01/06/2026
የአቶ አሻድሊ ሀሰን መልዕክት
ሠኞ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም
***
ዴሞክራሲያዊ ምርጫ የህዝብ ሉአላዊነት እና ብቸኛ የሥልጣን ምንጭነት ማረጋገጫ ነው።
እነሆ የዘንድሮው 7ኛው አገርአቀፍ ምርጫ በዛሬው ዕለት እንደአጠቃላይ በመላው ሀገራችን በተለይ ደግሞ በክልላችን በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ሠለማዊ በሆነ መንገድ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በከፍተኛ መነቃቃት እየተካሄደ ይገኛል።
እኔም በአሶሳ ዞን በቡልዲግሉ ወረዳ ምርጫ ክልል በመገኜት ድምፄን ሰጥቻለሁ።
መላ የክልላችን ህዝብ የምርጫውን ፋይዳ ከልብ በመረዳት ድምፁን ለመስጠት ያሳየውን ከፍተኛ መነቃቃት እስከምርጫ ማጠናቂያ ሠዓት ድረስ በማስቀጠል እና ድምፁን በመስጠት በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታችን ውስጥ ታሪካዊ አሻራውን እንዲያስቀምጥ የአደራ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!!