Shabe Woreda Cooperative Development Office

Shabe Woreda Cooperative Development Office Export Standards Coffee Arabica Shebedino

የጣራሜሳና አከባቢው የገበሬዎች ሁለ/መ/ኅ/ሥ/ ማህበር በሁለገብ ሥራ ዘርፍ ከስድስት ቀበሌ በተወጣጡ አ/አደሮች በ1968 ዓ.ም የቋቋመ ማህበር ነው ::ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ...
19/06/2020

የጣራሜሳና አከባቢው የገበሬዎች ሁለ/መ/ኅ/ሥ/ ማህበር በሁለገብ ሥራ ዘርፍ ከስድስት ቀበሌ በተወጣጡ አ/አደሮች በ1968 ዓ.ም የቋቋመ ማህበር ነው ::
ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ከአባላቱ የቡና ምርትን በማሰባሰብና በማዘጋጀት ለውጭ ገበያ በማቅረብ የአ/አደሩ ምርት የተሻለ ገበያ እንድያገኝና ተጠቃሚ እንድሆን ከማድረጉ በተጨማሪ ለሀገር የውጪ ምንዛሪ በማስገኘት ረገድ የራሱን ሚና በመወጣት ላይ የምገኝ ማህበር ነው ። ይህ በእንድህ እንዳለ ሆኖ ማህበሩ ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የአገልግሎት አድማስ በማስፋት የአባላቱን ተጠቃሚነት ለመጨመር በተወሰነ ሥራ ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ ከቆየበት ተጨማሪ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ወደ ሥራ መግባቱ የሚታወስ ነው ። በመሆኑም ማህበሩ እያደረገ ያለውን የዕድገት ግስጋሴ በማጠናከርና እራሱን አስተማማኝ ደረጃ ላይ በማድረስ ለአባላቱና ለአካባቢው ህበረተሰብ እንድሁም ለሀገር የሚያደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ ለመቀጠል የተለያዩ ተጨማሪ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ወደ ሥራ መግባት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ይህንን የነዳጅ ማደያ አቅዶ ወደ ሥራ ተገብቶ የግንባታ ሥራ ተጠናቅቆ ለህብረተሰቡና ለተጠቃሚዎች አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ ሆኖ ይገኛል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዓላማ :-
° የህብረተሰቡን ፍላጎትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ
° በአከባቢው ያለውን የነዳጅ ፍላጎት ማሟላት
° የማህበሩን ሁለንተናዊ ዕድገት በመጠበቅ ሞዴል ማህበር እንድሆን ለማድረግ
° ተጨማሪ የሥራ ዕድል ለመፍጠር
° ማህበረሰብ በቅርበት አስፈላጊ አገልግሎት እንድያገኙ ለማድረግ
° የአባላቱን ገቢ ለማሳደግ ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ራዕይ :-
° ማህበሩ የጀመረውን ሥራ ወደሰፊና ድንበር ዘለል ንግድ ተሻግሮ ማየት።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ተልዕኮ :-
° የማህበረሰቡ ፍላጎትና አቅም እየተከታተለ ምላሽ መስጠት
° ሰፍ የሥራ ዕድል መፍጠር
° ለአካባቢው ማህበረሰብ ጥያቄ መመለስ
° የተወዳዳሪነት መንፈስ ማሳደግ

28/12/2019

ሲዳማ ደርብ 85'

ሀዋሳ ከተማ 1_3 ሲዳማ ቡና

13/12/2019

" የራስህን ትኩስ እንጀራ ለመጋገር ስትል የሌላውን ቂጣ አትርገጥ "

 : Prime Minister Abiy Ahmed Ali has received the   at a ceremony in   City Hall in  ,  .  He is now the Nobel Peace Lau...
11/12/2019

: Prime Minister Abiy Ahmed Ali has received the at a ceremony in City Hall in , . He is now the Nobel Peace Laureate of 2019! !

Here are some excerpts taken live from his acceptance speech!

"I like to think of “Medemer” as a social compact for Ethiopians to build a just, egalitarian, democratic, and humane society by pulling together our resources for our collective survival and prosperity."

“በሰላም እንድታድር ጎረቤትህ ሰላም ይደር”
“yoo ollaan nagayaan bule, nagaan bulanni.”

"It is a saying shared in many African languages, which means: “For you to have a peaceful night, your neighbor shall have a peaceful night as well.”

"The Horn of Africa today is a region of strategic significance.The global military superpowers are expanding their military presence in the area.Terrorist and extremist groups also seek to establish a foothold. We do not want the Horn to be a battleground for superpowers..."

