳካ እና ዘመናዊና ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን አጠናክረን እንድንቀጥል የተጣለብን ትልቅ ኃላፊነትና የቤት ሥራ ነው።

በቀጣይም ይህንን የተከበሬ የላቀ አፈጻጸም ባህል አድርገን በመቀጠል፣ ለክልላችን ኢኮኖሚያዊ ዕድገትና ለህዝባችን ተጠቃሚነት በጋራና በጠንካራ መንፈስ እንደምንሰራ ሙሉ እምነት አለኝ።

በድጋሚ እንኳን ደስ አለን!

ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገብ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የእውቅና ሽልማት ተሰጠውበክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኢኒሼቲቮች ተሻለ የተ...
07/09/2026

በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የስራ አፈፃፀም በማስመዝገብ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የእውቅና ሽልማት ተሰጠው

በክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኢኒሼቲቮች ተሻለ የተግባር አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት መድረኩ ዕውቅና ተሰጥቷል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በላቀ አፈፃፀም የመኪና ተሸላሚ ሆኗል።

የክልሉ መንግስት በ 2018 የበጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሴክተር ቢሮዎች እዉቅና ሰጥቷልጳጉሜን 02/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በ 2018 የበጀት ዓመት የላቀ ...
07/09/2026

የክልሉ መንግስት በ 2018 የበጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ሴክተር ቢሮዎች እዉቅና ሰጥቷል

ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በ 2018 የበጀት ዓመት የላቀ ዉጤት ላስመዘገቡ ሴክተር ቢሮዎች እዉቅና ሰጥቷል።

በዚህም መሠረት፦

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍትህ ቢሮ፣ ፋይናንስ ቢሮ፣ ፕላን ቢሮ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ የመስኖና ቆላማ አከባቢዎች ልማት ቢሮ፣ ጤና ቢሮ እና ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮዎች ተሸላሚ ሆነዋል።

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ በበጀት ዓመቱ ባስመዘገበው የላቀ አፈፃፀም ልዩ ተሸላሚ በመሆን መኪና ተሸልሟል።

የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ሽልማቱን ለተሸላሚ ሴክተር ቢሮዎች ሰጥተዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የስራ አፈፃፀሞ ያስመዘገቡ ተቋማት ፣ ዞኖች እና የሪጂዮ ፖሊስ ከናተሞች  እውቅናና ሽልማት ተሰጣቸውበክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኢኒሼቲቮች...
07/09/2026

በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ የስራ አፈፃፀሞ ያስመዘገቡ ተቋማት ፣ ዞኖች እና የሪጂዮ ፖሊስ ከናተሞች እውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው

በክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በኢኒሼቲቮች ተሻለ የተግባር አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት መድረኩ ዕውቅና ተሰጥቷል።

* የክልሉ ገቢዎች ቢሮ እና የወላይታ ፣ ጋሞ እና ጌዴኦ ዞኖች በላቀ አፈፃፀም የሚኪና ተሸላሚ ሆነዋል።

* ከክልል ቢሮዎች ከፍተኛ አፈፃፀም የስመዘገቡ
የክልሉ ፍትህ ቢሮ፣ ፋይናንስ ቢሮ፣ ፕላን ቢሮ ፣ ገቢዎች ቢሮ፣ ጤና ቢሮ፣ መስኖና ቆላማ ቢሮ፣ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ፣

* ከዞን መዋቅሮች:- ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ የመኪና እና ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የተሸልመዋል ፡- 1ኛ ወላይታ ዞን 2ኛ ጋሞ ዞን 3ኛ ጌዴኦ ዞን፣ ተሸላሚ ሆነዋል።

*ከሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች ፡- ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ የሪጂዮ ፖሊስ ከተሞች 1ኛ- አርባምንጭ ከተማ 2ኛ- ወላይታ ሶዶ ከተማ 3ኛ ዲላ ከተማ አስተዳደር ተሻላሚ ሆነዋል ።

* እንዲሁም ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ጎፋ ፣ አሪ ፣ ደቡብ ኦሞ ፣ ኮንሶ፣ ባስኬቶ እና ጋርዱላ ዞን አስተዳደር ተሸላሚ ሆኖዋል።

በመድረኩ ኢኒሼቲቮችን በመፈፀም ጅምር አፈፃፀም ላስመዘገቡ አሌ ፣ ኮሬ እና ቡርጂ ዞን ተሸልመዋል።

የእውቅናው መስፈርት በግብርና ልማት ፣ ከተማና መሰረተ ልማት ፣ ትምህርት ልማት ፣ ጤና ልማት፣ ቱሪዝም ልማት፣ ንግድ ኢንደስትሪ ልማት ፣ ገቢ ንቅናቄ፣ ስራና ክህሎት እንዲሁም የዲጂታላይዘሽን ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ኢኒሼቲቮችን ትኩረት ያደረገ መሆኑን የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ ቦሻ ቦንቤ ( ዶ/ር ) የምዘና መስፈርቱን ባብራሩበት ወቅት ገልፀዋል።

