Prosperity Party Hawassa City Branch Office

Prosperity Party Hawassa City Branch Office Building a brighter future for Hawassa through economic growth, social equity, and community development. Join us in creating prosperity for all residents.

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ ፍፁም ሰላማዊ፣ ተዓማኒነት ያለውና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ በመጠናቀቁ የምስጋና መድረክ ተካሄደ። የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ...
04/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ ፍፁም ሰላማዊ፣ ተዓማኒነት ያለውና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ በመጠናቀቁ የምስጋና መድረክ ተካሄደ።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማ ደረጃ ፍፁም ሰላማዊ፣ ተዓማኒነት ያለውና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ በመጠናቀቁ ለከተማዋ አመራር እና የፀጥታ አካላት የምስጋና መድረክ አካሄደ።

የከተማው አጠቃላይ አመራርና የፀጥታ መዋቅሩ ቁርጠኝነትና ቅንጅት ለምርጫው ስኬታማነት ፍትሃዊ፣ ገለልተኛ ፣ነፃና ታዓማኒነት ያለው ምርጫ ለማካሄድ እጀ ንፁህና ልበ ንፁህ ሆኖ ማገልገሉና የተሰጠውን አቅጣጫ ተቀብሎ የመራበት አግባብ ለምርጫው ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱም ከመድረኩ ተመላክቷል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ታሪካዊ ምርጫ መሆኑን መድረኩን የመሩት የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገልፀው ለምርጫው ሰላማዊነትና ዴሞክራሲያዊነት ለሰሩና በምርጫው ሂደት ለተሳተፉ ለሁሉም አካላት የሚያኮራ ውጤት የተመዘገበበት ምርጫ መሆኑን አክለዋል።

የምርጫው ስኬት እንደተጠበቀ ሆኖ በከተማዋ በበጀት ዓማቱ የተጀመሩ የልማት ስራዎች በተያዘላቸው የጊዜ እና የዲዛይን ጥራት መሰረት ተጠናቀው ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እና በድል ለማጠናቀቅ በላቀ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም ከንቲባው አያይዘው ገልፀዋል።

የሐዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ዋና ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ በበኩላቸው ነዋሪው የተለያዩ ጫናዎችን ተቋቁሞ በምርጫው በነቂስ በመሳተፍ ዴሞክራሲያዊ መብቱን መጠቀሙ የከተማው ነዋሪ ሰላም ወዳድነት አንዱ ማሳያ መሆኑን ገልፀው በቅንጅትና በጋራ ከተሰራ በምርጫው የተመዘገበው ውጤት ማንኛውንም ስራ በብቃት ማሳካት እንደሚቻል አመላካች ነውም ብለዋል።

በመድረኩ በክብር እንግድነት የተገኙት የሲዳማ ክልል ከተማና መሰረተልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ሰለሞን በነዋሪው ሰላም ወዳድነትና የጎለበተ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ እንዲሁም በምርጫ ስራው በአመራሩና የፀጥታ አካላት ገለልተኛ፣ ፍትሃዊና ነፃ ሆኖ ማገልገል ምርጫው ፍፁም ሰላማዊና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆኖ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

ዘገባው የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ ነው

የሐዋሳ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።ምክር ቤቱ ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን ተከ...
02/06/2026

የሐዋሳ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በሰላም መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

ምክር ቤቱ ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ ነው ለጋዜጤኞች ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጠው ።

የሐዋሳ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምቤት ቤት ሰብሳቢ አቶ ደምሴ ስኳሬ የምርጫ ሂደቱ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሲገልጹ ህዝቡ በጉጉት ሲጠብቅ የነበረ መሆኑን በመጠቆም ነው ።

የፖለቲካ ፓርቲዎች መልካም ስነምግባር ከህዝባችን ጨዋነት ጋር ተደምሮ በስኬት መጠናቀቁን የገለጹት አቶ ደምሴ ምርጫው በሰላማዊ መንገድ እንዳይከናወን የሚያደርግ ምንም አይነት ነገር አለመኖሩን ገልጸዋል።

አቶ ደምሴ አያይዘውም ለምርጫው በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቅ ከተማ አስተዳደሩ፣ ባለድርሻ አካላትና የጸጥታ ሀይሉ ሚና ትልቅ መሆኑን በምስጋና ጭምር ገልጸዋል።

የድምጽ አሰጣጡ በተቀመጠለት ጊዜው ገደብ የተጠናቀቀ መሆኑን የገለጹት አቶ ደምሴ ዋናው ውጤት በሀገር ደረጃ እስኪገለጽ ድረስ ፓርቲዎች በትግዕስት መጠበቅና በጸጋ በመቀበል ሀገርን ማስቀጠል ይመጠበቃል ብለዋል።

ም/ቤቱ ከምርጫ በፊት ያከናወናቸው ስራዎች ስልጠና ውይይትና ምክክሮች ለምርጫ ሂደቱ ምቹ ሁኔታ መፍጠር ስለመቻሉም አቶ ደምሴ አክለው ተናግረዋል።
👉ሐዋሳ የ/ሐ/ከ/መ/ኮ/መምሪያ

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ።ምክር ቤቱ የምርጫው መጠናቀቅን ተከትሎ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎ...
02/06/2026

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገለፀ።

ምክር ቤቱ የምርጫው መጠናቀቅን ተከትሎ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የሲዳማ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ በለጠ ሰጌቦ በዚህ ወቅት እንደገለፁት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሲዳማ ክልል ደረጃ በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል 23 የተመዘገቡ ሀገራዊና ክልላዊ ፓርቲዎች ያሉ ሲሆን 18ቱ ለምርጫው ዕጩዎቻቸውን ያቀረቡ ናቸው።

በክልሉ 19 የምርጫ ክልሎች እና 2266 የምርጫ ጣቢያዎች እንዳለውም ከምርጫ ቦርድ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ በለጠ በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት እንደገለፁት ከምርጫው በፊት በክልሉ ያሉ ፓርቲዎች ለሀገር የጋራ ጥቅም በቅርርብ መስራታቸው በምርጫው ወቅት ለተገኘው ውጤት መደላድል መፍጠሩን ተናግረዋል ።

በምርጫው ቀን በሁሉም አከባቢዎች ምርጫ መካሄዱን አንስተው ከየትኛውም ፓርቲ ቅሬታ አለመቅረቡን ተናግረዋል ።

ቅሬታዎች ብመጡም እንኳን በሰከነ መንገድ በንግግር ይታሉ ነው ያሉት።

በምርጫው ዕለት አመሻሽ 12 ሰዓት አከባቢ በርካታ ዜጎች አለመምረጣቸው በማስታወስ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰዓት መጨመሩ ተገቢ ነበር ብለዋል።

በአሁን ወቅት ግዜያዊ ውጤት በየምርጫ ጣቢያዎች እየተገለፀ ያለ ሲሆን ጠቅላላ ውጤት በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሚገለፅ በመሆኑ በትዕግሥት መጠበቅ ይገባል ብሏል የጋራ ምክር ቤቱ።

የኢትዮጵያ ህዝብ በምርጫ ካርዱ ፍላጎቱን ገልጿል ያሉት አቶ በለጠ የህዝቡን ድምፅ ማክበር ደግሞ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ይጠበቃል ብለዋል።

ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የፖለቲካ ልዩነታቸው እንደተጠበቀ ለሀገር ሰላምና አንድነት በጋራ እንዲሰሩ የጋራ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል ።
SBC

በሐዋሳ ከተማ የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤት እየለጠፉ ነውበሐዋሳ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ በማጠናቀቅ ጊዜያዊ ውጤት እየለጠፉ ይገኛሉ፡፡በትናንትናው ዕለት በተካሄደ...
02/06/2026