"Today, is highly regarded for press freedom. It is no more a “jailor of journalists”. Opposition leaders of all political stripes are free to engage in peaceful political activity. We are creating an Ethiopia that is 2nd to none in its guarantee of freedoms of expression"

Prime Minister Abiy Ahmed Ali received the Nobel Peace Prize for his efforts to achieve peace and international cooperat...
10/12/2019

Prime Minister Abiy Ahmed Ali received the Nobel Peace Prize for his efforts to achieve peace and international cooperation, and in particular for his decisive initiative to resolve the border conflict with neighbouring Eritrea. Read the full Nobel Lecture he delivered today:

08/12/2019

60'
SIDAAMA BUNA 3 SIHUL SHIRE 1

24/03/2012ቦርዱ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን የመጨረሻ ውጤት ይፋ አደረገ::አዲስ አበባ ፣ ህዳር 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን የመጨረሻ ...
04/12/2019

24/03/2012

ቦርዱ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን የመጨረሻ ውጤት ይፋ አደረገ::

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን የመጨረሻ ውጤት ይፋ አደረገ።

ባለፈው ህዳር 13 ቀን 2012 ዓ.ም የህዝበ ውሳኔው የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ይፋ የተደረገ ሲሆን፥ በዛሬው እለት ደግሞ የመጨረሻ ውጤት ይፋ አድርጓል።

በዚህም 97 ነጥብ 7 በመቶ የሆኑት መራጮች ሲዳማ በክልልነት እንዲደራጅ ድምጽ ሲሰጡ፥ 1 ነጥብ 47 በመቶዎቹ ሲዳማ በደቡብ ክልል ለመቆየት ድምጽ ሰጥተዋል።

ቦርዱ የምርጫ ጣቢያዎችን ውጤት በመገምገም፥ የድምር እንዲሁም ሌሎች የምርጫ ውጤት አለመጣጣም ያለባቸውን ጣቢያዎች በማየት ውሳኔ ማሳለፉንም ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ አስታውቋል።

በመሆኑም በአጠቃላይ ድምጽ ከተሰጠባቸው 1 ሺህ 692 ምርጫ ጣቢያዎች እና ተጨማሪ 169 ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች መካከል በ233ቱ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የድምርና የውጤት አለመጣጣም ችግር ማግኘቱን ገልጿል።

ችግሮቹ አስፈጻሚዎች ቁጥር በሚደምሩበት ወቅት የተገኘ የቁጥር ድምር ችግር እና ድምጽ የሰጡ መራጮች፥ ከተመዘገቡት አንጻር ከፍተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

እንዲህ አይነት ችግሮች በሚያጋጥሙበት ወቅት የችግሩን ምንጭ ለማወቅ የድጋሚ ቆጠራ መደረግ ቢኖበትም፥ ቦርዱ በአማራጭ ውጤቶቹ መካከል ያለው የውጤት ልዩነት ከፍተኛ ከመሆኑ አንጻር በውጤቱ ላይ ለውጥ ስለማያመጣና በሂደቱ ተአማኒነት ላይ ጥያቄ ስለማያስነሳ፥ የድጋሚ ቆጠራ በማዘዝ ውጤት ማሳወቂያ ጊዜው መጓተት የለበትም በሚል የድጋሚ ቆጠራ ማካሄድን አስፈላጊ ሆኖ እንዳለገኘውም ጠቅሷል።

በዚህም መሰረት ዓለም አቀፍ የምርጫ ውጤት አስተዳደር ልምድን፣ የምርጫው አይነት ህዝበ ውሳኔ መሆኑ እና በተወሰኑ ጣቢያዎች የተፈጠረው አለመጣጣም በአጠቃላይ የድምጽ ሰጭዎች ድምጽ ላይ የሚያመጣውን ተጽእኖ ውስንነት ከግምት ውስጥ በማስገባት ቦርዱ ችግር የተገኘባቸውን ጣቢያዎች ሁኔታ በማየት ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም ከተመዘገበው መራጭ በላይ ድምጽ ተሰጥቶ የተገኘባቸው የ127 ምርጫ ጣቢያዎች ውጤት እንዲሰረዝ እና በቆጠራ እና በድምር ስሌት ስህተት ከተገኘባቸው ጣቢያዎች መካከል የታየው ልዩነት 10 ድምጽ እና ከዚያ በታች የሆኑ ልዩነቶች ዋጋ እንዳላቸው ድምጽ እንዲቆጠሩ ወስኗል።

ከዚህ ባለፈም ከ10 ድምጽ በላይ የድምር ልዩነት የተገኘባቸው ጣቢያዎች ውጤት እንዳይካተት የወሰነ ሲሆን፥ በዚህ መሰረት 37 ምርጫ ጣቢያዎች በከፍተኛ የድምርና የስሌት ስህተት የተነሳ ውጤታቸው ተሰርዟል።

