Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission

Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission Sidam natinal rigional state stablished by proclamation number 10/2012 to fight against corruption

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ ከምዝበራ ማዳኑን አስታወቀ።ነሀሴ 11/2018ዓ.ምሀዋሳየሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ...
17/08/2026

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ ከምዝበራ ማዳኑን አስታወቀ።

ነሀሴ 11/2018ዓ.ም
ሀዋሳ

የሲዳማ ክልል ሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 ዓ.ም እቅድ ዝግጅት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ወ/ሮ ዘላለም ለማ እንደተናገሩት፤ በበጀት ዓመቱ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነጸ፣ ሙስናን የሚጠየፍ እና አጥብቆ የሚታገል ማኅበረሰብ በመገንባቱ ረገድ አበረታች ውጤት ተመዝግቧል።

ይህም በፀረ-ሙስና ትግሉ ውስጥ የላቀ የሕዝብ አጋርነት እንዲጎልበት ከማድረጉም በላይ በተቋማት ውስጥ የግልጸኝነትና የተጠያቂነት አሠራርን በማስፈን በሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ይታዩ የነበሩ ብልሹ አሠራሮችን በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ ማስቻሉን ገልጸዋል።

ኮሚሽነር ዘላለም አክለውም ከህዝብ የደረሱ ጥቆማዎችን በከፍተኛ ትኩረትና ጥንቃቄ በማስተናገድ አግባብነት ላላቸው አካላት በማቅረብ ከፍተኛ ሀብት ከምዝበራ ማዳን መቻሉን ተናግረዋል።

አያይዘውም ሌብነትንና ያለአግባብ ሀብት ማካበትን ለመታገል በሚደረገው እንቅስቃሴ፣ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ባፈሩ ግለሰቦች ላይ መረጃዎችን አደራጅቶ ወደ ሕግ የማቅረቡ ሂደት አሁንም መሻሻል የሚገባቸው ክፍተቶች እንዳሉበት ገልጸው፤ ከዚህ አንጻር የኮሚሽኑ ሠራተኞች በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

በሌላ በኩል በኮሚሽኑ የእቅድና በጀት ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ ዳይሬክተር አቶ በላይ ባንጋሳ የቀረበው ሪፖርት እንደሚያመለክተው፤ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለ205,600 የሕብረተሰብ ክፍሎች በሥነ-ምግባር፣ በሙስና ወንጀል ጎጂነት እና በትግል ስልቶች ዙሪያ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ተሰጥቷል።

በተጨማሪም በክልሉ በሚገኙ መንግሥታዊና ሕዝባዊ ተቋማት የሚታዩ የአሠራር ክፍተቶችን በጥናት በመለየት፣ በ4 ቁልፍ የልማት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ጥናቶች ተካሂደው ከተጠኚ ተቋማት ጋር የስምምነት ሰነድ በመፈራረም ወደ ትግበራ ተገብቷል ነዉ ያሉት።

የመንግሥት ሠራተኞችና ተሿሚዎች ሀብት ንብረታቸውን እንዲያስመዘግቡ በማድረግ የጥቅም ግጭትን ለመከላከልና የአገልግሎት አሰጣጥን በግልጽነት ለመምራት በተከናወነው የሀብት ምዝገባ ሥራ 5,463 ግለሰቦች ሀብታቸውን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመዘገቡ ሲሆን፣ የ89,790 ግለሰቦች ደግሞ እንዲታደስ ተደርጓል ስሉ አብራርተዋል፡፡

ዳይረክተሩ አክለውም በበጀት ዓመቱ ከሕዝብ የቀረቡ 711 ጥቆማዎችን መነሻ በማድረግ በተደረገ አስቸኳይ የቅድመ-መከላከል እንቅስቃሴ 38,427,726.3 ብር ከምዝበራና ከብክነት ማዳን መቻሉን ገልፀዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ በበጀት ዓመቱ የታዩ ጉድለቶችን በማረም የ2019 ዓ.ም ዕቅድን በላቀ ቅንጅት ለማስፈጸም የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ ተቀምጦ መድረኩ ፍጻሜ አግኝቷል።

ለፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎች
Email
[email protected]
WhatsApp
https://chat.whatsapp.com/KCvsTVV91bXLhSCNFmYd9I?mode=gi_t
YouTube
https://www.youtube.com/

Telegram
https://t.me/+2d8PjI0EYkQ5OTdk

Tikitok
https://www.tiktok.com/.ethics.acc?_r=1&_t=ZS-94chEynKxkG

ወደ ቢሮአችን በአካል ለመምጣት ከታች ያለውን የጎግል ማፕ መገኛ ይጠቀሙ።
https://maps.app.goo.gl/zTQ44e3nCqy5qEMC7?g_st=atm

06/08/2026
በሙስናና ሕገ-ወጥ አሠራር የተሳተፉ አካላት ላይ የሕግ እርምጃ ተወሰደ **************ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም የሲዳማ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን            ሀዋሳ ...
06/08/2026

በሙስናና ሕገ-ወጥ አሠራር የተሳተፉ አካላት ላይ የሕግ እርምጃ ተወሰደ
**************
ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም
የሲዳማ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን
ሀዋሳ

በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።

እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።

በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።

በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል

04/08/2026

ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ
*********************

ስንትባበር ምን ማድረግ እንደምንችል ደጋግመን ለዓለም ያሳየንበት የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዛሬም በድል ተጠናቋል።

ኢትዮጵያ የሚለው ስም በጋራ የመቻልና የጽኑ አቋም ተምሳሌት ነው። መንግሥት የሀገሪቱን ዘላቂ ጥቅም ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎችን ሲያስቀምጥ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብም ሀገራዊ ፍላጎቱን በጋራ ተነሣሽነት እውን የማድረግ የዘመናት ልምምድ አለው። በተለይም መንግሥት ለአረንጓዴ ልማትና ሀገራዊ ከፍታ ለሚያቀርበው ጥሪ ሕዝቡ በላቀ ተሳትፎ ምላሽ የመስጠት ቁርጠኝነቱ ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አብነት የሚሆን ነው።

መንግሥት በኢትዮጵያ የተራቆቱ አካባቢዎች በልጆቿ ብርቱ እጆች እንዲታከሙ፣ እየተስፋፋ የመጣው ድርቅና በረሃማነት በዘላቂነት እንዲገታ እና በአስተማማኝ መሠረት ላይ የተገነባ አረንጓዴ ኢኮኖሚ እውን እንዲሆን ግልጽና ጽኑ አቋም በመያዝ ጥሪ ሲያቀርብ ቆይቷል። በዚህም በላቀ የሕዝብ ተሳትፎና በመንግሥት መሪነት ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን ማድረግ ተችሏል፤ ኢትዮጵያዊያን ዛሬ ላይ ምድራቸውን አረንጓዴ ማልበስ ባህላቸው አድረገውታል ፤ባለፉት ሰባት ዓመታት ብቻ በአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለው ኢትዮጵያ አረንጓዴ ሸማ ለብሳለች። ዘንድሮም በንቅናቄው 8ኛው ዓመት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን፣ በክረምቱ ደግሞ በአጠቃላይ 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል መንግሥት ቁርጠኛ አቋሙን በይፋ አሳውቋል።

ለመንግሥት ሀገራዊ ጥሪ ቀናኢ የሆኑ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችም ይህንን ጥሪ በሙሉ ባለቤትነት ተቀብለው ለስኬቱ ከፍተኛ ርብርብ አድርገዋል። በዚህም በዛሬው ዕለት 26 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በአንድ ጀምበር ከ805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የተቀመጠውን ግብ ከዕቅድ በላይ አሳክተውታል። ይህ መንግሥትና ሕዘብ ሲተባበሩ ምን ማድረግ አንደሚችሉ የሚያሳይ፣ ማንም በዓለም ላይ ያለ ሀገር በቀላሉ ሊያሳካው የማይችል ድንቅ ስኬት ነው።

