Menjar Shenkora werda Communication

Menjar Shenkora werda Communication በሰሜን ሸዋ ዞን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽ

ጳጉሜን 1 «የእመርታ ቀን»፦ የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ከተረጅነት ወደ አምራችነት እያደረገው ያለው ታሪካዊ ሽግግር«የኢትዮጵያ መንሰራራት» በሚል መሪ ቃል በድምቀት እየተከበረ የሚገኘውን የጳጉ...
06/09/2026

ጳጉሜን 1 «የእመርታ ቀን»፦ የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ከተረጅነት ወደ አምራችነት እያደረገው ያለው ታሪካዊ ሽግግር

«የኢትዮጵያ መንሰራራት» በሚል መሪ ቃል በድምቀት እየተከበረ የሚገኘውን የጳጉሜን 1 «የእመርታ ቀን» ምክንያት በማድረግ፣ የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ሀገራችን ከተረጂነት ወደ አምራችነት እያደረገች ያለውን ታሪካዊ ሽግግር የሚያበስር ሰፊ የመስክ ግምገማና ምልከታ አካሄደ።

በምልከታው መርሃ ግብር በጨረቻ ቀበሌ በክላስተር እና በምርጥ ዘር የለማው፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራበት የሚገኘው ሰፊ የስንዴ ሰብል በማዕከላዊነት ተጎብኝቷል። የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካል ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ የኔነሽ አንበሉ በአረንጓዴው አሸብርቆ የሚታየው ይህ ሰብል የወረዳውን አምራችነትና የምግብ ዋስትና የማረጋገጥ ራዕይ በተግባር የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ፣ የህዝባችንን የጽናት ጉዞ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ከግብርናው የልማት ስራ ጎን ለጎን፣ ኢንተርፕራይዝ ላይ ማተኮር ለዘላቂ ፈጠራና ውጤታማነት መሰረት መሆኑ ይታመናልና በባልጪ ከተማ በሚገኘው የመንግስት የዕድል ማዕቀፍ የተደራጁ የእንጨት ውጤቶች ማምረቻ እና ሌሎችም ማዕከላት ተጎብኝተዋል። በዚሁ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ላይ የተሰማራው ሞዴል መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ የዕለቱን የበዓል ስሜት በማስተጋባት የኢትዮጵያን የዕድገትና የብልጽግና ጉዞ በተግባር አሳይቷል።

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!!ጳጉሜን የአሮጌው ዓመት መደምደሚያ፣ የአዲሱ ዓመት መነሻ ነው። አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ እንቀበላለን።በፈጠራና በፍጥነት በታጀበው ሀገራዊ ሪፎርም፣ ...
06/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት!!

ጳጉሜን የአሮጌው ዓመት መደምደሚያ፣ የአዲሱ ዓመት መነሻ ነው። አዲሱን ዓመት በአዲስ ተስፋና በአዲስ ራዕይ እንቀበላለን።

በፈጠራና በፍጥነት በታጀበው ሀገራዊ ሪፎርም፣ ኢትዮጵያ ከአዝጋሚ ዕድገት ወደ እመርታዊ ለውጥ እየተሸጋገረች ትገኛለች።

የመደመር መንግስት እሳቤ የቀደሙ ድሎችንና ወረቶችን ማስቀጠል ፣ ጉድለቶችን ማረምና አዳዲስ ፈጠራዎችን ማስፋት ነው። በባለፉት ዓመታት በሁሉም ዘርፍ እንደ ሀገር፣ ክልልና ዞን እንዲሁም ከተሞቻችን ድረስ የተመዘገቡት ስኬቶች የዚህ ማሳያ ናቸው።

የዘንድሮውን የጷጉሜን ቀናት ስያሜ የመጀመሪያው ቀን የሆነውን እመርታ ቀንን የምናከብረዉ የጀመርነዉን የከፍታ ጉዞ በማላቅ እና በማጽናት የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ነው፡፡