በአጠቃላይ 164 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያሉ ውጤቶች በተጠቀሱት ምክንያቶች የተነሳ እንዲሰረዙ የተደረገ ሲሆን፥ 71 የምርጫ ጣቢያዎች ግን የድምር ልዩነቱ ከ10 ድምጽ በታች በመሆኑ ስህተት ቢኖራቸውም ውጤታቸው ዋጋ ኖሮት እንዲቀጥል ተደርጓል።

ቦርዱ መሰል ችግሮች በሃገር አቀፍ ምርጫ ላይ ቢፈጠሩ ሊኖራቸው ከሚችለው ተፅዕኖ አንጻር ችግሮቹ የተፈጠሩበትን ምክንያት የሚያጣራ የቴክኒክ ቡድን አቋቁሟል፡፡

የቴክኒክ ቡድኑን ውጤት መሰረት አድርጎም ለቀጣዩ ምርጫ አስፈላጊውን የአቅም ግንባታ ስራዎች፣ የአስፈጻሚዎች ስልጠና እና የምርጫ ሂደቱን የማሻሻል ስራዎችን እንደሚሰራም ገልጿል።

በመጨረሻው ውጤት መሰረትም የተመዘገቡ መራጮች ቁጥር 2 ሚሊየን 304 ሺህ 577 ሲሆኑ ድምጽ የሰጡ መራጮች 2 ሚሊየን 279 ሺህ 22 ናቸው።
ከዚህ ውስጥ 248 ሺህ 97 መሰረዙንም ቦርዱ አስታውቋል።

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ  ጊዜያዊ ውጤትን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድህዳር 13 ቀን 2012 ዓ.ምሃዋሳየደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ህዳር 12 ቀ...
24/11/2019

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ጊዜያዊ ውጤትን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ህዳር 13 ቀን 2012 ዓ.ም
ሃዋሳ

የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ህዳር 12 ቀን 2011 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት የሲዳማ ዞን በክልልነት የመደራጀት ጥያቄ ህዝብ ውሳኔ ህዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም ተካሂዷል።

የህዝበ ወሳኔው አፈፃፀም ተአማኒ፣ ሰላማዊ እና ፍትሃዊ አንዲሆን ለማድረግ ቦርዱ እስከ ህዝብ ውሳኔው ድምጽ መስጫ እለት ድረስ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል። ቦርዱ የህዝበ ውሳኔውን ጥያቄ የማስፈፀም ሀላፊነቱን መወጣት የጀመረው ሂደቱ ፍትሃዊ፣ ሰላማዊ እና ተአማኒ እንዲሆን እንዲሁም በሲዳማ ዞን እና በሀዋሳ ከተማ የሚኖሩ ዜጎች ያለ አድሎ ፍላጎታቸውን የሚገልፁበት አሰራር ለመዘርጋት የሚያስችል የሲዳማ ህዝብ ውሳኔ አፈፃፀም መመሪያ በማጽደቅ ነው፡፡

ከዚህ በተጓዳኝ የህዝብ ወሳኔውን የአፈፃፀም የጊዜ ሰሌዳ በማዘጋጀት ለሚመለከታቸው የክልሉ እና የዞን መስተዳደር አካላት እንዲደርስ ለህዝብም ይፋ እንዲሆን ተደርጓል። ቦርዱ በህዝብ ውሳኔው እቅድ አፈፃፀም ከክልሉና የዞኑ መስተዳደር አካላት ጋር በርካታ ውይይት እና ስምምነቶችን አድርጓል። በዚህም መሰረት ለህዝብ ውሳኔ ማስፈፀሚያ የሚያስፈለገውን በጀት በክልሉ መንግስት እንዲፈቀድ ተደርጓል። ህዝብ ውሳኔው በሰላማዊ ሁኔታ ለማስፈፀም አስፈላጊ ሁኔታዎችን የክልሉ ምክር ቤት አስቀድሞ እንዲፈጽም በጠየቀው መሰረት የህዝቡ ውሳኔ የሲዳማ ዞን በክልልነት እንዲደራጅ የሚል ከሆነ በዞኑ ውስጥ የሚኖሩ ሌሎች ብሔረሰቦች መብት ጥበቃንና አዲስ በሚፈጠረው እና ነባሩ ክልል መሃከል የሚኖረውን የሃብት ክፍፍል የሚወሰንበት አስተዳደርና በህግ ማእቀፍ አውጥቶ አቅርቧል፡፡

