Menjar Shenkora werda Communication

Menjar Shenkora werda Communication በሰሜን ሸዋ ዞን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽ

ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መርጣለች! ሀገራችን ባከናወነችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረዣዥም የመራጮች ሰልፍ መስተዋሉ፣ ዜጎች በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ስለ...
03/06/2026

ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መርጣለች!

ሀገራችን ባከናወነችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረዣዥም የመራጮች ሰልፍ መስተዋሉ፣ ዜጎች በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ስለመሆናቸው ጉልህ ማሳያ ነው።

የዕድሜ መግፋት ፣ የጤና ሁኔታ መታወክ፣ አራስነት፣ ከቤት መቆየትን የግድ ያለው አሰገዳጅ ክስተት ሳይበግራቸው ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ይበጀኛል ያሉትን መርጠዋል።

አንድ ድምፅ ዋጋ እንዳለው በመረዳት ከሌሊት እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

በምርጫው ዕለት የታዩ ረዣዥም የመራጮች ሰልፎች የሕዝብ የፖለቲካ ፍላጎት እና የዴሞክራሲ ተሳትፎ መጉላትን የሚያሳዩ ናቸው።

7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም የተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ ።‎‎የምንጃር ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም የተጠናቀቀ መሆኑን ገለጸ ። ‎‎የምንጃር ወረዳ ፓሊስ አዛዥ  ኢንስፔክ...
03/06/2026

7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም የተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ ።

‎የምንጃር ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም የተጠናቀቀ መሆኑን ገለጸ ።

‎የምንጃር ወረዳ ፓሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ዘመን አስቻለው እንዳሉት በወረዳው ባሉ ምረጫ ጣቢያዎች በነቂስ በመውጣት ማህበረሰቡ ይበጀኛል፣ ይመራኛል ፣ ይጠቅመኛል ሰላምና ልማቱን ያመጣልኛል ያለውን በሰላማዊና በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲመርጥ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠርና በምርጫው የተሳተፉ ታዛቢዎች አስፈጻሚዎች ፣መራጮችንና አስመራጮችን ሰላምና ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲካሔድ ቅድመ ስራዎች የተሰሩ በመሆኑ በሰላም እንዲጠናቀቅ አድርጎታል ብለዋል ።

‎ አክለውም ምረጫውን ለማደናቀፍ የውጭም የውስጥም የጠላት ሀይል አቅደው ቢንቀሳቀሱም ምንም አይነት ችግር ሳይፈጠር በሰላም ማጠናቀቅ ተችሏል ሲሉ ገልጸዋል ።

‎በተለይ ደግሞ ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የ5ተኛ ክፍለ ጦር ሪፐፕሊካን ጋርድ አመራር ና አባላት ፣ለሰላም አስከባሪ እና ፖሊስ አባላት በሙሉ ለዚህ ምርጫ መሳካት ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ሰአት ድረስ ለተደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።

‎በመጨረሻም የምንጃር ወረዳ ህዝብ ላሳዩት ድጋፍ ምረጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተደረገው ትብብር ከፋ ያለ ምስጋናቸውን በማቅረብ በቀጣይም ለሚሰሩ ስራዎች በተለመደው አግባብ ከጎናችን እንድትሆኑ በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፤ የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ  ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ፤

የአውሮፓ ኅብረት እና ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ኤምባሲ ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ያካሄደችው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ መስጠት ሂደት በስኬት በመጠናቀቁ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ብሏል።

ለዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ ለሲቪል ማኅበራት ታዛቢዎች፣ ለበጎ ፈቃደኞች፣ ለምርጫ አስፈጻሚዎች እና ምርጫው ስኬታማ እንዲኮን ጊዜያቸውን ለሰጡት ሁሉ ያላውን አድናቆት ገልጿል።

የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) የታዛቢ ቡድኖች የነበራቸውን አስተዋጽኦ በበጎ እንቀበላለን ነው ያለው።

የአውሮፓ ኅብረትም ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መካሄዱን በደስታ እንቀበላለን ብሏል።

​ ለምርጫ መሳካት አስተዋጽዖ ያበረከቱትን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን፣ የምርጫ አስፈጻሚዎችን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ዕጩ ተወዳዳሪዎችን እና የሲቪል ማኅበራት ተዋናዮችን ጥረት እናደንቃለን ነው ያለው።

​የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን ( ኢጋድ) እንደ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች የተጫወቱትን ወሳኝ ሚና እንገነዘባለን ብሏል። የታዛቢዎችን ሪፖርት በጉጉት እንደሚጠብቅም አስታውቋል።

​በግንቦት 24 ቀን ምርጫ ማካሄድ ያልቻሉ ሁሉም የምርጫ ክልሎች ምርጫውን የማካሄድ ዕድል እንደሚያገኙ ያለውን ተስፋም ገልጿል።

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁየአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡ምርጫውን አ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና መስጫ ቀናትን ይፋ አደረገ። የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ  ፈተናዎች የሚሰጡበት...
02/06/2026

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ የፈተና መስጫ ቀናትን ይፋ አደረገ።

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናዎች የሚሰጡበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል።

ከቢሮው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፤ የ6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 08 እስከ ዐ9/2018 ዓ.ም ይሰጣል። የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ደግሞ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ክልላዊ ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደባሕር ዳር: ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮ...
02/06/2026

"በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ አሸንፈዋል" ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ

ባሕር ዳር: ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ትናንት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ማካሄዷንና በአማራ ክልልም ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ፍትሐዊ ኾኖ መጠናቀቁን ገልጸዋል። በምርጫው ሀገር እና ሕዝብ ማሸነፋቸውን ጠቅሰዋል።

"ከጥንትም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ አሻራ ያሳረፈው የክልላችን ሕዝብ ትናንት ደግሞ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ያለውን ቀናዒ ፍላጎት ለዓለም አሳይቷል፤ በአማራ ክልል ምርጫ ማካሄድ ድምጽ ከመስጠት ባሻገር ነው" ብለዋል።

በክልላችን ምርጫ እንዳይካሄድ፤ ዜጎች መብታቸውን እንዳይጠቀሙ፤ በሕዝብ ድምጽ የተመረጠ መንግሥት እንዳይመሠርት፣ ክልሉ ሁልጊዜ በድህነት እና በግጭት ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጉ የውይይት እና የሰላም ተቃራኒ ኃይሎች ብዙ ጥረት ማድረጋቸውንም አንስተዋል። "ይሁን እንጂ በሕዝባችን አስተዋይነት እና በጸጥታ ኃይላችን ጀግንነት እነርሱ የፈለጉት ሳይኾን ሕዝብ የፈለገው ኾኗል" ነው ያሉት።

የክልሉ ሕዝብ ትናንት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ያሳየው ተሳትፎ፣ ጽናት እና ትዕግሥት የብልሃት እና የጥበብ ምንጭ መኾኑን ያሰመሰከረበት ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ምርጫው ሕዝቡ ለፈተና የማይበገር፤ በዛቻ እና በማስፈራሪያ የማይሰበር፣ ለሰላም እና ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የትኛውንም መስዋዕትነት እንደሚከፍል ያሳየበት እንደሆነ አስታውቀዋል። "የክልላችን ሕዝብ በትናንትናው ምርጫ የፖለቲካ ሥልጣን የሚገኘው በሕዝብ ድምጽ እንጂ በኃይል አለመኾኑን ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈበት ነው" ብለዋል።

የአማራ ክልል ሕዝብ ሰላም ወዳድነቱን፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ፈላጊነቱን፤ በሕግና በሕዝብ ይሁንታ ለሚጸና መንግሥት ቀናዒነቱን በግልጽ እንዳሳየም አብራርተዋል። ለዚህ ደግሞ የከበረ ምስጋናዬን ከጥልቅ አክብሮት ጋር ማቅረብ እወዳለሁ ነው ያሉት።

"ከቅድመ ምርጫ ጀምሮ ምርጫው በክልላችን በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረገው ለሀገር መከለካያ ሠራዊት፣ ለክልላችን የጸጥታ ኃይል፣ በየደረጃው ለሚገኙ የክልላችን አመራሮች እና ለመላው የክልላችንን ሕዝብ በራሴ እና በአማራ ክልል መንግሥት ስም የላቀ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል ርእሰ መሥተዳድሩ።

ለሀገር እና ለሕዝብ በአንድነት መሥራት ምን አይነት ስኬታማ ውጤት እንደሚያስገኝ ምርጫው ሕያው ምስክር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

በምርጫው ጫፍ ረገጥ አስተሳሰቦች እስከ አደረጃጀቶቻቸው በሕዝብ ደምጽ ከሽፈዋል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ አሸንፋለች ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ባስተላለፉት መልእክት።

በሰሜን ሸዋ የአረርቲ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ። ሀገር በባዕዳን ሴራ በተፈተነችበት፤ የታላቅነቷን ታሪካዊ በትረ ንግስና ...
02/06/2026

በሰሜን ሸዋ የአረርቲ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ አባተ የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ።

ሀገር በባዕዳን ሴራ በተፈተነችበት፤ የታላቅነቷን ታሪካዊ በትረ ንግስና ልትጨብጥ በምታደርገው ትጋት የቀኑ ጠላቶቿ ፣ ጉትቻ መሀል "የለም ሀገረ መንግስት አዋቅራለሁ" ያለው የከተማችን ሰላም እና ልማት ወዳድ ህዝባችን 7 ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ችግሮችን ተቋቁሞ በነቂስ በመውጣት ድምፁን በኃላፊነት መስጠት ችሏል የሚወክለውንም መርጧልና ክብር ይገባዋል።

ለዚህም ሰላማዊ ፣ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ መሳካት የአንበሳውን ድርሻ የተወጣው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን፣የፀጥታ መዋቅራችን ፣ ከክልል እስከ ቀበሌ በተዋረድ ያስተባበራችሁ አካላት፣የማህበረሰብ በጎ ፈቃደኞች፣ኮሚቴዎች እና ታዛቢዎች በጥቅሉ ሀገር የማቆም ተግባር በሰላም እንዲጠናቀቅ ዋጋ ለከፈላችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ከልብ የመነጨ ነውና ክበሩልን።
በከተማችን የተከናወነው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ እና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን የፅ/ቤቱ ሀላፊ አቶ አጥናፋ አባተ ገልፀዋል።

"ሰላማዊ ምርጫ፤ ለእውነተኛ የስልጣን ሽግግርና ሀገር መንግስት ግንባታ"

አቶ አጥናፉ አባተ
የአረርቲ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ

02/06/2026
የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና መሬት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሱራፌል ጌታነህ የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ። ሀገር በባዕዳን ሴራ በተፈተነችበት፤ የታላቅነቷን ታሪካዊ በትረ ንግስና ልትጨብ...
02/06/2026

የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና መሬት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሱራፌል ጌታነህ የምስጋና መልዕክት አስተላለፉ።

ሀገር በባዕዳን ሴራ በተፈተነችበት፤ የታላቅነቷን ታሪካዊ በትረ ንግስና ልትጨብጥ በምታደርገው ትጋት የቀኑ ጠላቶቿ ፣ ጉትቻ መሀል "የለም ሀገረ መንግስት አዋቅራለሁ" ያለው የወረዳችን ሰላም እና ልማት ወዳድ ህዝባችን 7 ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ችግሮችን ተቋቁሞ በነቂስ በመውጣት ድምፁን በኃላፊነት መስጠት ችሏል የሚወክለውንም መርጧልና ክብር ይገባዋል።

ለዚህም ሰላማዊ ፣ፍትሀዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ መሳካት የአንበሳውን ድርሻ የተወጣው የሀገር መከላከያ ሰራዊታችን፣የፀጥታ መዋቅራችን ፣ ከክልል እስከ ቀበሌ በተዋረድ ያስተባበራችሁ አካላት፣የማህበረሰብ በጎ ፈቃደኞች፣ኮሚቴዎች እና ታዛቢዎች በጥቅሉ ሀገር የማቆም ተግባር በሰላም እንዲጠናቀቅ ዋጋ ለከፈላችሁ ሁሉ ምስጋናዬ ከልብ የመነጨ ነውና ክበሩልን።