ይህ ውጤት የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና የመንግሥት ስትራቴጂካዊ አቋም በአንድ አቅጣጫ ላይ እንደሚገኙ ማረጋገጫ ነው። በዛሬው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 26 ሚሊዮን ኢትዮያውያን ብርድ፣ ዝናብና ፀሐይ ሳይበግራቸው መሬት ሲያለምዱ ውለዋል፤ በዚሁ ጽኑ እንቅስቃሴም የዘንድሮው ክረምት ከገባ ጀምሮ 6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተክለዋል። ኢትዮጵያ በልጆቿ ኮርታለች፤ መንግሥትም የሕዝቡን ከፍተኛ ቁርጠኝነትና ባለቤትነት ባየበት በዚህ ታሪካዊ ክስተት ከፍተኛ ኩራትና ክብር ተሰምቶታል። ይህም መንግሥት ይህንን ታላቅ ሕዝብ በበለጠ ኃላፊነትና ታማኝነት የማገልገል ጽኑ አቋሙን እንዲያጠናክር ተጨማሪ ብርታት ሆኖታል።

ክቡራን ኢትዮያውያን፣ ክቡራን የኢትዮጵያ ወዳጆችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አካላት፤ ዛሬ ይኸንን አገራዊ ራዕይ በጋራ እውን ማድረግ እንድንችል ስላደረጋችሁት ከፍተኛ ርብርብ መንግሥት በኢትዮጵያ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀርባል። የክረምቱን አጠቃላይ የ8 ቢሊዮን ችግኞች ተከላ ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት የተጀመረው አገራዊ ተሳትፎና ጽኑ አቋም ተጠናክሮ ይቀጠጥላል ።

ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

የሲዳማ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሰራተኞች ''በጋራ ተስፋን እንትከል' በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ በሚገኘዉ ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት በመሳ...
03/08/2026

የሲዳማ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አመራሮችና ሰራተኞች ''በጋራ ተስፋን እንትከል' በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ በሚገኘዉ ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት በመሳተፍ ችግኝ ተከሉ።

ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም
ሀዋሳ

ተፈጥሮን የመንከባከብና ለትውልድ የሚተርፍ ሀብት የማፍራት ሀገራዊ ጥሪን በመቀበል፣ የኮሚሽኑ አመራሮችና ሠራተኞች በሀዋሳ ከተማ ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራቸውን አሳርፈዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኝ" የመትከል ታላቅ ግብ አካል የሆነው ይህ መርሃ-ግብር፣ ኮሚሽኑ ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበት ሆኗል።

ለስምንተኛ ዙር እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ መርሃ-ግብር፤ ኮሚሽኑ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችልና ተፈጥሯዊ የሥነ-ምህዳር ሚዛንን ለመጠበቅ ሚናው የጎላ የተከላ ተግባር አድርገዋል።

በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌድሪ የአደጋና ስጋት አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራዉ ተክለማሪያም እንደገለጹት፤ "ዛፍን መትከል እስትንፋስን እንደ መትከል ነዉ ብለዋል። ይህ ንቅናቄ ከውበት ባለፈ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳዎች ያሉት መሆኑን ጠቁመዉ "የምንተክለው እያንዳንዱ ችግኝ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ፣ ለደን ሽፋን እድገት እና ለካርቦን ልቀት ቅነሳ የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ ነው" ብለዋል።

በመጨረሻም ኮሚሽነር ሽፈራዉ ባስተላለፉት ጥሪ፤ ዋናው ስኬት ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን፣ የተተከሉትን ችግኞች እንደ አደራ በመቁጠር መንከባከብና መከታተል መሆኑን አሳስበዋል። "ችግኞቹ ጸድቀው ለታለመላቸው የልማት ግብ እንዲውሉ የሁላችንም ቀጣይነት ያለው ክትትል ያስፈልጋል" በማለት፣ ህብረተሰቡ ለድህረ-ተከላ እንክብካቤ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።

