05/09/2026
የበጎ ፈቃድ ልማዳችንን በማስቀጠል የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁላችንም የጋራ ኃላፊነታችንን እንወጣ!
****************
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የኢትዮጵያን ታሪካዊ የጋራ መከባበር፣ መተጋገዝና አብሮነት መንፈስ ከዘመናዊ የልማት ፍላጎት ጋር የሚያገናኝ ጠንካራ ድልድይ ነው።
ዜጎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን እና እውቀታቸውን ለሀገራቸው በፈቃደኝነት ሲለግሱ፣ ኢትዮጵያ በብሩህ ተስፋ ከፈተናዎች ተነስታ የከፍታ አድማሷን ታሰፋለች፤ ካሰበችበትም ትደርሳለች።
የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ እንዲፋጠንና እንዲሳካ ዜጎች በቀና ልብ እና በፈቃደኝነት የሚያሳዩት ተነሳሽነትና የሚሰጡት ተግባራዊ ምላሽ እጅግ ወሳኝ ነው።
ስለሆነም የበጎ ፈቃድ ልማዳችንን በማስቀጠል የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ሁላችንም የጋራ ኃላፊነታችንን እንወጣ።
ክብርት ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር