Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission

Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission Sidam natinal rigional state stablished by proclamation number 10/2012 to fight against corruption

በነዳጅ ግብይትና በገጠር መንገድ ግንባታ ላይ የሚታዩ የሙስና ተጋላጭነቶችን ለመታገል አዲስ ጥናት ይፋ ሆነ!ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም        ሀዋሳየሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ...
22/04/2026

በነዳጅ ግብይትና በገጠር መንገድ ግንባታ ላይ የሚታዩ የሙስና ተጋላጭነቶችን ለመታገል አዲስ ጥናት ይፋ ሆነ!

ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተለያዩ የመንግስት ተቋማት የአሰራር ስርዓት ላይ ሲያካሂድ የቆየውን ጥልቅ ጥናት ለባለድርሻ አካላት ይፋ ማድረጉን ቀጥሏል።

በዛሬው የሦስተኛ ቀን መርሐ-ግብር፣ በክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደሩ ባሉ ሁለት ስትራቴጂካዊ ዘርፎች ላይ ያተኮረ የምርመራ ውጤት ቀርቧል።

ጥናቱ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ሂደት ላይ የሚታዩ የህገ-ወጥ ዝውውር ችግሮችን በዝርዝር ዳስሷል። በተለይም፣ በአቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ለብልሹ አሰራር በር የሚከፍቱ የአሰራር ክፍተቶች፤ የቁጥጥር ስርዓቱን ደካማነት ተገን በማድረግ የሚታዩ የህገ-ወጥ ግብይት ተጋላጭነቶች፤ በህዝብ ተጠቃሚነት ላይ እንቅፋት የሆኑ የንግድ ስርዓት መዛባቶች በጥናቱ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።

ሁለተኛው የጥናት ግኝት ትኩረት ያደረገው በገጠር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ላይ ነው። ጥናቱ እንደሚያመለክተው፣ ከጨረታና ግዥ ሂደት ጀምሮ እስከ ፕሮጀክቶች ግንባታ ፍጻሜ ድረስ ያለው ሂደት ለከፍተኛ የሙስና ስጋት የተጋለጠ መሆኑ ተለይቷል። ይህም የክልሉን ውስን ሃብት ያለአግባብ ለብክነት እየዳረገ መሆኑ በውይይቱ ላይ በስፋት ተነስቷል።

በአሁኑ ሰዓት የሚመለከታቸው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሚካሄደው በዚህ መድረክ፣ ለሙስና ምቹ የሆኑ ቀዳዳዎችን በጋራ መለየት፤ ጠንካራ የተጠያቂነት ስርዓት መዘርጋት፤ የክልሉን ሃብትና ንብረት ከብክነት መታደግ የሚያስችሉ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ላይ ትኩረት ተደርጓል።

ኮሚሽኑ መሰል ጥናቶችን በጥሬ መረጃ አስደግፎ ይፋ ማድረጉ፣ ተቋማዊ ግልጽነትን ከማስፈኑ ባለፈ፣ የህዝብን ጥቅም ለማስከበር የሚደረገውን ትግል ወደ ሳይንሳዊ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይታመናል።

በእነዚህ ወሳኝ ዘርፎች ላይ የሚታየውን የሙስና ተጋላጭነት ለመቀነስ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የህዝብ ተሳትፎ ምን መምሰል አለበት ይላሉ? ሃሳብዎን ያካፍሉን።

ለፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎች

email
[email protected]
WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/KCvsTVV91bXLhSCNFmYd9I?mode=gi_t
YouTube
https://www.youtube.com/

Telegram
https://t.me/+2d8PjI0EYkQ5OTdk

Tikitok
https://www.tiktok.com/.ethics.acc?_r=1&_t=ZS-94chEynKxkG

ወደ ቢሮአችን ለመምጣት ከታች ያለውን የጎግል ማፕ መገኛ ይጠቀሙ።
https://maps.app.goo.gl/zTQ44e3nCqy5qEMC7?g_st=atm

በመሬት አስተዳደር ዘርፍ የሙስና ቀዳዳዎችን ለመድፈን ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል።ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም — ሀዋሳየሲዳማ ክልል የሥነ-ምግባርና የጸረ-ሙስና ኮሚሽን፣ በክልሉ የኢኮኖሚ የጀርባ ...
21/04/2026

በመሬት አስተዳደር ዘርፍ የሙስና ቀዳዳዎችን ለመድፈን ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል።

ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም — ሀዋሳ

የሲዳማ ክልል የሥነ-ምግባርና የጸረ-ሙስና ኮሚሽን፣ በክልሉ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት በሆኑ የልማት ዘርፎች ላይ ያካሄደውን ጥልቅ የሙስና ተጋላጭነት ጥናት ውጤት ለሁለተኛ ቀን ይፋ ማድረጉን ቀጥሏል።

የዛሬው የውይይት መድረክ ትኩረቱን በከተማ መሬት አስተዳደርና ልማት ዘርፍ ላይ ባሉ ስር የሰደዱ የአሰራር ክፍተቶች ላይ አድርጓል።

ኮሚሽኑ ይፋ ያደረገው ይህ ጥናት፣ በመሬት አስተዳደር ዘርፍ ለብልሹ አሰራር በር የሚከፍቱ የህግና የአሰራር ድክመቶችን በዝርዝር የለየ መሆኑ ተገልጿል።

ጥናቱ በዋናነት የአሰራር ግልጽነት ማነስን ለመቅረፍ፣ የተጠያቂነት ስርዓትን ለማስፈን እና ተቋማት ራሳቸውን እንዲፈትሹ እንደ ማንቂያ ደወል ሆኖ እንዲያገለግል ታስቦ የቀረበ መሆኑ በመድረኩ ተመላክቷል።

ይህ የጥናት ውጤት ተራ ሪፖርት ሳይሆን የተቋማትን ጤናማነት መለኪያ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። በመሆኑም ኮሚሽኑ አቅጣጫዎችን ከማስቀመጥ ባለፈ፣ የማስተካከያ እርምጃዎች በተግባር መተርጎማቸውን ለማረጋገጥ በየሶስት ወሩ የመስክ ክትትልና ቁጥጥር ስራዎችን በጥብቅ ያከናውናል ነዉ የተባለዉ።

በተለይም የማስተካከያ እርምጃ ለመውሰድ ቸልተኝነት በሚያሳዩ ተቋማትና አመራሮች ላይ ጉዳዩ በቀጥታ ወደ ህግ አካላት ተመርቶ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንደሚደረግ ጥብቅ ማስጠንቀቂያም ተሰጥቷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት ከፍተኛ የክልሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ተጠኚ ተቋም፣ የዘርፉ ቴክኒክ ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት የቀረቡትን ግኝቶች መነሻ በማድረግ ጥልቅ ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ።

ይህ የኮሚሽኑ ጥረት የሕዝብና የመንግሥት ሀብት ለታለመለት የልማት ግብ ብቻ እንዲውል ከማድረጉም ባለፈ፣ በከተማ መሬት ዙሪያ የሚነሱ ቅሬታዎችን በዘላቂነት ለመፍታትና የፍትሃዊነት ጥያቄን ለመመለስ እንደ ትልቅ እርምጃ ተወስዷል።

የሲዳማ ክልል ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአምስት ቁልፍ የልማት ዘርፎች ላይ ያከናወነውን የጥናት ውጤት ይፋ አደረገ።ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (ሀዋሳ) የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባ...
20/04/2026

የሲዳማ ክልል ሥነምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በአምስት ቁልፍ የልማት ዘርፎች ላይ ያከናወነውን የጥናት ውጤት ይፋ አደረገ።

ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም (ሀዋሳ)

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከፍተኛ የፋይናንስ እንቅስቃሴ በሚታይባቸውና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ ናቸው ተብለው በተለዩ አምስት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ያካሄደውን የጥናት ውጤት ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ ጀመረ።

ኮሚሽኑ ጥናቱን ያተኮረባቸው ዘርፎች በክልሉ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ትልቅ ድርሻ ባላቸው የከተማ መሬት አስተዳደር፣ የማዴያ ነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት፣ የመንግስት ንብረት አስተዳደር፣ የገጠር መንገድ ግንባታ አፈፃፀም እና በሲዳማ ልማት ኮርፖሬሽን የሀብት አስተዳደር ዙሪያ መሆናቸው ተገልጿል።

እነዚህ ዘርፎች ለክልሉ ዕድገት ወሳኝ ቢሆኑም፣ አሁንም ድረስ ለሙስናና ለብልሹ አሰራር ያላቸው ተጋላጭነት ከፍተኛ መሆኑ በጥናቱ ተመላክቷል። የጥናቱ ዋነኛ ዓላማም የአሰራር ክፍተቶችን በጥልቀት በመለየት የሙስና ስጋቶችን አስቀድሞ ለመከላከልና ተገቢውን የለውጥ ምክረ-ሐሳብ ለማቅረብ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል።

የክልሉ ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽነር ወ/ሮ ዘላለም ለማ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ የተቋማትን አሰራር በየጊዜው በመፈተሽ ለሙስና አጋላጭ የሆኑ ሁኔታዎችን አስቀድሞ ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

