Prosperity Party Hawassa City Branch Office

Prosperity Party Hawassa City Branch Office Building a brighter future for Hawassa through economic growth, social equity, and community development. Join us in creating prosperity for all residents.

በፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ፣ በከተማ ፅዳት፣ ውበትና አረንጓዴ ልማት ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ውይይት አካሄደየሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ በፋይዳ ኢት...
07/08/2026

በፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ፣ በከተማ ፅዳት፣ ውበትና አረንጓዴ ልማት ዙሪያ የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ውይይት አካሄደ

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ በፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ መርሃ ግብር፣ በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች፣ በከተማ ፅዳት፣ ውበትና አረንጓዴ ልማት ሥራዎች እንዲሁም በሌሎች የከተማው ወቅታዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ያተኮረ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በውይይቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊዎች፣ የወሳኝ ኩነት አመራሮች፣ የሴቶችና የወጣቶች ክንፍ አመራሮች በመገኘት በተነሱ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። በተለይም የፋይዳ ኢትዮ-ኮደርስ ፕሮግራምን በማጠናከር የዲጂታል ክህሎትን ማሳደግ፣ መልካም አስተዳደርን ማጠናከር፣ የከተማውን ፅዳትና ውበት በዘላቂነት ማስጠበቅ እንዲሁም አረንጓዴ ልማትን በህዝባዊ ተሳትፎ ማስፋፋት የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተወያይተዋል።

ተሳታፊዎች የከተማውን ልማታዊ እንቅስቃሴዎች በቅንጅትና በተጠያቂነት ለማስቀጠል፣ የፓርቲ አደረጃጀቶች ከህብረተሰቡ ጋር ያላቸውን ቅርበት በማጠናከር ለከተማው እድገትና ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚያበረክቱ ሥራዎችን በትኩረት ለማስፈጸም የጋራ ግንዛቤ ላይ መድረሳቸው ተገልጿል።

የሀዋሳ ከተማ ጽዳትና ውበትን በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከህብረተሰብ አደረጃጀቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደየሀዋሳ ከተማ ጽዳትና ውበትን በዘላቂነት ለማስጠበቅ፣ የህዝብ ተሳትፎን ለማጠናከር እ...
06/08/2026

የሀዋሳ ከተማ ጽዳትና ውበትን በዘላቂነት ለማስጠበቅ ከህብረተሰብ አደረጃጀቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ

የሀዋሳ ከተማ ጽዳትና ውበትን በዘላቂነት ለማስጠበቅ፣ የህዝብ ተሳትፎን ለማጠናከር እና የህግ ማስከበር ስርዓቱን ለማጎልበት ያለመ የምክክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ አዘጋጅነት ከተለያዩ የህብረተሰብ አደረጃጀቶች ጋር ተካሂዷል።

በመድረኩ የከተማዋን ጽዳት፣ ውበትና ሥርዓት የሚጎዱ ተግባራትን በመከላከል የሁሉንም ዜጎች ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ ተገልጿል። በተለይም የግንባታ ግብዓቶችን በየመንገዱ አግባብ ባልሆነ መንገድ መደርደርና ማራገፍ፣ የመሠረተ ልማት ስርቆትን መከላከል፣ ስድ የሚለቀቁ እንስሳትን መቆጣጠር እንዲሁም እያንዳንዱ ባለይዞታ በይዞታው ዙሪያ 20 ሜትር ራዲየስ ያለውን አካባቢ በተከታታይ የማጽዳት ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት በመስጠት አቅጣጫ ተሰጥቷል።

በውይይቱ እነዚህን አሰራሮች በዘላቂነት ለማስፈጸም በየደረጃው ያሉ የህብረተሰብ አደረጃጀቶችና መዋቅሮች በቅንጅት እንዲሰሩ፣ የቁጥጥር ሥርዓቱ እንዲጠናከር እና ህግን የማስፈጸም ሥራ በተጠያቂነት እንዲከናወን አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

ተሳታፊዎችም ንጹህ፣ ውብና ለነዋሪዎችና ለጎብኚዎች ምቹ የሆነች ሀዋሳን ለመገንባት የሁሉም ዜጋ ተሳትፎ፣ የተቋማት ቅንጅት እና የህግ የበላይነት በተግባር መረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን በማስገንዘብ በየደረጃው የተጣለባቸውን ኃላፊነቶች በብቃት ለመወጣት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።

የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ለማሳካት የሚያግዙ ግብዓቶች ለሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ተረከቡሀዋሳ፦ የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በቀጣይ...
06/08/2026

የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎትን ለማሳካት የሚያግዙ ግብዓቶች ለሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ተረከቡ