በቅድመ ህዝበ ውሳኔ ዝግጅት በቦርዱ ባለሞያዎች የመስክ ጥናት አካሂደው የድምፅ መስጫ ጣቢያዎችን መረጃ አደራጅተዋል፡፡። በዚህም መሰረት ለህዝበ ውሳኔው ማስፈጸሚያ 1692 ምርጫ ጣቢያዎች የተቋቋሙ ሲሆን ከድምጽ ሰጪዎች ምዝገባ በኋላ ተጨማሪ 169 የድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ተደራጅተዋል። የህዝብ ወሳኔው አፈፃፀም ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ እንዲያስችል የክልሉ፣ ከዞኑ፣ ከሃዋሳ ከተማ እንዲሁም የፌደራል የጸጥታ ተቋማት እና አስተዳደር ተቋማት የህዝበ ውሳኔው ፀጥታ እቅድ አዘጋጅተው አቅርበዋል፡፡ የእቅዱንም አፈጻጸም ቦርዱ በጋራ ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ከቅድመ ህዝበ ውሳኔ ዝግጅት እስከ ድህረ ህዝበ ውሳኔ የነበረው የፀጥታና ደህንነት ሁኔታ በዚህ እቅድ መሰረት በጋራ ኮሚቴ በየጊዜው እየታየ ሰላማዊ ህዝበ ውሳኔ ለማካሄድ ተችሏል።

ህዝበ ውሳኔውን በገለልተኝነትና በህግ መሰረት የሚያስፈፅሙ 6843 አስፈፃሚዎችን ከአዲስ አበባ ከተማ እና ኦሮምያ ክልል አከባቢዎች በመመልመል በዞኑ ያሰማራ ሲሆን ሁሉም አስፈጻሚዎች ህዝበ ውሳኔውን እንዴት እንደሚያስፈጽሙ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል፡፡ ስልጠናውም ቀድመው የአሰልጣኞች ስልጠና በወሰዱ 20 አሰልጣኞች ለ5 ቀናት የተከናወነ ሲሆን ሁሉም አስፈጻሚዎች የታተመ የማስፈጸሚያ ማንዋል እንዲኖራቸው ተደርጓል፡፡

የመራጮች ምዝገባ በዞኑ እና በሃዋሳ ከተማ መስተዳድር ለሚኖሩ ማንኛውም ህጋዊ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ዜጎች ክፍት ሆኖ ከጥቅምት 27 እስከ ህዳር 06/2012 ዓ.ም ድረስ ምዝገባው ተካሂዶ 2,280,147 ድምጽ ሰጪዎች ተመዝግበዋል፡፡

የድምጽ ሰጪዎች ህዝበ ውሳኔው ድምጻቸውን ለመስጠት እንዲመዘገቡ ለመቀስቀስ በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተለያዩ የምዝገባ መስፈርቶችን የሚገልጹ እንዲሁም ስለድምጽ አሰጣጡ የሚያብራሩ መልእክቶች ተላልፈዋል፡፡ በድምጽ ሰጪዎች ምዝገባና ድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ የዜጎች መብት እንዳይገደብ እና የሂደቱን ሰላማዊነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከነዚህም መካከል የመጀመሪያው የቦርዱ አመራር አባላት በሃዋሳ፣ በይርጋአለም፣በወንዶ ገነት፣ በበሌላ፣ በመዘዋወር የድምጽ ሰጪዎች ምዝገባና ድምጽ ሰጪዎች ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ክትትል በማድረግ የታዩ ጉድለቶች እና የአሰራር ዝንፈቶች እንዲስተካከሉ ያደረጉ ሲሆን፣ በተጨማሪም ዜጎች በድምጽ ሰጪዎች ምዝገባ እንዲሁም በድምጽ መስጠት ሂደቱ የታዘቧቸውን ግድፈቶች በቀጥታ ለቦርዱ ለማሳወቅ እንዲችሉ የቀጥታ የስልክ መስመሮች ተዘጋጅተው ለመገናኛ ብዙሃን እና ማህበራዊ ሚዲያ ይፋ ተደርጓል፡፡ በደረሱት ጥቆማዎችም መሰረት የተለያዩ ማስተካከያ እርምጃዎች እንዲሁም መረጃዎች ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡

በቦርዱ አባላት በተደረጉ ጉብኝቶች እና ቀደም ብሎ ከዞኑ እና ከክልል መስተዳድር ተቋማት ጋር በተደረጉ ተከታታይ ግንኙነቶች በህዝበ ውሳኔው ሂደት በርካታ ማስተካከያዎች የተደረጉ ሲሆን ከነዚህም ጥቂቶቹ

- የአካባቢ ሚሊሻ አባላት የምርጫ ጣቢያዎችን ጸጥታ አጠባበቅ ምንም አይነት ሚና እንዳይኖራቸው ተደርጓል፡
- በህዝበ ውሳኔው አፈጻጸም ያልተገባ ጣልቃ ገብነት የፈጸሙ ሰዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል፡፤
- በህዝበ ውሳኔው መራጮች ምዝገባ እና ድምጽ መስጠት ሂደት ሁለቱም አማራጮችን የሚወክሉ ወኪሎች አንዲገኙ ጥረት ተደርጓል፡፡
- የተጓደሉ የህዝበ ውሳኔ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶች በፍጥነት እንዲሟሉ ተደርጓል፡፡

