ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ስፖርት ኮሚሽን Benishangul Gumuz Sport Commission

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ስፖርት ኮሚሽን Benishangul Gumuz Sport Commission

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ስፖርት ኮሚሽን Benishangul Gumuz Sport Commission to dissiminate sport information to the people

የክረምት በጎ አድራጎት ስፖርታዊ ስልጠና በአሶሳ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የክረምት በጎ አድራጎት እንቅስቃሴ አካል የሆነዉ በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ለታዳጊ ህፃናት እየተሰጠ ያለው ስልጠና...
02/09/2026

የክረምት በጎ አድራጎት ስፖርታዊ ስልጠና
በአሶሳ
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም
የክረምት በጎ አድራጎት እንቅስቃሴ አካል የሆነዉ በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ለታዳጊ ህፃናት እየተሰጠ ያለው ስልጠና በአሶሳ ከተማ ሻንጉል ስቴዲየም ምልከታ ተደረገ።
በምልከታው የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስፖርት ኮሚሽን የውድድርና ስልጠና ዳይሬክቶሬት አቶ አጠይብ መሀመድ እና በተለያዩ የስፖርት ዓይነቶች ታዳጊዎችን በማሰልጠን ላይ የሚገኙ አሰልጣኞች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የስልጠናው አፈጻጸም፣ የታዳጊ ህፃናት ተሳትፎ እና የስፖርት ችሎታ እድገት ተመልክቷል።
የክረምት ስፖርታዊ ስልጠናው ታዳጊዎች ክረምታቸውን በአግባቡ እንዲያሳልፉ፣ የስፖርት ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ እና ለወደፊት የሀገር ስፖርት ልማት የሚያገለግሉ ተስፋ ያላቸው ስፖርተኞችን ለማፍራት የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

02/09/2026

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የTelegram group

ሪከርድ ተመዘገበ በኤፈንጅ ባኬ             ከነሀሴ 23-30/2018 ዓ.ም  ጀምሮ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ ክብደት ማንሳት ሻምፒዮና ላይ ክልላችንን በመወከል እየ...
02/09/2026

ሪከርድ ተመዘገበ
በኤፈንጅ ባኬ

ከነሀሴ 23-30/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ ክብደት ማንሳት ሻምፒዮና ላይ ክልላችንን በመወከል እየተካሉ የሚገኙት የስፖርት ልዑካን አባላት በ 26/12/18 ዓ.ም በተካሄዱ ውድድሮች ላይ ተጨማሪ ውጤት ተመዝግቧል። በሴቶች 61 ኪ.ግ. ምድብ/ካታጎሪ በኤፈንጅ ባኬ የወርቅ ሜዳሊያ የተመዘገበ ሲሆን ከዚህ ቀደም በግሏ ተይዞ የነበረውን የሀገራችንን የሴቶች የክብደት ማንሳት ውድድር ሪከርድ በማሻሻል የውድድሩ ኮከብነቷን አስመስክራለች እንዲሁም በወንዶች 95ኪ.ግ ምድብ/ካታጎሪ በአልፈላ ኢብራሂም የነሀስ ሜዳሊያ ለማስመዝገብ ተችሏል።

 #የኮሚሽኑ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሮክቶሬት የክፍሉን 2019 የኮሙኒኬሽን እቅድ እየከለሰ ነው!
02/09/2026

#የኮሚሽኑ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሮክቶሬት የክፍሉን 2019 የኮሙኒኬሽን እቅድ እየከለሰ ነው!

ማስታወቂያ የቤ/ጉ/ክ እግር ኳስ ፌደሬሽን በክልሉ ለሚገኝ የክለብ እና የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት እግር ኳስ አሰልጣኞች የCAF 'D' ደረጃ  እና የCAF 'C' ደረጃ የአሠልጣኝነት ስልጠና ለ...
02/09/2026

ማስታወቂያ

የቤ/ጉ/ክ እግር ኳስ ፌደሬሽን በክልሉ ለሚገኝ የክለብ እና የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክት እግር ኳስ አሰልጣኞች የCAF 'D' ደረጃ እና የCAF 'C' ደረጃ የአሠልጣኝነት ስልጠና ለማሠጠት በዝግጅት ላይ የሚገኝ ሲሆን መስፈርቱን የምታሟላ አሠለጣኞች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

የኢትዮጵያ ከ23ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ተጋጣሚ የነበረችው ዩጋንዳ ከውድድሩ መውጣቷን ገለጸች።የኢትዮጵያ ከ 23ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን የ 2027 የግብፅ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከዩጋንዳ...
01/09/2026

