Berea Bible Study Ministry

Berea Bible Study Ministry Bible study and preaching the Gospel

መማር ለምትፈልጉ የማትከስሩበት ነው ተጠቀሙ
17/06/2025

መማር ለምትፈልጉ የማትከስሩበት ነው ተጠቀሙ

https://youtu.be/QTob53p1v78
25/04/2025

https://youtu.be/QTob53p1v78

ይህ ቻናል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት የምንማማርበት ነው። ዓላማውም ክርስቲያኖችን ማገልገል ፣ መጽሐፍ ቅዱስ የማጥናት ልምድ የሌላቸውን ለማነሳሳት እና ክርስትናን ላልተረዱት ወንጌል ...

02/10/2024

ሕዝ 38፡1-7 እየተፈፀመ ይሆን? ቤተክርስትያን ተነጥቃለች ወይስ ...? በዓለማችን የወንድማማቾች ጦርነት በዝቷል። ምን ተረዳችሁ?

18/08/2024

የወንጌል አገልጋይ ሆይ:-
ቲቶ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤
¹⁴ መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል።
¹⁵ ይህን በሙሉ ሥልጣን ተናገርና ምከር ገሥጽም፤ ማንም አይናቅህ።

30/03/2024

ሐዋርያት 13 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁸ እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ የኀጢአት ይቅርታ የሚገኘው በኢየሱስ በኩል መሆኑ እንደ ተሰበከላችሁ ዕወቁ፤
³⁹ በእርሱ የሚያምን ሁሉ በሙሴ ሕግ በኩል ማግኘት ያልተቻለውን ጽድቅ ያገኛል።
⁴⁰ ስለዚህ ነቢያት እንዲህ ብለው የተናገሩት እንዳይደርስባችሁ ተጠንቀቁ፤
⁴¹ “ ‘እናንት ፌዘኞች፤ ተመልከቱ፤ ተደነቁ፤ ጥፉም፤ ማንም ቢነግራችሁ፣ የማታምኑትን ሥራ፣ እኔ በዘመናችሁ እሠራለሁና።’ ”
እንግዲህ እናንተ የምድር ሰዎች ሆይ ይህን እውነት እንዳትቃወሙ። ብትቃወሙ ዕንባቆም 1:5 ላይ እንደተናገረው እያያችሁ እየጠፋችሁም የእግዚአብሔር ስራውን ይሰራል። ይልቁን እንዲገለጥላችሁ ጸልዩ እንጂ።

10/03/2024

Our great hope, Jesus, is coming.

09/03/2024

1ኛ ቆሮንቶስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸ ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን።
¹⁹-²⁰ የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።

“የወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ትልቁ ጥፋት ይህ ነው፥ የወንጌሉ ዓለም ለእውነት በእውነት መቆም አለመቻላቸው ነው።” Francis Schaeffer (1912 - 1984)
04/02/2024

“የወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ትልቁ ጥፋት ይህ ነው፥ የወንጌሉ ዓለም ለእውነት በእውነት መቆም አለመቻላቸው ነው።”
Francis Schaeffer (1912 - 1984)

The conviction that the Bible held basic answers for basic question would characterize his life and work.

09/01/2024

“ሕጉ ምንም ፍጹም አላደረገምና፥ ስለዚህም የምትደክም የማትጠቅምም ስለሆነች የቀደመች ትእዛዝ ተሽራለች፥ ወደ እግዚአብሔርም የምንቀርብበት የሚሻል ተስፋ ገብቶአል።”
— ዕብራውያን 7፥18-19

09/01/2024

“በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን፦ የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም።”
— ኤርምያስ 3፥16

እኚህ አባት አቡነ ጎርጎሪዮስ ይባላሉ። ከጎን ያለው ፎቶ ወጣት ሳለው የተነሳሁት ነው። ከአቡነ ጎርጎሪዮስ ከተማርኳቸው ትምህርቶች አንዱ ስለታቦት ነበር። በዚያን ጊዜ ለእኔ መንፈሳዊ ትምህርት...
07/01/2024