''በጋራ ተስፋን እንትከል'

27/07/2026
የሲዳማ ኩራትና ድምቀት የሆነው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፕዮና ሲዳማ ቡና ክለብ  የጀግና አቀባበል ተጀመረሀዋሳ፣ ሐምሌ 6/2018 (ሲዳማ ክልል የሥ/ም/ፀ/ሙ/ኮ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊ...
13/07/2026

የሲዳማ ኩራትና ድምቀት የሆነው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፕዮና ሲዳማ ቡና ክለብ የጀግና አቀባበል ተጀመረ

ሀዋሳ፣ ሐምሌ 6/2018 (ሲዳማ ክልል የሥ/ም/ፀ/ሙ/ኮ)

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን በመሆን የሲዳማን ክብር እና ኩራት ከፍ ያደረገው ሲዳማ ቡና ክለብ ከአዲስ አበባ ወደ ሀዋሳ ሲደርስ በደማቅና በአይነቱ ልዩ የጀግና አቀባበል ለመቀበል የዝግጅት እንቅስቃሴ በሀዋሳ ተጀምሯል።

የክልሉ መንግሥት፣ የስፖርት ቤተሰብ፣ ወጣቶችና የሲዳማ ሕዝብ ለሻምፒዮኑ ቡድን የሚመጥን የድል አቀባበል ለማድረግ በመተባበር እየተንቀሳቀሱ ናቸው።

የሲዳማ ቡና የሻምፒዮንነት ድል ለክልሉ ስፖርታዊ እድገት ታሪካዊ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ በሀዋሳ የሚደረገው የጀግና አቀባበልም የሕዝቡን አንድነት፣ የስፖርት ፍቅር እና ለክለቡ ያለውን ኩራት በደማቅ ሁኔታ የሚያንጸባርቅ ይሆናል።

መላው የሲዳማ ሕዝብ በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በንቃት ተሳትፎ በማድረግ የክለቡን ድል እንዲያከብር ጥሪ ቀርቧል።

10/07/2026
Sidaamu Da/Qo/Mo/A/Tse/Mu/ Komishiine 2018 m.d.Xaphooma Mixote Jeefishshi Ripoorte  Amaalete Minira Shiqishshe  Keensiis...
09/07/2026

Sidaamu Da/Qo/Mo/A/Tse/Mu/ Komishiine 2018 m.d.Xaphooma Mixote Jeefishshi Ripoorte Amaalete Minira Shiqishshe Keensiissu.

Maaja, 01/2018 m.d.
Hawaasa

Komishiine loosu dirira amaddino mixo jeefishsha yanna yanantenni Qo/A/Minira shiqinshannita qummi assite xaphooma diru jeefishshu ripoorte komishiinete maaneejimentenna amaalete mini Se/Fa/Da/Ga/uu/komite noowa shiqishshinoti Qo/A/Tse/Mu/Ko/ komishiiner Zelaalm Lemma komishiine amaddino mixo addi addi straateeje horoonsiratenni woyyino guma maareekka dandiinoonnita xawissino.
Keenote bare amadinohu ayirradu kalaa Yoosef Yossihu qoqqowu amaale mine Se/ Fa/ nna Da/ Ga/ Ha/ uurrinshu komite ganbisaanchi komishiine diroho amaddino mixo konni garinni jeefisase addinta galantannite yee addinta luphiima looso loonse mussinnunna bainchu assooti aana amandoonni sharro lowonta jawaachishannote. Ledoteno,diru giddo qolloonninna hafanfaratenni gattinnoti dagate jiro assinoonnita jawaata sharro leellishshanohura komishiine addinta galatantanno yitanno hedo woreenna keenote bare xaphi yitino.

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama National Regional State Ethics and Anti Corruption Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share