የህዝበ ውሳኔውን ሂደት ሰላማዊ ፣ ፍትሃዊነት እና ግልጽነቱን ለማረጋገጥ፣ እንዲሁም ለወደፊት መሻሻል ላለባቸው አሰራሮች ትምህርት ለመውሰድ ለ128 የሲቪል ማህበራት ታዛቢዎች እና 74 የአገር ውስጥና የውጪ ሚዲያ ጋዜጠኞች ሂደቱን እንዲታዘቡና እንዲዘግቡ የሚያስችል እውቅና ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር በመነጋገር የኮሚሽኑ 20 ታዛቢዎች ህዝበ ውሳኔውን እንዲታዘቡ ተደርጓል፡፡ በኢትዮጵያ መንግስት ህዝበ ውሳኔውን እንዲታዘቡ ፍቃድ የተሰጣቸው የአሜሪካን መንግስት ወኪሎችና ዲፕሎማቶች ህዝበ ውሳኔን እንዲታዘቡ አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጓል፡፡

የድምጽ ሰጪዎች ምዝገባ ከተጠናቀቀበት እስከ ድምጽ መስጫው ቀን ባሉት ጥቂት ቀናት ቦርዱ የድምጽ መስጫ ቁሳቁሶችን ያሰራጨ ሲሆን በዚህም ሂደት 3000 የድምጽ መስጫ ሳጥኖች እና 2.5 ሚልዮን በላይ ( መጠባበቂያን ጨምሮ) የድምጽ መስጫ ወረቀቶች እንዲሁም የተለያዩ ቅጾችና ቁሳቁሶች ስርጭት ተከናውኗል፡፡

በህዝበ ውሳኔው ሂደት ጸጥታ እና ደህንነት አስመልክቶ ቦርዱ ሂደቱን በሚመራበት ወቅት የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም መረጃ በመሰብሰብ፣ በሃዋሳ ከተማ እንዲሁም በሌሎች ወረዳዎች የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች የመስክ ጉብኝት አድርጓል፡፡ ከአስተዳደር ወሰን ጋር በተያያዘ እና ቀድሞ ግጭት በነበረባቸው የተወሰኑ ቀበሌዎች ከማህበረሰብ ክፍሎች የቀረቡ አቤቱታዎችን በማዳመጥ የቦርድ አመራር አባላት በቦታው በመገኘት የመስክ ቅኝቶችን አድርገው ከቀበሌ አስተዳደሮች ጋርም ውይይት አድርገዋል፡፡ ከውይይቱም በተጨማሪ የሲዳማ ዞን እና የደቡብ ክልል የጸጥታ አካላት፣ የፌደራል ፓሊስ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊትን ያካተተ የፀጥታ ችግሮችን በጋራ የሚያይ መድረክ በማቋቋም ሂደቱ ሰላማዊ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

ኅዳር 10 ቀን የተከናወነው የድምጽ መስጠት ሂደት ሰላማዊ እና ጉልህ የሎጄስቲክስ ችግር ያልታያበት ሲሆን አንዳንድ ቦታዎች ላይ የመራጮች ቁጥር ከፍተኛ በመሆኑ ሰልፎች ከመኖራቸው በስተቀር በታቀደበት ሁኔታ ተጠናቋል፡፡ በእለቱ የቦርድ አመራር አባላት የመስክ ጉብኝቶችን ያካሄዱ ሲሆን የምርጫ ቆጠራውም በእለቱ ተጠናቆ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ተለጥፏል፡፡ በእለቱ ከመራጮች የሚመጡ ጥቆማዎችንም መሰረት በማድረግ የተለያዩ እርምት እርምጃዎች ሲከናወኑ ውለዋል፡፡

በዚህም መሰረት በአጠቃላይ ከተመዘገበው 2,280,147 መራጭ 2,277,063 ሰው ድምጹን ሰጥቷል፡፡ ይህም የምርጫ ቀን የድምጽ መስጠት ተሳትፎ ( voter turnout) 99.86 በመቶ መሆኑን ያሳያል፡፡ ሲዳማ በነባሩ ክልል ውስጥ እንዲደራጅ ጎጆ ምልክትን የመረጠ ሰው ብዛት 33,463 ሲሆን የሲዳማ በክልልነት መደራጀትን ሻፌታን የመረጠ ሰው ብዛት 2,225,249 ነው፡፡ በውጤቱም ሻፌታ የመረጠው 98.51 % ሲሆን ጎጆን የመረጠው 1.48 % ነው፡፡ ፡፡ በሂደቱ የዋጋ አልባ ድምጽ ቁጥር 18,351(0.000002%) ነው፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት አንቀጽ 47/2/ እና /3/ ማንኛውም ብሄር ብሄረሰብ ወይም ህዝብ የራሱ ክልል የመቋቋም መብት አለው በማለት በሚደነግገው መሰረት የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ህጋዊና ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ ተፈጽሟል፡፡ የዞኑ ነዋሪዎች በነፃ ፈቃዳቸው በሰጡት ውሣኔ መሰረት ሲዳማ ክልል ሆኖ መደራጀት የሚያስችለውን ድምፅም በዚህ ውሳኔ አግኝቷል፡፡

የህዝበ ውሳኔው ሂደት ሰላማዊና ተአማኒ እንዲሁም ከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ የታየበት ነው፡፡ ህዝበ ውሳኔው ዜጎች መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ ተግባራዊ ያደረጉበት እና በሀገራችን የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ አንድ እርምጃ ነው ብሎ ቦርዱ ያምናል፡፡ በውጤቱ መሰረትም በህገ መንግስቱ አንቀጽ 47/3/መ ላይ እንደተጠቀሰው የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት እና በሲዳማ ዞን አስተዳደር የህዝቡን ድምጽ ባከበረ፣ ሰላማዊ እና ግልጽ በሆነ መልኩ እንዲሁም ሽግግሩን ጊዜን በጠበቀ ሁኔታ በማከናወን የስልጣን ርክክቡን በአግባቡ አከናውነው ይህንን ህዝበ ውሳኔ ውጤት እንደሚያስፈጽሙ ቦርዱ የጸና እምነት አለው፡፡


ያጋጠሙ ተግዳሮቶች

የህዝበ ውሳኔው አፈፃፀም ሰላማዊና ህጋዊ መሆኑ በዚህ ሂደት የተገኘ በጎ ውጤት ሲሆን፣ ለዝግጅት ከነበረው አጭር ጊዜም አንጻር የቦርዱ አፈጻጸም የተሳካ ነው ብሎ ያምናል፡፡ የአፈፃፀም ሂደቱ ጠቃሚ ትምህርት የተገኘበት መሆኑን ያህል ተግዳሮቶች የነበሩበት በመሆኑ ለቀጣይ ትምህርት ይሆን ዘንድ የሚከተሉትን ማንሳት ተገቢ ይሆናል፤

•የህግ ማዕቀፍ እንዲወጣ (የአነስተኛ ቡድኖች መብት ጥበቃ፤ የሀብት ክፍፍል) በቦርዱ የቀረበው ጥያቄ በክልሉ ምክር ቤት የተሰጠው ምላሽ መዘግየት

•የህዝበ ውሳኔው ቅስቀሳ ሂደት የአንድን ወገን አማራጭ ብቻ የቀረበበት መሆኑ እና የህዝበ ውሳኔውን ሂደት እንዲታዘቡ የክልሉ መንግስት ወኪሎች እንዲመድብ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢቀርብለትም አለመመደቡ

•የድምጽ መስጫ ጣቢያዎችን ለመወሰን የሚያስፈልገው የህዝብ ቁጥር የተሟላ መረጃ አለመኖር

•በተወሰኑ የሀዋሳ ከተማን የገጠር አካባቢ ድምፅ መስጫ ጣቢያዎች የማይመለከታቸው ሰዎች መገኘት፣ በድምፅ ሰጪዎች ላይ በአንዳንድ ጣቢያዎች ተፅእኖ የማሳደር ሁኔታ መታየት

•በአንዳንድ ቦታዎች በድምፅ ሰጪዎች ብዛት ምክንያት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች መጨናነቅ መከሰቱ

•በህዝበ ውሳኔው ውጤት አገላለጽ ላይ ከሃዋሳ ከተማና ከዞኑ መስተዳድ ተቋማት ሃላፊዎች በቦርዱ ይፋዊ መግለጫ ከመሰጠቱ በፊት አስቀድሞ የመመገመት (Projection) እና የመግለጽ ችግር መታየቱ

•በአንዳንድ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች በህግ የተቀመጠን የምርጫ ጣቢያ መክፈቻ እና መዝጊያ ሰአት አለመጠበቅ እንደዋና ተግዳሮት የሚጠቀሱ ሲሆን ማለትም የክልሉ የጸጥታ ተቋማት፣ የደቡብ እዝ የአገር መከላከያ ሰራዊት) የህዝበ ውሳኔ ቁሳቁስ ማጓጓዝ፣ የአካባቢ ጸጥታ እና ደህንነትን በመጠበቅ፣ የአስፈጻሚዎች ስምሪትን እንዲሁም ድምጽ የተሰጠባቸውን ሰነዶችን ጥበቃ በማድረግ እጅግ የሚመሰገን ድጋፍ ማድረጋቸው እና በህዝበ ውሳኔው ሂደት ከፍተኛ ቅንጅት መኖሩ እንደትልቅ ስኬት የሚነሳ ነው፡፡

ምስጋና
በሲዳማ የክልልነት የመደራጀት ህዝበ ውሳኔ እስካሁን በሃገራችን ከነበረው ልምድ የተለየ እና መጀመሪያው ቢሆንም ሰላማዊ እና ህጋዊ በሆነ ሁኔታ ሊፈጸም ችሏል፡፡ ይህንን ህዝበ ውሳኔ ስኬታማ ለማድረግ ቦርዱ ከተለያዩ አካላት፣ ተቋማት እና ግለሰቦች ድጋፍ አግኝቷል፡፡ በዚህም መሰረት የኢትዪጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሚከተሉት ተቋማትና ግለሰቦች ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

-በህዝበ ውሳኔው በሰላማዊ እና ስነሰርአት ባለው ሁኔታ ለተሳተፉት የሲዳማ ዞን ነዋሪዎች በሙሉ
-ከመኖሪያ አካባቢያቸው ርቀው በመሄድ ባልተሟላ አንዳንዴም በአስቸጋሪ ሁኔታ ህዝበ ውሳኔውን ላስፈጻሙ የህዝበ ውሳኔው አስፈጻሚዎች እና ስራውን በማስተባበር ለደከሙ የቦርዱ ሰራተኞች
-ለህዝበ ውሳኔው አስፈጻሚዎች ምልመላ ድጋፍ ያደረጉልን፣ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ከንቲባ ፣ ለአ.አ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ፣ የአአ ትምህርት ቢሮ፣ የአአ ጤና ቢሮ ፣ ለኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ
-ለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤትለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ርእሰ መስዳድር እና የርእሰ መስተዳድሩ ጽህፈት ቤት
-ለሲዳማ ዞን ምክር ቤት
-ለሲዳማ ዞን አስተዳደር
-ለሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት
-ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሃገር መከላከያ ሰራዊትና ለአገር መከላከያ ሰራዊት ደቡብ እዝ
-ለፌደራል ፓሊስ
-ለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ፓሊስ ኮሚሽን
-ለሲዳማ ዞን ፓሊስ
-ለሃዋሳ ከተማ ፓሊስ
-ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን
-ህዝበውሳኔውን ለመታዘብ ለተሳተፉ ሲቪል ማህበራት
-የተለያዩ እገዛን ላደረጉልን የአሜሪካን የልማት ድርጅት (USAID/IFES) እና የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (UNDP)
-ለአዲስ ፓርክ

በሲዳማ የህዝብ ውሳኔ ጥቅም ላይ በሚውሉ ምልክቶች ውይይት ተደርጎ ይፋ ሆኑ********************************************************የሲዳማ ዞን ክልል ሆኖ ለመ...
26/09/2019

በሲዳማ የህዝብ ውሳኔ ጥቅም ላይ በሚውሉ ምልክቶች ውይይት ተደርጎ ይፋ ሆኑ
********************************************************

የሲዳማ ዞን ክልል ሆኖ ለመደራጀት በሚካሄደው የህዝብ ውሳኔ ጥቅም ላይ በሚውሉ ምልክቶች ላይ በቂ ውይይት ከተካሄደ በኋላ ይፋ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡

በምልክቶቹ የመጀመሪያው ረቂቅ ላይ ለመወሰን የደቡብ ክልል ምክር ቤት ውይይት ማድረጉን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮምዩኒኬሽንስ አማካሪ ወ/ት ሶሊያና ሽመልስ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡

በህዝበ ውሳኔው የሚቀርቡ ምልክቶቹ ምን አይነት ይሁኑ በሚለው እና ምልክቶቹ በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ገለልተኛ፣ የማህበረሰቡን ምስል የሚያሳዩ እንዲሁም ጥያቄዎቹን ግልጽ እንዲሆኑ ተሰርቷል ተብሏል፡፡

በውይይቱ ላይ ስምምነት የተደረሰባቸው ምልክቶች ለህዝብ ይፋ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

በዚህም መሰረት፡-
1. “ሲዳማ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ውስጥ እንዲቆይ እፈልጋለሁ” ለሚለው አማራጭ የጎጆ ቤት ምልክት፣

2. “ሲዳማ ራሱን ችሎ በክልልነት እንዲደራጅ እፈልጋለሁ” ለሚለው አማራጭ የሻፌታ ምልክት ሆኖ ለህዝበ ውሳኔው ድምጽ መስጫነት እንዲያገለግል የተወሰነ መሆኑን ቦርዱ አስታውቋል።

የህዝበ ውሳኔው አፈጻጸሞች በክልሉ ጥያቄ ለተወሰኑ ቀናቶች ከተራዘሙት ውጪ አብዛኞቹ በተያዘላቸው መርሀ ግብር እየተከናወኑ እንደሆነም ተነግሯል፡፡