ይህ እመርታም በተጨባጭ ውጤቶች ተገልጧል። በለውጡ ስርዓት እመርታዊ ለውጦችን ሀገራችን አስመዝግባለች፡፡ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊ መንገዳችን ነው። እንደ ሀገር ከተረጂነት ለመላቀቅ የምናደርገው ጉዞ ውጤት አምጥቶ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ስንዴ አምራች ሆነን በምግብ ራስን ለመቻል የወጠንነው ጉዞ ፍሬ እያፈራ ነው።

በሀገር ደረጃ ተረጂነትን በመቀነስ በምግብ ራስን የመቻል ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ስኬት ከግብ ለማድረስ በዞናችን ትኩረት በመስጠት ተግባራት እየተከናወኑ ነው። በዞናችን የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ በተቀረፁት ፍኖቶችና ፓኬጆች ልዩ ትኩረት ተይዞ እየተሠራ ሲሆን በዚህ አመትም ከ1119 ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈን ችለናል።

ከ152 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ የተሰባሰበና መጋዘን በመገንባት እህል የመከዘን ሥራ እየተሠራ በመሆኑ ይህንን ተግባር ጥር 9/2019 ተረጅነት በማስቀረት በራስ አቅም ለመሸፈን ዞኑ በትኩረት እየሰራ ነው።

ሀገራችንም ወደተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ውስጥ ገብታ ያለመችዉን አሳክታለች፡፡ የተረጋጋ ማክሮ-ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ተወዳዳሪነትና የገበያ ድርሻ ማሳደግ፣ የማዕድን ዘርፉን ዐቅም እና ሕጋዊ ሥርዐት ማጠናከር፣ የቱሪዝሙን የኢኮኖሚ ድርሻ ማላቅ፣ ዲጀታላይዜሽንን ማስፋፋት እና የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራዉ ትኩረት የተሰጣቸዉና የተፈፀሙ ናቸው፡፡

በመኸርና በበጋ መስኖ፣ በተረጂነት ቅነሳና ራስን በምግብ የመቻል ሉዓላዊነት፣ በሌማት ትሩፋት እና በአረንዴ ዐሻራ በልዩ ትኩረት የተሠራበት ግብርና እመርታዊ ስኬት ተመዝግቦበታል፡፡ ለማክሮ ኢኮኖሚዉ መረጋጋት ከመፍጠሩም ባሻገር ለዓለማቀፍ ገበያ ምርቶች መቅረባቸውና የውጭ ምንዛሬ ማስገኘታቸው ተጠቃሽ ነው። ቡና፣ ማንጎ፣ የቅባት እህሎች ችና ሌሎችም በስፋት ኤክስፖርት መደረግ ጀምረዋል፡፡

በሥጋ እና እንቁላል አቅርቦትም ከፍተኛ መሻሻል ታይቷል፡፡ የኢንዱስተሪዎች የማምረት ዐቅም በእጅጉ ተሻሽሏል፡፡ አዳዲስ ኢንቨስትመንት በዞኑ ተመዝግበዋል። ተኪ ምርቶችን በከፍተኛ መረጠን እያመረቱ ነው፡፡ በዓለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ተፈላጊ ምርቶችን በማምረትም ኤክስፖርት እያደረጉ በመቶ ሚሊዮኖች ዶላር ማስገባት ጀምረዋል፡፡

የከተሞች መሠረተ ልማቶች እየዘመኑ መምጣት፣ የኮሪደር ልማት በበርካታ ከተምችና ገጠር ቀበሌዎች መተግበራቸው፣ የአረንጓዴ አሻራ ስራችን በሶፋትና በመጠን ጨምሮ መተግበሩ ተጨማሪ ማሳያዎች ናቸው።

ኢትዮጵያ በአሏት የማዕድንና የመስሕብ ጸጋዎች ልክ እንድትጠቀም ሰፊ ሥራ ተሠርቷል፡፡ የወርቅ ማውጣት ሥራዉንና ግብይቱን በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል እጅን በአፍ የሚያስጭን ስኬት ተመዝግቧል፡፡