በሐዋሳ ከተማ የሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤት እየለጠፉ ነው

በሐዋሳ ከተማ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ ቆጠራ በማጠናቀቅ ጊዜያዊ ውጤት እየለጠፉ ይገኛሉ፡፡

በትናንትናው ዕለት በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሐዋሳ ምርጫ ክልል በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጽ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

በዚህም በከተማዋ የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤቶችን ለሕዝብ እይታ ግልጽ በሆኑ ቦታዎች እየለጠፉ ይገኛል።

አሁንም መራጩ ህዝብ ድምፁን ለመስጠት ያለውን ጊዜ እየተጠቀመ ይገኛል!!!አሁናዊ ድባብ በሀዋሳ ምርጫ ክልል ጨፌ ቀበሌ መሳፍንት ዘለቀ ምርጫ ጣቢያ
01/06/2026

አሁንም መራጩ ህዝብ ድምፁን ለመስጠት ያለውን ጊዜ እየተጠቀመ ይገኛል!!!

አሁናዊ ድባብ በሀዋሳ ምርጫ ክልል ጨፌ ቀበሌ መሳፍንት ዘለቀ ምርጫ ጣቢያ

ኢትዮጵያ ትቀጥላለች ፣ ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ይቀየራል ፣በኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ ሀገረ መንግስት እንገነባለን።ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ #ኢትዮጵያእየመረጠችነው...
01/06/2026

ኢትዮጵያ ትቀጥላለች ፣ ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ይቀየራል ፣በኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ ሀገረ መንግስት እንገነባለን።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ

#ኢትዮጵያእየመረጠችነው

በአዲስ አበባ አስተዳደር በም/ከንቲባ ማዕረግ ስራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማትዎስ በተወዳደሩበት በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በደሴ ምርጫ ክልል ተገኝተው ድምጻቸውን ሰጥተዋ...
01/06/2026

በአዲስ አበባ አስተዳደር በም/ከንቲባ ማዕረግ ስራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ቢሮ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማትዎስ በተወዳደሩበት በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን በደሴ ምርጫ ክልል ተገኝተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።

#ኢትዮጵያእየመረጠችነው

የኢፌዴሪ ፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፃቸውን ሰጡ። ሚኒስትሯ በሐዋሳ ምርጫ ክልል በብልፅግና ፓርቲ በኩል ለተወካዮች ምክር ቤት በእጩነት ቀርበው እየተ...
01/06/2026

የኢፌዴሪ ፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሰፋ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፃቸውን ሰጡ።

ሚኒስትሯ በሐዋሳ ምርጫ ክልል በብልፅግና ፓርቲ በኩል ለተወካዮች ምክር ቤት በእጩነት ቀርበው እየተወዳደሩ ሲሆን በሚሊንየም ቀበሌ ደብረ ወርቅ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ዶ/ር ፍጹም አሰፋ እንደገለፁት፣ ምርጫው በሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ መንገድ እየተካሄደ ሲሆን መራጮችም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በንቃት እየተሳተፉ መሆኑን ጠቅሰው በቀሪው ሰዓትም መራጮች ድምፃቸውን በመስጠት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

የምርጫ ሂደቱ በከተማዋ በሚገኙ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች በሰላም እየተካሄደ መሆኑንም ዶ/ር ፍፁም አሰፋ ጨምረው ገልፀዋል።
👉የሐ/ከ/አስ/የመ/ኮ/ጉ/መምሪያ

የሲዳማ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃ ማርሻሎ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
01/06/2026

የሲዳማ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃ ማርሻሎ ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

 ምርጫ የሀገሬ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጉዳይ ነው ያለ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን እየሰጠ ይገኛል።
01/06/2026


ምርጫ የሀገሬ ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጉዳይ ነው ያለ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን እየሰጠ ይገኛል።

Address

Awassa
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prosperity Party Hawassa City Branch Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share