Athlete Tirunesh Dibaba Sport Training Center-Assela

Athlete Tirunesh Dibaba Sport Training Center-Assela To produce qualified, competent and victorious Athletes in the world championship. Government Organization

የቀድሞ የማዕከላችን ሰልጣኝ አትሌት ገመቹ ጎዳና በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ በ3000 ሜትር መሰናክል ውድድርን አሸነፈ!************ጷግሜ 1/2018 ዓ.ም | የማዕከላችን ኩራትና የቀድሞ...
06/09/2026

የቀድሞ የማዕከላችን ሰልጣኝ አትሌት ገመቹ ጎዳና በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ በ3000 ሜትር መሰናክል ውድድርን አሸነፈ!
************
ጷግሜ 1/2018 ዓ.ም | የማዕከላችን ኩራትና የቀድሞ ሰልጣኝ የሆነው አትሌት ገመቹ ጎዳና በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ በ3000 ሜትር መሰናክል ውድድር ድንቅ ብቃቱን በማሳየት የመጀመሪያ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ ሆኗል።

አትሌት ገመቹ ከፍተኛ ፉክክር በተደረገበት በዚህ ውድድር ርቀቱን በ8:08.67 ሰከንድ በመጨረስ በላቀ የበላይነት አንደኛ ወጥቷል።

ይህ ድል ለአትሌቱ የወቅቱን ምርጥ ብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከ12 ቀናት በፊት በፖላንድ ሲሌሲያ በተካሄደው የ3000 ሜትር መሰናክል ውድድርም አንደኛ በመውጣት ተመሳሳይ ድል ማስመዝገቡ ይታወሳል።

ማዕከላችን ያፈራውና የቀድሞ ሰልጣኛችን የሆነው አትሌት ገመቹ ጎዳና በዓለም አቀፍ መድረክ እያስመዘገበ ባለው አስደናቂ ውጤት ታላቅ ደስታ ይሰማዋል። ለአትሌታችን ገመቹ ጎዳና እንኳን ደስ አለህ እያለ፣ ለቀጣይ ውድድሮቹም ሙሉ ስኬትን ይመኛል!


---------------------------------------
ሳይንሳዊ ስልጠና ቀጣይነት ላላው ተተኪ አትሌቶች “
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://atdatc.edu.et
Email: [email protected]

የማዕከላችን ኮከቦች በ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ የሽልማት እጩነት ውስጥ በደመቀ ሁኔታ ተካተቱ!*************ነሃሴ 30/2018 | በኢ...
05/09/2026

የማዕከላችን ኮከቦች በ2018 የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ የሽልማት እጩነት ውስጥ በደመቀ ሁኔታ ተካተቱ!
*************
ነሃሴ 30/2018 | በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የፊታችን ማክሰኞ ጳጉሜ 3 ቀን 2018 ዓ.ም በኢሊሊ ሆቴል በሚካሄደው የክበቦች የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ የማዕከላችን ተጫዋቾች እና አሰልጣኝ በበርካታ ዘርፎች በኮከብነት በዕጩነት ቀርበዋል።

በ2018 የውድድር ዘመን ባሳዩት ድንቅ ብቃት እና አስደናቂ ተሳትፎ የሚከተሉት የማዕከላችን አባላት በእጩነት ተመርጠዋል፡

👉 በኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ፡
# ኮከብ ተጫዋች እጩ፡ ሊዲያ ሰለሞን
# ኮከብ ግብ ጠባቂ እጩ፡ ኢትዮጵያ ዳንግ
# ኮከብ አሰልጣኝ እጩ፡ አሰልጣኝ ሰለሞን ገለታ
👉በኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ፡
# ኮከብ ተጫዋች እጩ፡ ፀጋአብ ኤልያስ

ስፖርተኞቻችን እና አሰልጣኛችን ለዚህ ትልቅ ስኬት እና የሽልማት እጩነት በመብቃታቸው ማዕከሉ የተሰማውን ታላቅ ደስታ እየገለጸ፣ በማክሰኞው የሽልማት ስነ-ስርዓት መልካም እድል እና አሸናፊነት ይመኛል!

29/08/2026
የማዕከሉ ሰልጣኝ አትሌት ዋቢ ወጂራ ለሀገራችን የብር ሜዳሊያ አስገኘ!🇪🇹*********ነሀሴ 20/2018| በኬንያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የአኖካ ዞን 5 ውድድር ሀገራችን ኢትዮጵ...
26/08/2026

የማዕከሉ ሰልጣኝ አትሌት ዋቢ ወጂራ ለሀገራችን የብር ሜዳሊያ አስገኘ!🇪🇹
*********
ነሀሴ 20/2018| በኬንያ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የአኖካ ዞን 5 ውድድር ሀገራችን ኢትዮጵያ በ1500 ሜትር የወንዶች የሩጫ ውድድር በማዕከሉ ሰልጣኝ ዋቢ ወጂራ የብር ሜዳሊያ እና በሴቶች 800 ሜትር አትሌት ነፃነት ሰለሞን የወርቅ ሜዳሊያ አግኝተዋል።