ከዚህ ቀደም በዓመት ይገኝ ከነበረዉ በብዙ እጥፍ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክቀርቧል፡፡ የቱሪዝም መዳረሻዎች በእጅጉ ተስፋፍተዋል፤ ለጎብኝዎች ምቹ ተደርገዋል፡፡የኮንፈረንስ ቱሪዝም ባልተለመደ መልኩ አድጎ በዓመቱ በርካታ ዓለማቀፍ ጉባኤዎች ተመዝግበዋል፡፡

እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ ያለመችውን የብልፅግና ጉዞ ለማሳካትና ለማንሰራራት መሰረት ለመጣል ያስቻሉዋት አስደማሚ ስኬቶች ናቸው፡፡ ስኬቶቹ ሁሉ ታሪክ ቀያሪ አመርታዎች ናቸው፡፡

በመሆኑም የተጀመሩ እመርታዊ ስኬቶችን አጠናክሮ ለመቀጠልና የኢትዮጵያን ርዕይ ወደሚጨበጥ ብርሃን ለማሸጋገር ጳጉሜን 1 የእመርታ ቀን ተብሎ ተሰይሟል፡፡ በየደረጃው የተመዘገቡ ስኬቶችን በማሳወቅ ለቀጣይ መሠረት የሚጥል መነሳሳትን እንፍጠር።

የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የጳጉሜን ቀናት በሰፊው ዝግጅት ሊያከብር መሆኑን አስታወቀ ።የሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የዘንድሮውን የጳጉሜን ቀናት በይፋ ለማክበር የሚያስችሉ ሁነቶችን አ...
06/09/2026

የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የጳጉሜን ቀናት በሰፊው ዝግጅት ሊያከብር መሆኑን አስታወቀ ።

የሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የዘንድሮውን የጳጉሜን ቀናት በይፋ ለማክበር የሚያስችሉ ሁነቶችን አቅዶ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል።

እያንዳንዱ የጳጉሜን ቀን የሚከተሉትን ይዘቶችና የተለዩ መርሃ ግብሮች ይዞ ይከበራል ፦
ጳጉሜ 1 – የእምርታ ቀን (የምግብ ሉዓላዊነትና ምርታማነት) ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር ተያይዞ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋጡ ተግባራት የሚከናወኑበት ዕለት ነው። በየአካባቢው ከተረጅነት ወደ ምርታማነት የተደረገውን ሽግግር የሚያሳዩ የሰብል ማሳዎች ጉብኝት ይደረጋል ብለዋል።

ጳጉሜ 2 – የማንሰራራት ቀን (ልማትና ኢኒሼቲቮች) በተለያዩ አከባቢዎች የተሰሩ የልማት ፕሮጀክቶች የሚጎበኙበት እና የፓርቲ ኢኒሼቲቭ ተግባራት አፈጻጸም የሚገመገምበት ቀን እንደሆነም ተገልጿል።

ጳጉሜ 3 – የፅናት ቀን (የፀጥታ ሀይላት ክብርና አገር ፍቅር) የፀጥታ ሀይሎችን የሚደግፍና የሚያጀግን ቀን ነው። በከተሞች መስመሮች የሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ፣ በአደባባይ በመሰለፍ ብሔራዊ መዝሙር መዘመር እና ባንዲራ የመስቀል ስነ-ሰርዓት ይከናወናል ብለዋል።

ጳጉሜ 4 – የህብር ቀን (አብሮነትና ሰው ተኮር ስራዎች) አብሮነትን፣ መረዳዳትን እና ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ስራዎች ይከናወናሉ። በተለይም ለችግረኞች እና ለድሃ ድሃዎች ድጋፍ የሚደረግበት ሰው ተኮር ስራዎች የሚሰሩበት እንደሆነ ገልፀዋል።

