06/09/2026
አጋርነቱ ያልተቋረጠው ኢቲዮ ቴሌኮም ለ2019 የትምህርት ዘመን "ለነገ ተስፋዎች" በሚል መሪ ሀሳብ 2,300 ደርዘን ደብተር ስርጭት በአሶሳ ከተማ አስተዳደር አጤጦ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ድጋፍ ማድረጉን ጀምሯል
------------- ------------- ------------- ---------------
(ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም ፤ አሶሳ) አጋርነቱ ያልተቋረጠው ኢቲዮ ቴሌኮም ለ2019 የትምህርት ዘመን "ለነገ ተስፋዎች" በሚል መሪ ሀሳብ 2,300 ደርዘን ደብተር ስርጭት በአሶሳ ከተማ አስተዳደር አጤጦ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ድጋፍ ማድረጉን ጀምሯል
27,600 ደብተር ለተማሪዎቾ ድጋፍ በዚህ ዓመት ኢቲዮ ቴሌኮም ድጋፍ ሲያደርግ ትውልድን በዕውቀት በክህሎትና በአመለካከት ለማብቃት ሃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኢቲዮ ቴሌኮም ምዕራብ ምዕራብ ሪጅን ሃላፊ አቶ ጥላሁን እጅጉ ገልጸዋል።
2,4 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የተማሪዎች መማሪያ ደብተር በክልሉ በሶስቱም ዞኖች ፣ በአሶሳ ከተማ አስተዳደርና በማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ ለሰባት ትምህርት ቤቶች ከ2,300 ተማሪዎች በላይ ድጋፍ ይደረጋል ተብሏል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ተወካዮች ፣ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ የወረደ ሁለት ዋና አስተዳዳሪ በደረዲን አህመድ ፣ የትምህርት መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ጎጃም አያናና የአጤጦ ቀበሌ አመራሮችና መምህራን ተገኝተዋል።
በዛሬውም ዕለትም በአሶሳ ከተማ አስተዳደር በአጤጦ ትምህርት ቤት ለ350 ተማሪዎች የመማሪያ ደብተር ኢቲዮ ቴሌኮም ምዕራብ ምዕራብ ሪጅን ድጋፍ አድርጓል።
ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሰ ሁሉም ህጻናት በትምህርት ገበታ ላይ እንዲገኙ ብቻ አይደለም ፤ የዓመቱንም ትምህርት ተምረው እንዲያጠናቅቁ አቶ በደረዲን መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፤ የኢቲዮ ቴሌኮም ምዕራብ ምዕራብ ሪጅን ለዳረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
ተማሪዎች መስከረም 5/2019 ዓ.ም ትምህርት እንደሚጀመር አውቀው በትምህርት ገበታ ተገኝተው እንዲማሩ ያሳሰቡት የትምህርት መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ጎጃም አያና የኢቲዮ ቴሌኮም ምዕራብ ምዕራብ ሪጅን ሁል ጊዜ አጋራችን ነው እናመሰግናለን ብለዋል።
ያልተቋረጠ የሰባት ዓመት የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍና መሰል ጊዜውን የዋጀ የዲጂታል ቴክኖሎጂና የ2018 ዓ.ም የሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተናና በቅርበት በማገዝ ትምህርቱን ለማዘመን ኩባኒያቸው በጉልህ እየተሳተፈ መሆኑን የገለፁት የኢቲዮ ቴሌኮም ምዕራብ ምዕራብ ሪጅን ሃላፊ አቶ ጥላሁን እጅጉ ሲሆኑ "የነገ ተስፋዎች" በሚል መሪ ሀሳብ የተደረገው መማሪያ ደብተር አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።
10,000 ደብተር "ለህብር ቀን" ከወዲሁ ተጀምሯል። የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪና የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል። የዘገበው የቢሮው ኮሙኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው።