06/09/2026
የቀድሞ የማዕከላችን ሰልጣኝ አትሌት ገመቹ ጎዳና በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ በ3000 ሜትር መሰናክል ውድድርን አሸነፈ!
************
ጷግሜ 1/2018 ዓ.ም | የማዕከላችን ኩራትና የቀድሞ ሰልጣኝ የሆነው አትሌት ገመቹ ጎዳና በብራስልስ ዳይመንድ ሊግ በ3000 ሜትር መሰናክል ውድድር ድንቅ ብቃቱን በማሳየት የመጀመሪያ ደረጃን በመያዝ አሸናፊ ሆኗል።
አትሌት ገመቹ ከፍተኛ ፉክክር በተደረገበት በዚህ ውድድር ርቀቱን በ8:08.67 ሰከንድ በመጨረስ በላቀ የበላይነት አንደኛ ወጥቷል።
ይህ ድል ለአትሌቱ የወቅቱን ምርጥ ብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከ12 ቀናት በፊት በፖላንድ ሲሌሲያ በተካሄደው የ3000 ሜትር መሰናክል ውድድርም አንደኛ በመውጣት ተመሳሳይ ድል ማስመዝገቡ ይታወሳል።
ማዕከላችን ያፈራውና የቀድሞ ሰልጣኛችን የሆነው አትሌት ገመቹ ጎዳና በዓለም አቀፍ መድረክ እያስመዘገበ ባለው አስደናቂ ውጤት ታላቅ ደስታ ይሰማዋል። ለአትሌታችን ገመቹ ጎዳና እንኳን ደስ አለህ እያለ፣ ለቀጣይ ውድድሮቹም ሙሉ ስኬትን ይመኛል!
---------------------------------------
ሳይንሳዊ ስልጠና ቀጣይነት ላላው ተተኪ አትሌቶች “
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://atdatc.edu.et
Email: [email protected]