ኮሚሽነሯ አክለውም፣ በተቋማት ላይ የሚስተዋለውን ብልሹ አሰራር ለማረም የሚደረገው ጥረት ፍሬ እያፈራ መሆኑን ጠቅሰው፣ በተለይም ተጋላጭ የሥራ ዘርፎችን በመለየትና የቁጥጥር ስርዓቱን በማጠናከር ረገድ የተከናወኑ ተግባራት የህዝብና የመንግስት ሀብትን ከምዝበራ ለመታደግ ማስቻላቸውን አስረድተዋል።

በንግግራቸው ወቅት የውሳኔ አሰጣጥ ጥራትን ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አጽንዖት የሰጡት ኮሚሽነር ዘላለም፤ የግል ጥቅም ጣልቃ የሚገባባቸውን አሰራሮች በማስቀረት ውሳኔዎች በህግና በስርዓት ላይ ብቻ የተመሰረቱ እንዲሆኑ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ለቀጣይ አምስት ቀናት በሚቆየው በዚህ የምክክር መድረክ፣ በዛሬው ዕለት የሲዳማ ልማት ኮርፖሬሽን የሀብት አስተዳደር ለሙስናና ብልሹ አሰራር ያለዉ ተጋላጭነት ላይ የቀረበው ጥናት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ጥናቱ የተካሄደበት ተቋም በግኝቶቹ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ የተለዩ ስጋቶችን ለመቅረፍና ምክረ-ሐሳቦቹን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የሥራ አቅጣጫ አስቀምጧል።

ኮሚሽኑም በጥናቱ የተለዩ ግኝቶችን ወደ ተግባር ለመለወጥና ተከታታይ ክትትል ለማድረግ ከተጠኚ ተቋም ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

15/04/2026
መላዉን የክርስትና እምነት ተከታዮች የኮሚሽናችን አመራር አካላትና ሠራተኞች እንኳን ለ2018 ዓ.ም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም  አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴን አየ...
11/04/2026

መላዉን የክርስትና እምነት ተከታዮች የኮሚሽናችን አመራር አካላትና ሠራተኞች እንኳን ለ2018
ዓ.ም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴን አየገለጽኩኝ
በዓሉ የሰላም ፣የፍቅር፣ እርስ በርስ የመተሳሰብ እንድሆንልን እመኛለሁ ።

የሚዲያ ተቋማት ሙስናን በመታገል ረገድ ያላቸው አጋርነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀሀዋሳ፦ መጋቢት 24/2018 ዓ.ምየሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ''ሚዲያ የመንግስት ተ...
02/04/2026

የሚዲያ ተቋማት ሙስናን በመታገል ረገድ ያላቸው አጋርነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ

ሀዋሳ፦ መጋቢት 24/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ''ሚዲያ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳለጥና ብልሹ አሰራርን ለማታገል ያለው ሚና'' በሚል ሰነድ ላይ በሀዋሳ ከተማ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አሸናፊ ኤልያስ እንደገለጹት፤ ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት ጠንካራ ሚዲያ መኖሩ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ሚዲያው ማህበረሰቡ የሙስና ድርጊትን እንዲጸየፍ ከማስተማርና ከማንቃት ባለፈ፣ ብልሹ አሰራሮችን በማጋለጥ ረገድ የመረጃ ድልድይ ሆኖ ማገልገል እንዳለበትም አሳስበዋል።

አቶ አሸናፊ አክለውም፣ ውስን የሆነውን የሀገር ሀብት ካልተገራ የግል ፍላጎት በመጠበቅ ለልማት እንዲውል ለማድረግ ከሚዲያ ተቋማት ጋር ያለው ቅንጅታዊ አሰራር መጠናከር እንዳለበትም ገልጸዋል።

የክልሉ ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ለማ በበኩላቸው፤ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የሚዲያ ተቋማት ተኪ የሌለው ሚና አላቸው ብለዋል።

ኮሚሽነሯ አክለውም፣ ሚዲያዎች ህዝቡ የሙስና ጥቆማዎችን የትና እንዴት መስጠት እንዳለበት ግንዛቤ ከመፍጠር ባለፈ፣ ሙስና በሀገርና በማህበራዊ ፍትህ ላይ የሚያመጣውን ጠባሳ በዝርዝር ማሳወቅ ይገባቸዋል ብለዋል።