ይህንን ትልቅ ድል ለሀገራችን ያበሰሩት አትሌት ዋቢ ወጂራ በውድድሩ ላይ ድንቅ የሜዳ ላይ ብቃትና ፍጥነት በማሳየት 2ኛ ደረጃን በመያዝ የብር ሜዳሊያውን አሸናፊ ሲሆን በሴቶች 800 ሜ አትሌት ነፃነት ሰለሞን የወርቅ ሜዳሊያ ለሀገራቸው አስገኝተዋል።

አትሌት ዋቢ ወጂራ በማዕከሉ የ3ኛ ዓመት ሰልጣኝ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በማዕከሉ ውስጥ በከፍተኛ ትጋትና ዲሲፕሊን የስልጠና ሂደቱን በመከታተል ላይ የሚገኝ ተስፋ ሰጪ አትሌት መሆኑ ተገልጿል።

ማዕከላችን ለአትሌት ዋሚ ወጂራ እንኳን ደስ አለህ እያለ፣ ወደፊት በሚጠብቁት ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ውድድሮች ለላቀ ስኬትና ድል እንዲበቃ መልካም ምኞቱን ይገልጻል!
እንኳን ደስ አለን! 🇪🇹

---------------------------------------
ሳይንሳዊ ስልጠና ቀጣይነት ላላው ተተኪ አትሌቶች “
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://atdatc.edu.et
Email: [email protected]

26/08/2026

እና አካባቢው ምልመላ ነገ ይጀምራል

ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም
አካዳሚው በመጀመሪው ዙር ተደራሽ ያላደረጋቸውን የምልመላ ጣቢያዎች በሁለተኛ ዙር ለመመልመል ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።በዚሁ መሰረት
የአካዳሚው የቡድን_15 መልማዮች ነገ ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም እና አካባቢው ከተውጣጡ ታዳጊዎች መካከል በአትሌቲክስ፣ በወርልድ ቴኳንዶ፣ ቦክስ እና በእግርኳስ ስፖርት አይነቶች በሁለቱም ፆታ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ ስለሚያደርጉ እድሚያችሁ ከ17 አመት በታች የሆናችሁ ታዳጊዎች ከጠዋቱ 2:30 ሰአት ላይ ይዛችሁ በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳውቃለን።

ማስታወሻ ፦ አካዳሚው የሁሉንም መልማይ ልዑካን መዳረሻ በየጊዜው በማህበራዊ ድህረ-ገፃችን የምናሳውቅ መሆኑን እናሳውቃለን።

ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

26/08/2026

#የቡራዩ እና አካባቢው ምልመላ ነገ ይጀምራል

ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም

አካዳሚው በመጀመሪው ዙር ተደራሽ ያላደረጋቸውን የምልመላ ጣቢያዎች በሁለተኛ ዙር ለመመልመል ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።በዚሁ መሰረት
የአካዳሚው መልማዮች ነገ ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም #ከቡራዩ እና አካባቢው ከተውጣጡ ታዳጊዎች መካከል በአትሌቲክስ እና በእግርኳስ ስፖርት አይነቶች በሁለቱም ፆታ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ ስለሚያደርጉ እድሚያችሁ ከ17 አመት በታች የሆናችሁ ታዳጊዎች ከጠዋቱ 2:30 ሰአት ላይ ይዛችሁ በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳውቃለን።

ማስታወሻ ፦ አካዳሚው የሁሉንም መልማይ ልዑካን መዳረሻ በየጊዜው በማህበራዊ ድህረ-ገፃችን የምናሳውቅ መሆኑን እናሳውቃለን።
ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

26/08/2026

#የአሰላ እና አካባቢው #የእግርኳስ ምልመላ ነገ ይጀምራል

ነሀሴ 20/2018 ዓ.ም

አካዳሚው በመጀመሪው ዙር ተደራሽ ያላደረጋቸውን የምልመላ ጣቢያዎች በሁለተኛ ዙር ለመመልመል ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።በዚሁ መሰረት
የአካዳሚው መልማዮች ነገ ነሀሴ 21/2018 ዓ.ም #ከአሰላ እና አካባቢው ከተውጣጡ ታዳጊዎች መካከል #በእግርኳስ ስፖርት አይነት በሁለቱም ፆታ የእጩ ሰልጣኞች ምልመላ ስለሚያደርጉ እድሚያችሁ ከ17 አመት በታች የሆናችሁ ታዳጊዎች ከጠዋቱ 2:30 ሰአት ላይ ይዛችሁ በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ እናሳውቃለን።

ማስታወሻ ፦ አካዳሚው የሁሉንም መልማይ ልዑካን መዳረሻ በየጊዜው በማህበራዊ ድህረ-ገፃችን የምናሳውቅ መሆኑን እናሳውቃለን።
ለበለጠ መረጃ
ፌስቡክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100064708597717&mibextid=ZbWKwL
ቴሌግራም https://t.me/+0K6_bE7YFzU5YmY0
ድህረ ገፅ http://www.esacademy.gov.et/
ቲክቶክ www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy" rel="ugc" target="_blank">https://www.tiktokcom@ethiopiansportsacademy
"ወርቃማ የትውልድ ቅብብሎሽን እናረጋግጣለን"
”We Ensure the Golden Generational Continuity”

Address

Asella

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Athlete Tirunesh Dibaba Sport Training Center-Assela posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Athlete Tirunesh Dibaba Sport Training Center-Assela:

Shortcuts

Share