ሀዋሳ፦ የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በቀጣይ በሚያከናውነው የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር የሚውሉ የተለያዩ ግብዓቶችን ከሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችና ከሌሎች የፓርቲ አደረጃጀቶች ተረክቧል።

በዚህ መሰረት የታቦር፣ የባህል አዳራሽና የመናኸሪያ ክፍለ ከተሞች ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሁም የኢንዱስትሪ ዘርፍ የፓርቲ አደረጃጀት ለመርሃ ግብሩ የሚያገለግሉ ግብዓቶችን በማስረከብ ያላቸውን ድጋፍና ተሳትፎ አረጋግጠዋል።

የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤቱ የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የመደጋገፍ፣ የመተባበርና የማህበራዊ ኃላፊነት እሴቶችን በማጠናከር ለወገኖች ተጨባጭ ድጋፍ ለማድረስ የታለመ መሆኑን ገልጿል። ለመርሃ ግብሩ የተደረገው የግብዓት ድጋፍም የአደረጃጀቶች አንድነትና የተቀናጀ አሰራር ማሳያ መሆኑ ተጠቁሟል።

የሀዋሳ ከተማ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን ገምግሟልየሀዋሳ ከተማ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ በ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ ፍ...
06/08/2026

የሀዋሳ ከተማ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ እስካሁን የተከናወኑ ተግባራትን ገምግሟል

የሀዋሳ ከተማ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ በ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ ግብር ማዕቀፍ እስካሁን የተከናወኑ የአገልግሎት ተግባራትን በመገምገም የቀሩ ሥራዎችን በተቀናጀ መንገድ ለማጠናቀቅ አቅጣጫ አስቀምጧል።

በግምገማው ወቅት በክረምቱ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብር የተካተቱ 14 የአገልግሎት ዘርፎች አሁናዊ የአፈጻጸም ሂደት በዝርዝር ተገምግሟል። በዚህም የአቅመ ደካሞች ቤት ጥገና፣ የደም ልገሳ፣ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ የአካባቢ ጽዳት፣ ማህበራዊ ድጋፍና ሌሎች በክፍለ ከተሞች እና በከተማ ደረጃ የተከናወኑ ተግባራት የደረሱበት ሁኔታ ተመልክቷል።

በግምገማው ላይ ተሳታፊዎች እስካሁን የተመዘገቡ ውጤቶች የሚበረታቱ መሆናቸውን በመግለጽ፣ በቀሪው የአገልግሎት ጊዜ የተጀመሩ ሥራዎች በጥራትና በወቅቱ እንዲጠናቀቁ የሁሉም አካላት ቅንጅታዊ ርብርብ ሊጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።

አብይ ኮሚቴው በተለይም ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ የግል ዘርፍ እና ህብረተሰቡ በጀመሩት የበጎ ፍቃድ እንቅስቃሴ ያሳዩትን ተሳትፎ በማድነቅ፣ በቀሪው የመርሃ ግብር ጊዜም ተሳትፏቸውን በማጠናከር ሀዋሳን የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የአብሮነት እሴቶች የሚጎለብቱባት ከተማ ለማድረግ የጀመረው ጥረት በተሻለ ውጤት እንዲቋጭ ጥሪ አቅርቧል።

መድረኩን የሀዋሳ ከተማ ዋና የመንግስት ተጠሪ እና የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ መርተውታል።

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በቀጣይ ለሚያከናውነው የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ግብአቶችን የሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ...
05/08/2026

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በቀጣይ ለሚያከናውነው የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ግብአቶችን የሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስረከበ።

ድጋፉ የፓርቲው አባላት በመተባበር ማኅበራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣትና የመደጋገፍ ባህልን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።

ግብአቶቹን የሐይቅ ዳር ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀሪሁን መኮንን እና የክፍለ ከተማው ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ መሰረት ተስፋዬ በጋራ አስረክበዋል። በዚሁ ወቅት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብሩ የመተሳሰብ፣ የአንድነትና የህብረተሰብ አገልግሎት እሴቶችን በተግባር የሚያጎለብት መሆኑ ተጠቅሷል።

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በቀጣይ በሚያካሂደው የወሰን ተሸጋሪ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎችን በመደገፍ ማህበራዊ ትስስርን ከማጠናከር ባሻገር የብልፅግና ፓርቲ የመደጋገፍ፣ የመረዳዳትና የጋራ ብልፅግና እሴቶችን ወደ ተግባር ለመቀየር የሚያስችል ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

በበጀት ዓመቱ በሀዋሳ ለ26 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱ ተገለጸ​በ2019 በጀት ዓመት በሀዋሳ ከተማ ለ26 ሺህ 464 ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችል አቅጣጫ ተቀም...
05/08/2026

በበጀት ዓመቱ በሀዋሳ ለ26 ሺህ በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መታቀዱ ተገለጸ