የኢትዮጵያ ከ23ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ተጋጣሚ የነበረችው ዩጋንዳ ከውድድሩ መውጣቷን ገለጸች።

የኢትዮጵያ ከ 23ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን የ 2027 የግብፅ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከዩጋንዳ ጋር መደልደሏ ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የሀገሪቱ እግርኳስ ፌዴሬሽን ለዋናው ብሔራዊ ቡድን ዝግጅት ሲባል ከ23 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኑን ከውድድር አስወጣቶታል።

ዩጋንዳ በመጀመሪያው ዙር ማጣሪያ ከኢትዮጵያ ጋር የደርሶ መልስ ጨዋታ እንድታደርግ ነው የተደለደለችው።

ዩጋንዳ ከውድድሩ መውጣቷን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሁለተኛው ዙር ማጣሪያ ከሞሮኮ ጋር የምትጫወት ይኾናል።

በዚህም መሠረት የሁለተኛው ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ ጥቅምት 30/2019 ዓ.ም ሲካሄድ የመልሱ ጨዋታ ደግሞ ኅዳር 12/2019 ዓ.ም ይካሄዳል።

#አሚኮ #ስፖርት #ኢትዮጵያ🇪🇹



በዳናይት ሲሳይ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

01/09/2026

የክብደት ማንሳት ዉድድር ዉጤት
በቪድዮ
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

ክረምት በጎ አድራጎት ምክንያት በማድረግ የሴክተር መስሪያ ቤቶች የጤና ቡድን ዉድድር  ዉጤት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በከማሽ ዞን በምዥጓ ወረዳ  የጤና ቡድን / የማስ ስፖርት የሴክተር መስ...
01/09/2026

ክረምት በጎ አድራጎት ምክንያት በማድረግ የሴክተር መስሪያ ቤቶች የጤና ቡድን ዉድድር ዉጤት

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በከማሽ ዞን በምዥጓ ወረዳ የጤና ቡድን / የማስ ስፖርት የሴክተር መስሪያ ቤቶች የደረጃ ጨዋታ የክልሉ አድማ ብተናና ልዩ ጥበቃ እግር ኳስ ክለብ አቻውን ጤና ጽ/ቤት 5 ለ 1 በማሸነፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ።

በወረዳው ማስ ስፖርት ጨዋታ የሴክተር መስሪያ ቤቶችና የከተማው ክለቦች ጨዋታ በወረዳው የሚገኘው የክልሉ አድማ ብተናና ልዩ ጥበቃ እግር ኳስ ክለብ የጤና ጽ/ቤት እግርኳስ ክለብ ጋር 8:00 ሠዓት ላይ ጨዋታውን ያደረገ ሲሆን በደረጃ 5 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ጨዋታው ተጠናቋል።

ጨዋታው ፍፁም ስፖርታዊ ጨዋነትን የተላበሰ ሆኖ የታዳሚውን ቀልብ በመሳብ ቁም ነገር አዝሎ ተመልካቹን ሲያዝናና ውሏል።

በውጤቱም በወረዳው የክልሉ አድማ ብተናና ልዩ ጥበቃ እግር ኳስ ክለብ ሶስተኛ ደረጃ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል።

በቀጣይ ሳምንት የዋንጫ ጨዋታ መርሃ ግብር ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም 4:00 ሠዓት ላይ የመስተዳድር እግር ኳስ ክለብ የፖሊስ አቻውን የሚገጥም ሲሆን አዲስ ክለብ የእምፑዌይ ክለብ ጋር ለዋንጫ ጨዋታ ይጠበቃሉ።

ነሀሴ 24/2018 ዓ.ም (ምዥጋ)

አሰደሳች ዜና ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዳማ ከተማ ከነሀሴ 23-30/2018 ዓ.ም  ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ ክብደት ማንሳት ሻምፒዮና ላይ ክልላችንን በመ...
01/09/2026

