07/08/2026
በፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ፣ በከተማ ፅዳት፣ ውበትና አረንጓዴ ልማት ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ውይይት አካሄደ
የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ በፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር፣ በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች፣ በከተማ ፅዳት፣ ውበትና አረንጓዴ ልማት ሥራዎች እንዲሁም በሌሎች የከተማው ወቅታዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በውይይቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች፣ የወሳኝ ኩነት አመራሮች፣ የሴቶችና የወጣቶች ክንፍ አመራሮች በመገኘት በተነሱ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። በተለይም የፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ ፕሮግራምን በማጠናከር የዲጂታል ክህሎትን ማሳደግ፣ መልካም አስተዳደርን ማጠናከር፣ የከተማውን ፅዳትና ውበት በዘላቂነት ማስጠበቅ እንዲሁም አረንጓዴ ልማትን በህዝባዊ ተሳትፎ ማስፋፋት የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተወያይተዋል።
ተሳታፊዎች የከተማውን ልማታዊ እንቅስቃሴዎች በቅንጅትና በተጠያቂነት ለማስቀጠል፣ የፓርቲ አደረጃጀቶች ከህብረተሰቡ ጋር ያላቸውን ቅርበት በማጠናከር ለከተማው እድገትና ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚያበረክቱ ሥራዎችን በትኩረት ለማስፈጸም የጋራ ግንዛቤ ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።