የህግ አስፈጻሚ እና የጸጥታ አካላት እንዲሁም የቦርዱ የስራ አመራር አባላት የህዝበ ውሳኔውን አፈጻጸም ሰላማዊነት ለማረጋገጥ ውይይት ማካሄዳቸው ታውቋል፡፡

የድምፅ ሰጪዎች ምዝገባ፣ እንዲሁም የድምፅ መስጫ እና ድህረ ምርጫ ሂደቱን ሰላማዊነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የምርጫ አስፈጻሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ የህግ አስፈጻሚ አካላት ትብብር እንደሚያስፈልግ ቦርዱ ለተሳታፊዎቹ ማስገንዘቡ ተገልጿል፡፡

ለህዝበ ውሳኔ ምርጫ አስፈፃሚዎች ስልጠና በአዲስ አበባ ከተማ ከመስከረም 24-30 ከተሰጠ በኋላ እንደሚሰማሩም ተነግሯል፡፡

በቀጣይ የሚካሄዱ ተግባራትም በመርሃ ግብሩ መሰረት ለማከናወን ዝግጅቶች እየተካሄዱ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በማስተዋል መታፈሪያ

Ethiopia, as the Birthplace of Coffee, is known throughout the world for its rich variety of coffees and cup profiles. S...
23/09/2019

Ethiopia, as the Birthplace of Coffee, is known throughout the world for its rich variety of coffees and cup profiles. Some buyers use words like floral, spicy, juicy and mysterious to describe our coffees. Others are lost for words.

Coffee is found throughout our country in many types of environments from a few trees in a small household garden, to a vast forested hillside where it grows wild. We believe this diversity is our greatest asset.

The Shebedino Coffee Farmers Cooperative represents 4 primary cooperatives as well as 20,000 independent smallholder producers in the Sidama Region of southern Ethiopia. Typically, producers here cultivate coffee under a shade canopy of native trees. They intercrop coffee with other crops for subsistence farming and to have an alternative source of income.

Shebedino coffees exemplify this wealth of flavors and landscapes. From the rugged Highlands of Arbegona mero, Asarado mero, Telamo to the valleys of Taramsa, Fura and the Northern side Howolso Primary coffee farmers there is coffee. Shebedino produces more washed coffee than any other woreda's in the Sidama Region and has built a reputation for quality over many decades. Coffee is engrained in our people's way of life.

The Shebedino Coffee Farmers Cooperative provides marketing, Finance and technical services to societies and over 20,000 farmers.

☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆በአለም ለ97ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ11ኛ ጊዜ የሚከበረዉ አለም አቀፍ የኅብረት ስራ ቀን በነገዉ ዕለት በደማቅ ሁነታ ይከበራል ለዚህም በዛሬዉ ዕለት ከተለያየ አ...
06/06/2019

☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆☆
በአለም ለ97ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ11ኛ ጊዜ የሚከበረዉ አለም አቀፍ የኅብረት ስራ ቀን በነገዉ ዕለት በደማቅ ሁነታ ይከበራል ለዚህም በዛሬዉ ዕለት ከተለያየ አከባቢ እንግዶች ስገቡ የሐር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፖሊስ ማርሽ ባንድ ደማቅ አቀባበል አድርጎልናል።
በአሉ "ኅብረት ስራ ማኅበራት ለፍትሀዊነትና ዘላቂ ሰላም" በሚል መሪ ቃል ግንቦት 30 _ ሰኔ 1 ቀን 2011 ዓ.ም ነገ ከጧዋቱ 2:30 ጀምሮ በሀረሪ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሀረር ከተማ አሚን አብዱላህን አደራሽ በታላቅ ስነ ስርአት ይከበራል። በዚህ መድረክ በመጀመሪያዉ ዕለት የተሻለ ተሞክሮ ያላቸዉ ኅብረት ስራ ማኅበራት ተሞክሯቸዉን የሚያካፍሉበት ሲምፓዚየም የሚካሄድ ሲሆን በሁለተኛዉ እና በማጠናቀቂያዉ እለትም ለዘርፉ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት ፣ ግለሰቦች እንዲሁም በተለያዬ ዘርፍ የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ኅብረት ስራ ማኅበራት ፣ ግለሰብ አባላት ፣ ህጻናት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እዉቅና የሚያገኙበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል ።
ለዚህ ፕሮግራም የሸበዲኖ ወረዳ ኅብረት ሥራ ል/ጽ/ቤት
እና ቴላሞና አከባቢዉ ሁለ/የገ/መ/ኅ/ሥ/ማህበር በፈደራል ደረጃ ተሸላም ሆኖ ቀርቧል።

Address

Awassa

Telephone

+251462260060

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shabe Woreda Cooperative Development Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Shabe Woreda Cooperative Development Office:

Share