እኚህ አባት አቡነ ጎርጎሪዮስ ይባላሉ። ከጎን ያለው ፎቶ ወጣት ሳለው የተነሳሁት ነው። ከአቡነ ጎርጎሪዮስ ከተማርኳቸው ትምህርቶች አንዱ ስለታቦት ነበር። በዚያን ጊዜ ለእኔ መንፈሳዊ ትምህርት የመጀመሪያዬ ስለነበር ነጭ ወረቀት ላይ የመጻፍ ዓይነት ነበር። ስለታቦት፡-
በኢትዮጵያውያ ኦርቶዶክስ ቤተከርስቲያን ብቻ ያለ ስርዓት መሆኑን ተምሬአለሁ። ከአምስቱ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ አገራት ውስጥ ኢትዮጵያ ብቻ ይህንን ስርዓት ስታካሂድ አንዳቸውም አልተከተሏትም፤ ምክንያቱም የግድ አይደለም ደግሞም አላመኑበትም ማለት ነው። ይህን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ የሌለውን ስርዓት ለመፈጸም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ መዋሸት ያስፈልጋል። ይህንን ከባድ ውሸት በድፍረት የፈጸመች ሀገር ብትኖር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ሕዝቡም አንባቢ እና ጠያቂ ስላልነበረ ለተሸከሙት እንጨት ሲያሰግዱት ይሰግዳል ፣ ጠፋ ተሰረቀ ሲሉት ለፍለጋ ይወጣል። በዝዋይ ገብርኤል ገዳም በአቡነ ጎርጎርዮስ ከተማርኩ በኋላ አዲስ አበባ አቡነ ገብርኤልን አግኝቼ ስለታቦቱ ጠይቄያቸው ነበር ምላሻቸው የኢትዮጵያ ባህል ነው እንጂ ዶግማ አይደለም ብለውኛል። ታዲያ ለምንድነው የእናቴን ሽንኩርት መክተፊያ የሚያክል ነገር በቄስ አሸክመው የሚያሰግዱን? የሚል ጥያቄ በውስጤ ብቅ ቢልም በሰዓቱ መጸሐፍ ቅዱስን በሚገባ ስላልተረዳሁ በአንደበቴ ማውጣት አልቻልኩም ነበር። ነገር ግን መጽሐፉን ሳነብ ያገኘሁት የብሉይ ኪዳን ታቦት ከላይ በምስል እንደለጠፍኩት አራት ካህና የሚሸከሙት ትልቅ ሳጥን መሰል ነገር እንደነበር ስረዳ የአገራችን ታቦታት ምንም ዓይነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ የሌለውና ወደ ጣዖት አምልኮ የሚጠጋ እንደሆነ ተረዳሁ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሰዎች ወይም በመላእክት ስም የተቀረጸ ታቦት አላገኘሁም። በአጸደ ስጋ በሌሉ ሰዎችና መናፍስት በሆኑ መላእክት ስም ቅርጽ ሰርቶ ማምለክ የመናፍስት ጠሪና የባለብዙ አማልክት ተከታይ የሆኑ የሕንዶች ዓይነት ልምምድ ነው። ይህን እውነት አባቶች በደንብ ያውቁታል። ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ከዚህ ጉድ ራሷን ብታጠራ እና ንጹውን የክርስቶስን ወንጌል መስበክ ብትጀምር ከአፍሪካ አልፎ ለዓለም በደረሰች ነበር። አሁንም አልረፈደም!

አቡነ ጎርጎሪዮስ ትልቅ ባለውለታዬ ናቸው። መጽሐፍ ቅዱስን እንድወደው እና የዕለት ተዕለት ምግቤ እንዲሆን መነሻ የሆኑኝ እኚህ አባት ናቸው። ዛሬ በሕይወት ቢኖሩ የምጠይቃቸው ብዙ ነገር ነበረኝ ግን ለዚህ አልታደልኩም።

ቀጥሎ እውቀት ለጨመሩልኝ ለእነ አቡነ ገብርኤል እና አቡነ መልከጼዴቅ ትልቅ ክብር አለኝ።
ለኦርቶዶክስ ቤ/ክ ለዓለም የሚተርፍ የተሐድሶ ዘመን እንዲፈጥንላት ጸሎቴ ነው።
ወይትባረክ ለእግዚአብሔር!!!

“ብዙ ኀዘን የማያቋርጥም ጭንቀት በልቤ አለብኝ ስል በክርስቶስ ሆኜ እውነትን እናገራለሁ፤ አልዋሽምም፤ ሕሊናዬም በመንፈስ ቅዱስ ይመሰክርልኛል።”
— ሮሜ 9፥1-2

ዛሬ በቤተክርስቲያን ዘማሪያን እንደዚህ ደምቀው በምስጋና፣ በውዳሴና በአምልኮ እየመሩን በእግዚአብሔር መንፈስ በሀልዎቱ ውስጥ እንድንሆን አድርገውናል። ዘመናችሁ ይባረክ!!! ባርኳቸው
07/01/2024

ዛሬ በቤተክርስቲያን ዘማሪያን እንደዚህ ደምቀው በምስጋና፣ በውዳሴና በአምልኮ እየመሩን በእግዚአብሔር መንፈስ በሀልዎቱ ውስጥ እንድንሆን አድርገውናል። ዘመናችሁ ይባረክ!!! ባርኳቸው

Address

Awassa

Opening Hours

Monday 16:00 - 20:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Berea Bible Study Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Berea Bible Study Ministry:

Share