አሰደሳች ዜና
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዳማ ከተማ ከነሀሴ 23-30/2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የኢትዮጵያ ክብደት ማንሳት ሻምፒዮና ላይ ክልላችንን በመወከል እየተካፈሉ የሚገኙት የስፖርት ልዑካን አባላት አመርቂ ውጤት እያስመዘገቡ ይገኛሉ። በተካሄዱ ውድድሮችም በሴቶች 53 ኪ.ግ. ምድብ/ካታጎሪ የጦሪ ባኬ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በ 57ኪ.ግ ምድብ/ካታጎሪ በይዳ አብዱራህማን የወርቅ ሜዳሊያ፣ በወንዶች 75 ኪ.ግ. ምድብ/ካታጎሪ ሀብታሙ ጴጥሮስ የወርቅ ሜዳሊያ፣ በ 70 ኪ.ግ. ምድብ/ካታጎሪ እላሙዲን ኢተፋ የነሀስ ሜዳሊያ ያስመዘገቡ ሲሆን ቀሪ ውድድሮችን ሳጨምር አስካሁን ድረስ በተካሄዱ ውድድሮች
1.በሴቶች 3 የወርቅ ሜዳሊያ፣
2.በወንዶች 1 የወርቅ፣ 2 የብርና 1 የነሀስ ሜዳሊያ በጠቃላይ 4 የወርቅ፣ 2 የብርና 1 የነሀስ ሜዳሊያ ለማስመዝገብ ተችሏል።

የተዳጊ ወጣቶች ስልጠናና የስፖርት ህክምናን በሳይንሳዊ ጥናቶች ተደግፎ መተግበር በዘርፉ ለሚፈለገው ውጤት መሰረታዊ አቅም ነው፦ ክቡር መኪዩ መሐመድነሃሴ 25፣ 2018 ዓ.ም         አዲ...
01/09/2026

የተዳጊ ወጣቶች ስልጠናና የስፖርት ህክምናን በሳይንሳዊ ጥናቶች ተደግፎ መተግበር በዘርፉ ለሚፈለገው ውጤት መሰረታዊ አቅም ነው፦ ክቡር መኪዩ መሐመድ

ነሃሴ 25፣ 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የኢፌዲሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ በሀገራችን ከሚገኙ የስፖርት ማህበራት አመራሮችና ባለሞያዎች ጋር በመተባበር የታዳጊ ወጣቶች በየዕድሜ ደረጃቸው በተለያየ የስፖርት አይነቶች እያዘጋጀ በሚገኘው የስፖርት ስልጠና ማሰልጠኛ ማንዋል የክለሳ ስራ የግብአት ማሰባሰቢያ መድረክ ዛሬ ጀመረ።

በመድረኩ የተገኙት የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር መኪዩ መሐመድ የተዳጊ ወጣቶች ስልጠናና የስፖርት ህክምናን በሳይንሳዊ ጥናቶች ተደግፎ መተግበር በዘርፉ ለሚፈለገው ውጤት መሰረታዊ አቅም መሆኑን ገልፀዋል።

በማስከተልም ሚንስትር ዴዔታው እየተዘጋጁ የሚገኙ የታዳጊዎች የስፖርት ስልጠና ማንዋሎች የሀገራችን ስፖርት ልማት የደረሰበትን ደረጃ የሚያሳዩ፣ ስፖርቱ በዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የደረሰበትን የእድገት ደረጃ የሚመጥኑና የሚተገበሩ፣ ብሎም ወደ ተጠቃሚዎች የሚደርሱ ሆነው በጊዜ እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል።

በዛሬው እለት ከሀገራችን የተለያዩ የስፖርት አካዳሚዎች፣ ፌዴሬሽኖችና የትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ከፍተኛ የስፖርት ምሁራን በተገኙበት የተጀመረው የግብአት ማሰባሰቢያ መድረክ ውሎውን በካራቴ፣ በቦክስ እና በወርልድ ቴኳንዶ ስፖርቶች የተዘጋጁ የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት ማሰልጠኛ እና የስፖርት ህክምና ሰነዶች ለተወያዮች ቀርበዉ ከዘርፍ ምሁራን ጠቃሚ ግብአቶች መሰብሰብ ተችሏል።

በተመሳሳይ መድረኩ እስከ ፊታችን አርብ ነሃሴ 29/2018ዓ.ም በቀሩት የስፖርት አይነቶች የተዘጋጁ ሰነዶች ለምሁራን ቀርበው ግብአቶች የሚሰበሰቡበት መሆኑ ታውቋል።

ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!

የቴሌግራም ቻናላችንን ይከተሉ፡ https://t.me/MoCSofficial

ዩቲዩብ፡ https://youtube.com/

ፌስቡክ: https://www.facebook.com/cultureandsportethiopia?mibext

ቲክቶክ፡ https://vm.tiktok.com/ZMAV65gyo/

ትዊተር/ኤክስ፡https://x.com/Mocs_20252017?t=tdzYOBsTjbL7y-JBgDKIBQ&s=09

Address

Field
Asosa

Telephone

+251922229580

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ስፖርት ኮሚሽን Benishangul Gumuz Sport Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share