ጳጉሜ 5 – የነገ ቀን (ዲጂታል ትውልድና የወደፊት እይታ) ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር የተያያዙ ተግባራት የሚከናወኑበት ነው። ወጣቶች በ«ኢትዮ ኮደርስ» (Ethio Coders) መርሃ ግብር ላይ ግንዛቤ እንዲያገኙ ይደረጋል፤ እንዲሁም የ«ሞሰብ አንድ ማዕከል» ግንባታ የጀመሩ አካላት ጉብኝት ይካሄዳል ብለዋል።

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በሚገኙ ሁሉም ቀበሌዎች እነዚህ አምስቱም የጳጉሜን ቀናት ህዝብን ባሳተፈ መልኩ በልዩ ትኩረት ይተገበራሉ ።

የመንግሥትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቀሉ፤በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ ምስራቃዊ ቀጠና ከበለስ እስከ አጣምታና መረባ አካባቢዎች ታጥቀዉ  በጫካ ውስጥ ሲንቀሳ...
05/09/2026

የመንግሥትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ታጣቂዎች ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቀሉ፤

በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ ምስራቃዊ ቀጠና ከበለስ እስከ አጣምታና መረባ አካባቢዎች ታጥቀዉ በጫካ ውስጥ ሲንቀሳቀስ የቆየውና ራሱን የ208ኛ ኮር የራስ ገብሬ ብርጌድ ብሎ የሚጠራዉ ታጣቂ ቡድን የሰላም አማራጭን በመምረጥ በሰላም ገብቷል።

በታጣቂዎች አጠራር በብርጌድ መሪው ዜናው ሃይለማርያም መሪነት የተደራጀው ይህ ኃይል፣ የሻለቃ አመራሮችንና የሻምበል መሪዎችን ጨምሮ አጠቃላይ 56 ታጣቂ አባላቱን ይዞ ወደ ሰላሙ ማህበረሰብ ተቀላቅሏል።

ቡድኑን ይዞት ከመጣው የጦር መሣሪያ ዝርዝር ውስጥ አንድ ስናይፐር፣ አንድ ብሬን እና የተለያዩ ነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች ይገኙበታል።

የአካባቢው ህብረተሰብ እና አመራሮች ታጣቂዎቹን በደማቅ ሁኔታ የተቀበላቸው ሲሆን በስነ-ስርዓቱ ላይ የዞን፣ የመከላከያ፣ እንዲሁም የወረዳ የፀጥታና የፖለቲካ አመራሮች ተገኝተዋል።

አማራ ክልል ኮሙኒኬሽን

05/09/2026

የበጋ መስኖ እርሻ፤ በምግብ ራሳችንን ለመቻል በሚደረገው ጉዞ ውስጥ የጸና መሰረትን የጣልንበት ምዕራፍ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የአዲስ አመት የበዓል ገበያ ድባብ በምንጃር አረርቲ በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ የ2019 ዓ/ም የአዲስ አመት የበዓል ገበያ ድምቅ ብሎ ውሏል። የከተማ አስተዳደሩ...
05/09/2026

የአዲስ አመት የበዓል ገበያ ድባብ በምንጃር አረርቲ

በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በአረርቲ ከተማ የ2019 ዓ/ም የአዲስ አመት የበዓል ገበያ ድምቅ ብሎ ውሏል።

የከተማ አስተዳደሩ እና የወረዳችን ህዝብ አዲሱን አመት በደስታ ለመቀበል በድምቀትና በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተጠባበቁ እንደሆነ በገበያ አካባቢዎች ላይ ያለው የገበያ ድባብ እንቅስቃሴ ያሳያል።

ህዝባችን ባህላዊ ቱውፊቱን ጠብቆ በልዩ ተስፋ አዲሱን አመት ለመቀበል የቅድመ ዝግጅት እና የበዓል ገበያ በሁሉም የግብይት ዘርፎች በመልካም ሁኔታ ተካሄደዋል።

መልካም አዲስ አመት !!