መድረኩ ተቋማት ከክቡር ርዕሰ መስነዳድሩ ጋር የግብ ስምምነት በመፈራረምም ተጠናቋል።

ደረሰኝ አለመሰጠት (ወይም አለመቀበል) በሀገር ኢኮኖሚ፣ በሸማቹ እና በነጋዴው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል። 1. በሀገር እና በሕዝብ ላይ የሚደርስ ጉዳት👉የታክስ ገቢ ማጣት፦ መንግሥት ለሕዝ...
07/09/2026

ደረሰኝ አለመሰጠት (ወይም አለመቀበል) በሀገር ኢኮኖሚ፣ በሸማቹ እና በነጋዴው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።

1. በሀገር እና በሕዝብ ላይ የሚደርስ ጉዳት

👉የታክስ ገቢ ማጣት፦ መንግሥት ለሕዝብ አገልግሎት (ለምሳሌ ለትምህርት ቤት፣ ለጤና፣ ለሕክምና እና ለሕዝብ መሠረተ ልማት) የሚጠቀምበትን የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና ሌሎች ቀረጥ ማሰባሰብ እንዳይችል ያደርጋል።
👉የሕገ-ወጥ ንግድ መስፋፋት፦ ደረሰኝ የማይሰጡ ነጋዴዎች ገቢያቸውን ስለሚደብቁ ኮንትሮባንድ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲስፋፋ በር ይከፍታል።

2. በሸማቹ (በገዢው) ላይ የሚደርስ ጉዳት

👉የዋስትና መብት ማጣት፦ የተገዛው ዕቃ ቢበላሽ ወይም ጉድለት ቢገኝበት፣ ደረሰኝ ከሌለ ዕቃውን ለመቀየር ወይም ገንዘብ ለማስመለስ ሕጋዊ ማስረጃ አይኖርም።
👉ለማጭበርበር መጋለጥ፦ ነጋዴው የተጋነነ ዋጋ ቢጠይቅ ወይም ጥራት የሌለው ዕቃ ቢሸጥ፣ ሸማቹ መብቱን ለማስከበር እና አቤቱታ ለማቅረብ ይቸገራል።

3. በነጋዴው ላይ የሚደርስ ጉዳት

👉የሕግ ተጠያቂነት እና ከባድ ቅጣት፦ ደረሰኝ አለመስጠት በኢትዮጵያ የታክስ ሕግ መሠረት የወንጀል ድርጊት ነው። ደረሰኝ ሳይሰጡ መገኘት እስከ ከባድ የገንዘብ መቀጮ እና የእስራት ቅጣት ሊያደርስ ይችላል።
👉ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድር፦ ሕጋዊ ነጋዴዎች ታክስ ከፍለው ሲሸጡ፣ ደረሰኝ የማይሰጡት ግን ታክስ ስለማይከፍሉ ገበያውን ያዛባሉ። ይህ ደግሞ በታማኝ ነጋዴዎች ላይ ጉዳት ያደርሳል

ጷግሜን 2 የማንሠራራት ቀን
07/09/2026

ጷግሜን 2 የማንሠራራት ቀን

07/09/2026

''ህብረተሰቡ ደረሰኝ የመጠየቅና የመቀበል ሕጋዊ መብት አለው።'' የደ/ ኢ/ ክ/ ገቢዎች ቢሮ ም/ኃላፊና የታክስ ስርዓት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ደግፈ

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልላዊ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛልርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልል አቀፍ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በወላይታ ...
07/09/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልላዊ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት ክልል አቀፍ የከፍተኛ አመራሮች መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ በመካሄድ ላይ ሲሆን፤ መድረኩ በዋናነት በክልሉ መንግስት የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ አፈጻጸም፤ በ2019 መሪ ዕቅድ እንዲሁም የቀጣይ 5 ዓመት ጠቋሚ ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያ የሚመክር ይሆናል፡፡

የ2018 ዓ.ም ማጠቃለያ የሆነው ይሄው የአመራሮች መድረክ፤ የክልሉ መንግስት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለክልላዊ እና ሀገራዊ የሰላም፤ የልማትና የብልጽግና ራዕይ ስኬት ባከናወናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት የተመዘገቡ ውጤቶችን በመገምገም፤ ለ2019 የላቀ አፈጻጸም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

