29/05/2026
በመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በቢሮ በኩል እየተሰሩ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶች ስራዎችን በድጋፍ እና ክትትል ቡድን ምልከታ እየተደረገ ይገኛል::
በዩራፕ የጫቤ ሃማራሮ የ8.7 ኪሜ የግንባታ መንገድ ፕሮጀክት የጠጠር መበተን ሥራ እና የኮምፓክሽን ሥራ 5 ኪሜ የተሰራ ሲሆን ቀሪ ስራዎች በአጭር ጊዜ ዉስጥ ተጠናቆ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነ ለማየት ተችሏል:: የፕሮጀክቱ አካል የሆነው የstructure ስራዎች በ12 ቦታዎች ጎን ለጎን እየተሰራ ይገኛል::
በመንገዶች ባለስልጣን በኩል የጥገና ስራው እየተከናወነ የሚገኘው የባንሳ ዋሬ ቡራ መንገድ የጥገና በጥሩ ሁኔታ ሥራው እየተሰራ መሆኑ ታይቷል::
በሪካፕ ፕሮግራም የሚሰራ የጥገና ፕሮጀክት የ7 ኪሜ መንገድ የዳምፕንግና ሌሎች ሥራዎችን የማስጀመር ሥራ ተሰርቷል:: በሌላም በኩል በቦና ዙሪያ ወረዳ እየተሰራ ያለው የቂቄ ቂልጦ መንገድ ላይ የጋቢዮን ግንባታ እየተከናወነ መሆኑ የድጋፍ እና ክትትል ቡድን ተመልክተዋል::
እንዲሁም የቦና 01 ቡርሳ የጥገና መንገድ በመንገዶች ባለስልጣን በኩል እየተሰራ ያለዉን መመልከት ተችሏል::
በዞን ደረጃ የድልድይ ግንባታ የባሬ ድልድይ ;የአሳሮ የአሎ እንዲሁም የሀይጥሌ ድልድዮች በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን የሎዶማ ድልድይ ጭሬ ወረዳ እና የጋንቤልቱ ድልድይ በጫቤ ወረዳ በቅርቡ ግንባታቸው የሚጀመሩ እንደሆነ ታይቷል::
የድጋፍ እና ክትትል ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ::
ግንቦት 21/09/2018 ዓ.ም
በንሳ ዳዬ