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በጎንደር ከተማ የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።በጉብኝቱ ከርእሰ መሥተዳድሩ በተጨማሪ የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተሳትፈዋል። ከፍተኛ የሥራ ኀ...
05/09/2026

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በጎንደር ከተማ የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።

በጉብኝቱ ከርእሰ መሥተዳድሩ በተጨማሪ የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተሳትፈዋል። ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎቹ ታሪክን ከዘመናዊት ጋር አስተባብሮ የተገነባውን የዞብል ፓርክ እና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ነው በምሽት ያላቸውን ገጽታ ተዘዋውረው የተመለከቱት።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በጎንደር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን ተናግረዋል። የጎንደር ከተማ ልዩ ምልክት በኾነው በታሪካዊው የቅዱስ ፋሲለደስ ባሕረ ጥምቀት ዙሪያ ገባ የተሠራው ፓርክ በአማረ ሁኔታ መልማቱን ተናግረዋል።

ልማቱ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት አንዱ አካል መኾኑን ገልጸዋል። ጎንደር ደግሞ የቱሪዝም ከተማ በመኾኗ ለጎብኝዎች ምቹ የማድረግ ሂደት መኾኑን ነው ያነሱት።

ፓርኩ ለቱሪዝም መዳረሻነት ኾኖ የሚያገለግል፣ ለመዝናኛም የሚኾን ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ በጎንደር የኮሪደር ልማት ከፒያሳ ቀጥሎ ትልቁ የመዝናኛ ማዕከል እንደኾነ ነው ያነሱት። አካባቢው ከአሁን በፊት ለጎብኝዎችም ኾነ ለነዋሪዎቹ የተመቸ አልነበረም፤ አሁን ግን ከባሕረ ጥምቀቱ በተጨማሪ ራሱን ችሎ ለጎብኝዎች መዳረሻ ኾኖ እንዲያገለግል ባማረ ሁኔታ ተገንብቷል ብለዋል።

በጎንደር የልማት እንቅስቃሴ የበለጠ እየሰፋ መሄዱን ገልጸዋል። ጎንደር በ2018 በጀት ዓመት ሥራ አፈጻጸም በክልሉ ከተሞች አንደኛ መውጣቷን ያስታወሱት ርእሰ መሥተዳድሩ በ2019 በጀት ዓመትም የበለጠ መሥራት እንዲቻል ያለመ ጉብኝት እንዳደረጉ አንስተዋል።

በተመለከቱት የልማት ሥራ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸውም ገልጸዋል።

ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ድንበር የለሽ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፤​የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ቡድን ከአማራ ክልል መንግ...
05/09/2026

ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ድንበር የለሽ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራ ማከናወን እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፤

​የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ አመራሮችና ባለሙያዎች ቡድን ከአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ጋር በባህርዳር ከተማ የልምድ ልውውጥ አደረጉ።

​በልምድ ልዉዉጥ መድረኩ የተገኙት የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሄኖክ ሙሉነህ እንደገለጹት፤ የአማራ ክልል የሀገራችን የቱሪዝም የስበት ማዕከልና ከራሱ አልፎ ለሀገር የሚተርፍ ትልቅ ሀብት ያለው ክልል ነው።

በባሕር ዳር ከተማ ተዘዋውረን የተመለከትናቸው የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ጸጋዎች ለሀገራችን የወደፊት የቱሪዝም እድገት ትልቅ ተስፋ የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የባህርዳር በለዉጥ ላይ ነች የከተማዋ የለዉጥ ጉዞም የብልጽግና ጉዟችን ዋነኛ ማሳያ ምልክት ነዉ ብለዋል።

​ሃላፊዉ ክልሉ ከነበረበት የጸጥታ ችግር ወጥቶ አሁን ትኩረቱን ልማት ላይ ማድረጉን በቆይታቸው መታዘባቸውን ገልጸው፤ በቀጣይ በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በጋራ እንደሚሠሩ አጋርነታቸውን አረጋግጠዋል።

​የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ትብለጥ መንገሻ በበኩላቸው፤ ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን ለመገንባት ሚዲያው ዋነኛ መሳሪያ ነዉ። ከሀረሪ ክልል ጋር የነበረውን የቆየ መልካም ግንኙነት እና የተግባራት አፈጻጸም ልምድ በመካፈልና በማዳበር፣ ለክልላችን እንዲሁም ለሀገር ገጽታ ግንባታ የሚጠቅሙ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል። የልምድ ልውውጡም ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና የነበሩ ክፍተቶችን ለማሻሻል የሚረዳ መሆኑን ጠቁመዋል።

​የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙሉነህ ዘበነ በበኩላቸው፤ የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ ከምናሳካባቸው ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ ዲጂታል ኮሙኒኬሽን መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህ የሚመጥን ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የሆነ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት አሁናዊ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ፤ የልምድ ልውውጡ በቀጣይ በጋራ ለሚከናወኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሥራዎች ጠንካራ መሠረት የጣለ ነውም ብለዋል።

 #ሸዋምንጃር ሸንኮራ ግብርናን በጥበብ ሲገልጸው እንዲህ ነው ።
05/09/2026

#ሸዋ
ምንጃር ሸንኮራ ግብርናን በጥበብ ሲገልጸው እንዲህ ነው ።

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ"ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ    የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን"በሚል መሪ ሀሳብ ከኮምቦልሻ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሄደ...
04/09/2026

በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ"ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን"በሚል መሪ ሀሳብ ከኮምቦልሻ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሄደ ።

ነሀሴ 29/2018 ዓ/ም(ምሸወመኮ)በሰሜን ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በኮምቦልሻ ቀበሌ “ ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ሀሳብ ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተካሂዷል።

የመወያያ ሰነዱን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ተክሉ አቅርበው በቀረበው ሰነድ ላይ መነሻ በማድረግ በሀገራዊ የሰላምና ወቅታዊ ሁኔታ ፣ በውጫዊ የስጋት ምንጮች ፣ ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋ ያስከተለውን ፖለቲካዊ ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች ዙሪያ በሰፊው መወያየት ተችሏል ።

በውይይቱ የተሳተፉ አካላትም በሰጡት አስተያየት ፣የሰላም ጥበቃና የሀገር አንድነት ለሁሉም የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ጠቁመው፤ህብረተሰቡ የፅንፈኝነትን አደጋ በመመከት ለሰላም መጠናከር ንቁ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግም አንስተዋል።

በመድረኩ ተሳታፊዎችም የሰላም ሁኔታን ለማስጠበቅ ፣ የፅንፈኝነትን አደጋ ለመከላከልና እነረደ ቀበሌ የገጠመንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ሊፈቱ የሚችሉት እንዲሁም ሌሎችም የልማት ሥራዎችን ለማፋጠን በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ሀሳቦችን አንስተዋል።

አቶ ዘካሪያስ ተክሉ በመድረክ ማጠቃለያው እንደገለጹት የሰላምና የልማት ሂደትን ለማስቀጠል የህብረተሰቡ አንድነትና ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ፣ አሁን ላይ የገጠመንን የውጭ የወረራ ስጋትንና የውስጥ የጽንፈኝነት አደጋን ለመቀልበስ ህዝባችን ከመንግስት ጎን በጋራ በመቆም የሰላምና የልማት ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበው፤ ውይይቱም ዘላቂ ሰላምን በማስፈን የልማት ጥረቶችን ለማጠናከር በጋራ መስራት እንደሚገባም በማሳሰብ ተጠናቋል።

መድረኩን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ ተክሉ፣ የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ገንዝብ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አማረ ሙሉጌታ እና የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ሀምሳለቃ ከፍያለው ደጀኔ በጋራ በመሆን መርተውታል።

በውይይት መድረኩ ላይ ሌሎችም የወረዳው አመራሮችና የጸጥታ መዋቅር ተገኝቷል።

Address

Arerti

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menjar Shenkora werda Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Menjar Shenkora werda Communication:

Shortcuts

Share