መድረኩ የዞን፤ የረጂዮ ፖሊስ ከተሞች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት የበጀት ዓመቱን አጠቃላይ የተግባራት አፈጻጸም መሠረት ያደረገ የምዘና ውጤት ዙሪያም የሚወያይ ሲሆን፤ ይህም በክልሉ በየደረጃው ያሉ መዋቅሮችና አስፈጻሚ ተቋማት የማስፈጸም አቅም በማጎልበት ለተሻለ ውጤት ለማብቃት የጎላ ፋይዳ የሚኖረው ይሆናል፡፡

በተጨማሪም መድረኩ የክልሉን የብልጽግና ፍኖቴ ካርታ፤ ሀገራዊ የዘላቂ ልማት ግቦችንና የሁለንተናዊ ብልጽግና ራዕይ ማዕከል አድርጎ በተዘጋጀ የክልሉ መንግስት የቀጣይ 5 ዓመት ጠቋሚ ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያም የሚመክር ከመሆኑም በላይ የክልሉ አስፈጻሚ ተቋማት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ የግብ ስምምነት የሚፈራረሙ ይሆናል፡፡

በመድረኩ የተገኙት ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በተለይ የክልሉ መንግስት የትኩረት አቅጣጫ በሆኑ ቁልፍ የልማት ዘርፎችና ሀገራዊ የልማት ኢኒሼቲቮች የውጤት ዘላቂነትን ከማረጋገጥ ባሻገር በላቀ አፈጻጸም የክልሉን ሕዝብ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ቀጣይ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ ለአመራሩ ስምሪት የሚሰጡ ይሆናል፡፡

በዚህም መድረኩ የአመራሩን የዓላማ፤ የአመለካከትና የተግባር አንድነት በማጠናከር ለቀጣይ የዘላቂ ሰላምና ልማት ተልዕኮ ያዘጋጃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የክልሉ መንግስት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ ህዝብ ግንባር ቀደም ተሳትፎ በሁሉም የልማት አውታሮች ዘርፍ ብዙ ውጤታማ የሰላም፤ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በመስራት አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉ ይታወቃል፡፡

በክልሉ በዚሁ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት፤ በተሻለ የተግባር አፈጻጸም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ መዋቅሮች እና የክልል አስፈጻሚ ተቋማት መድረኩ ዕውቅና ይሰጣል ተብሎም ይጠበቃል፡፡

በመድረኩ ከርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ገ/መስቀል ጫላ፤ የክልሉ አስተባባሪ አካላት፤ አፈ ጉባኤዎች፤ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፤ የዞን ዋና አስተዳዳሪዎችና የፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከፍተኛ አመራሮች፤ የረ/ፖ/ከተማ ከንቲቦችን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ አመራሮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸዉን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መረጃ ያመላክታል፡፡

ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀንከተስፋ ወደ እመርታ!ሀገራችንን ከተረጂነት ለማላቀቅና በራሷ አቅም የምትቆም ኢትዮጵያን ለመገንባት የተያዘው የእመርታ አቅጣጫ ከቃል ባሻገር ወደ ተጨባጭ ተግባር እየተ...
06/09/2026

ጳጉሜ 1 — የእመርታ ቀን

ከተስፋ ወደ እመርታ!

ሀገራችንን ከተረጂነት ለማላቀቅና በራሷ አቅም የምትቆም ኢትዮጵያን ለመገንባት የተያዘው የእመርታ አቅጣጫ ከቃል ባሻገር ወደ ተጨባጭ ተግባር እየተቀየረ ይገኛል።

በምግብ ራስን መቻል፣ ምርታማነትን ማሳደግ፣ የሥራ ዕድል መፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን ወደ ምርት መቀየር የዚህ የእመርታ ጉዞ ዋና አቅጣጫዎች ናቸው።

ይህንን ሀገራዊ ጉዞ በክልላዊ ደረጃ በማጠናከር፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የሕዝቡን አቅምና ያሉትን የልማት ሀብቶች በማስተሳሰር ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየሠራ ይገኛል።

በግብርናና መስኖ፣ በቡናና ኮረሪማ፣ በኢንዱስትሪና ንግድ፣ በውሃና መንገድ ልማት፣ በትምህርትና ጤና፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በቱሪዝምና ባህል፣ እንዲሁም በበጎ ፈቃድና የሕዝብ ተሳትፎ የተደረጉ ጥረቶች የእመርታው ጉዞ ተጨባጭ አካላት ናቸው።
እመርታ የአንድ ቀን ውጤት ሳይሆን፣ በየቀኑ በተግባር የሚፈጠር ውጤት ነው።

በአዲሱ ዓመትም የተጀመረውን የእመርታ ጉዞ የበለጠ ለማፋጠን፣ ክልላዊ አንድነታችንንና ትብብራችንን በማጠናከር ሁላችንም የየበኩላችንን አስተዋጽኦ በማበርከት ለእመርታው ጉዞ መረባረብ ይጠበቃል።

06/09/2026

ኢ-ታክስ

Address

Limat
Arba Mintch

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Region Revenue Bureau /የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share