"ሰላማዊ ምርጫ፤ ለእውነተኛ የስልጣን ሽግግርና ሀገር መንግስት ግንባታ"

አቶ ሱራፌል ጌታነህ
የምን/ሸን/ወ/ም/አስተዳዳሪ እና መሬት ጽ/ቤት ኃላፊ

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ተሳትፎ እና በስኬት መጠናቀቁን የፓርቲ ተወካዮች ገለጹ።ደብረብርሃን፡ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ሸዋ ዞን በተለያዩ የምርጫ ክልሎች የተካሄደው የ...
02/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሕዝብ ተሳትፎ እና በስኬት መጠናቀቁን የፓርቲ ተወካዮች ገለጹ።

ደብረብርሃን፡ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ሸዋ ዞን በተለያዩ የምርጫ ክልሎች የተካሄደው የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የሕዝብ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ሰላማዊ፣ አካታች እና ፍትሐዊ በኾነ መንገድ መጠናቀቁን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች እና ዕጩ ተወዳዳሪዎች በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።

‎በመሀል ሜዳ የምርጫ ክልል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) በመወከል ለክልል ምክር ቤት ዕጩ ተወዳዳሪ ኾነው የቀረቡት ወይዘሮ ቤተልሔም አበራ እንዳሉት የምርጫ ሂደቱ ከቀደሙት ጊዜያት በተሻለ መልኩ አወዳዳሪ እና አካታች ነበር።

‎ሕዝቡ ለመምረጥ ያሳየው ትጋት እጅግ የሚበረታታ እንደነበር የጠቆሙት ተወዳዳሪዋ ፓርቲያቸው የምርጫውን ውጤት በጸጋ ለመቀበል ዝግጁ መኾኑን አረጋግጠዋል።

‎በተመሳሳይ በአረርቲ ምርጫ ክልል ለክልል ምክር ቤት ዕጩ ኾነው የቀረቡት የአርጎባ አንድነት ጄበርቲ ፓርቲ ሊቀመንበር ሐሰን ሙሐመድ በበኩላቸው መራጩ ሕዝብ ያለምንም ጫና ድምጽ መስጠቱን ተናግረዋል።

‎ፓርቲያቸው በአሁኑ ወቅት በየጣቢያው እየተለጠፈ ያለውን ውጤት በቅርበት እየተከታተለ መኾኑን የገለጹት ሊቀመንበሩ አጠቃላይ የምርጫውን ውጤት በጸጋ ለመቀበል፤ ካሸነፉ ለሕዝብ ለመሥራት፣ ከተሸነፉም ከአሸናፊው ፓርቲ ጋር በመተባበር ለመሥራት መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል።

‎የብልጽግና ፓርቲን በመወከል በሮቢት ምርጫ ክልል ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩት ኤሊያስ አበበ በበኩላቸው ምርጫው ሥልጣን እና ሕዝብን የማሥተዳደር ኀላፊነት የሚገኘው በሰላማዊ መንገድ እና በሕዝብ ፍላጎት ብቻ መኾኑን የሰሜን ሸዋ ሕዝብ በተግባር ያሳየበት የታሪክ ምዕራፍ መኾኑን ጠቁመዋል።

‎የብልጽግና ፓርቲም እንደ ሌሎቹ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ሁሉ የምርጫ ቦርድን ይፋዊ ውጤት በጸጋ ለመቀበል እየተጠባበቀ መኾኑን ገልጸዋል።

‎የፓርቲ ተወካዮቹ ለሂደቱ መሳካት ገለልተኛ በመኾን በብርታት ለሠሩ የጸጥታ መዋቅር፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ለሲቪክ ማኅበራት እና ለመላው ሕዝብ የላቀ ምሥጋና አቅርበዋል።

#ኢትዮጵያ

ዘጋቢ፦ ደጀኔ በቀለ

Address

Arerti

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menjar Shenkora werda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Menjar Shenkora werda Communication:

Share