ሰፊ የሚዲያ ሽፋን በመስጠት ረገድ አሁንም ክፍተቶች እንዳሉ የጠቆሙት ኮሚሽነር ዘላለም፤ "በተለይም ዜጎች ሙስናን እንደ 'ነውርና ወንጀል' እንዲመለከቱት የአስተሳሰብ ለውጥ ማምጣት የሚዲያ ተቋማት ቀዳሚ ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ጠቁመዋል፤ አያይዘዉም ተቋማቱ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን የህዝብ 'ዓይንና ጆሮ' ሆነው ሊሰሩ ይገባል" ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ፤ ሚዲያው የመንግስት ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በማረም፣ የተሳለጠ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ እና ትክክለኛ መረጃ ለህዝብ በማድረስ ረገድ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ተመላክቷል።

በዚህ የጋራ የምክክር መድረክ ላይ የሚዲያ ተቋማት አመራሮች፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል።

የጥላው ሽሽትሲያግበሰብስ ለሆዱ ሲዘርፍ ብቻውን፣ አያውቀውም ነበር ወገን ዘመዱን ፤ የህዝብን ሲሳይ  ለራሱ ሲያደርገው፣ የሌላውን ጉዳይ  ዘንግቶት ነበረው።የክፋቱ ፍሬ  ሀቁ ሲመዘዝ፣ ተጠያቂ...
26/03/2026

የጥላው ሽሽት

ሲያግበሰብስ ለሆዱ ሲዘርፍ ብቻውን፣
አያውቀውም ነበር ወገን ዘመዱን ፤

የህዝብን ሲሳይ ለራሱ ሲያደርገው፣
የሌላውን ጉዳይ ዘንግቶት ነበረው።

የክፋቱ ፍሬ ሀቁ ሲመዘዝ፣
ተጠያቂነቱ መጥቶ ሲያቅበዘብዝ፤

“ጎሳዬ ተነካ” ብሎ ይጮኻል፣
በወገኑ ካባ ውስጥ ሊደበቅ ይሻል።

ሲበላ የረሳው የወገኑን ጥማት፣
ሲያዘርፍ የከዳው የጎሳውን ጥራት፤

ዛሬ የክስ ሰልፍ ቤቱን ሲያንኳኳ፣
ሊያደርጋቸው መጣ የሌብነቱ ጋሻ።

ወንጀልና ጎሳ ምን ያገናኛቸዋል?
የግል ድፍረት ጥፋት ለማን ይተርፋል?

ክብርን አጉድፎ በስርቆት ተገኝቶ፣
በብሄር መሸሸግ ውርደት ነው ከቶ።

ስለዚህ ወዳጄ ህሊናህንሽጠህ፣
በገዛ እጅህ ራስህን አዋርደህ፣
ትንሽ አታፍርም ወይ ብሔር ጎሳ ሲትጠራ፣
የብቻህ ኃጢአት በወል አይወራ።

በአጥናፉ አባቴ

23/03/2026
15/03/2026
ሲዳማ ብ/ክ/መ/ሥ/ም/ፀ/ሙ/ኮሚሽን
14/03/2026

ሲዳማ ብ/ክ/መ/ሥ/ም/ፀ/ሙ/ኮሚሽን

በሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን
14/03/2026

በሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን

በሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ተከበረሀዋሳ | የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ምየሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን "የሴቶች ድ...
09/03/2026

በሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በድምቀት ተከበረ

ሀዋሳ | የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን "የሴቶች ድምፅ ለእኩልነት እና ለበለፀገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል 50ኛውን ሀገር አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) የኮሚሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አክብሯል።

በበዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር አቶ መልካሙ መንገሻ፣ የሴቶች ተሳትፎ ለበለፀገች ኢትዮጵያ ወሳኝ መሆኑን አንስተዉ፣ ሴቶች በሥራ ገበታቸውም ሆነ በማኅበራዊ ሕይወት ያላቸውን ሚና ማጠናከር ይገባል ብለዋል።

አክለዉም ፣ በዓሉ የሴቶችን መብት በማክበርና ተቋማዊ አቅምን በማጠናከር ረገድ ትልቅ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የትውልድ ግዴታ ነዉ ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሁሉም ማህበረሰብ ክፍል ቁርጠኝነት አስፈላጊ መሆኑንም አንስተዋል።

የሴቶች እኩልነት ጉዳይ የአንድ ወገን ሳይሆን የጠቅላላው ማኅበረሰብ የብልጽግና መሠረት ነዉ ስሉም አንስተዋል።

በዕለቱ በሴቶች መብትና እኩልነት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድ የቀረበ ሲሆን፣ ሰነዱን ያቀረቡት የሴቶችና ሕፃናት ወጣቶች ቢሮ የሴቶች አቅም ማጎልበቻ ዳይሬክቶሬት ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ አልማዝ ርቅዋ ናቸው።

በቀረበው ጽሁፍ ላይ ከኮሚሽኑ አመራርና ሰራተኞች ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share