​በ2019 በጀት ዓመት በሀዋሳ ከተማ ለ26 ሺህ 464 ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የሚያስችል አቅጣጫ ተቀምጦ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ።

​ይህ የተገለጸው የከተማዋ አስተዳደር የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ግምገማ መድረክ ባካሄደበት ወቅት የከተማው ሥራ አሠሪና ሠራተኛ መምሪያ ባቀረበው ሪፖርት ላይ ነው።

​የከተማው አስተዳደር በበጀት ዓመቱ የታቀደውን ሰፊ የሥራ ዕድል እውን ለማድረግ የእሴት ሰንሰለት አሠራርን፣ የሥራ አጥ ምዝገባና አጠቃቀምን እንዲሁም የቤተሰብ እና የማህበረሰብ የንግድ ማዕከላትን ታሳቢ ያደረጉ አሠራሮችን ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ በማድረግ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተጠቁሟል።

​ከዚህ በተጨማሪም የመንግሥት ተቋማትን እንደ ካፒታልና የድጋፍ አቅም አድርጎ በመጠቀም የተያዘውን የሥራ ዕድል ፈጠራ ዕቅድ እውን ማድረግ ሌላው ማስፈጸሚያ ስልት እንደሆነ ተገልጿል።

​ከዚሁ ጋር ተያይዞ የዲጂታል አጠቃቀምንና የዲጂታል ሥራ ዕድል ፈጠራን በማበረታታት የሥራ ገበያውን ማዘመን እና ወጣቶችን ከዓለም አቀፍ የሥራ ዕድሎች ጋር በማገናኘት በበጀት ዓመቱ ዕቅድ ውስጥ ቅድሚያ ከተሰጣቸው ተግባራት መካከል ይጠቀሳሉ።

​በተጨማሪም የሥራ ማዕከላትን ከተለመደው አሠራር በማላቀቅ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ ማድረግ፣ የወጣቶችን የሥራ ላይ ልምምድ ማሳደግ እና ውጤታማ የሀብት አጠቃቀም ላይ ትኩረት እንደሚደረግ ተመላክቷል።

​ለሥራ ዕድል ተጠቃሚዎችም በግልጽነትና በታማኝነት የልየታ ምዝገባ በማካሄድ ተገቢውን የሙያና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መስጠት ለአሠራሩ ስኬታማነት ሌላኛው አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ በልዩ ትኩረት ከሚሠራባቸው ተግባራት መካከል እንደሆነ ተጠቁሟል።

​አስተዳደሩ የተጣለበትን ዓላማ ለማሳካት የቦታ አቅርቦት፣ የፋይናንስና የብድር ድጋፍ እንዲሁም የገበያ ትስስርን በተቀናጀ መልኩ በማቅረብ የታቀደውን ዕቅድ ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ለማስገባት ዝግጁ መሆኑ ተብራርቷል።

05/08/2026

እንኳን ደስ አላችሁ /አለን

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ምዘና አንደኛ በመሆን ተሸላሚ ሆነ

የሞተር ብስክሌት የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) እና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል።

እንኳን ደስ አላችሁ /አለን የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ምዘና አንደኛ በመሆን ተሸላሚ ሆነየሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2018 ዓ....
05/08/2026

እንኳን ደስ አላችሁ /አለን

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም የአፈጻጸም ምዘና አንደኛ በመሆን ተሸላሚ ሆነ

የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በአመቱ ያከናወናቸው የተለያዩ የፓርቲ አቅም ግንባታ፣ የአባላት አቅም ማጎልበት፣ የህዝብ ተሳትፎ እና ሌሎች ተግባራት ባሳየው የላቀ አፈጻጸም በሲዳማ ክልል ከሚገኙ ሁሉም የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች መካከል አንደኛ ደረጃን በማስመዝገብ ተሸላሚ ሆኗል።

የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም አፈጻጸም ማጠቃለያ ኮንፈረንስ ባካሄደው መድረክ ላይ የሀዋሳ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የአመቱን የሥራ እቅዶች በውጤታማነት በማስፈጸሙ እና የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የአንደኝነት ዋንጫ፣ የሞተር ብስክሌት የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት) እና ሽልማት ተበርክቶለታል።

ይህ እውቅና የተገኘው በየደረጃው ያሉ የፓርቲ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች በቅንጅት በሰሩት ውጤታማ ሥራ ሲሆን፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ይህንን ስኬት መነሻ በማድረግ በቀጣይም የተሻለ አፈጻጸም በማስመዝገብ የፓርቲውን ዓላማና የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራትን በትጋት እንደሚያስቀጥል ገልጿል።

የክልሉን አመራር በአሰራር በመመልመል፣ በስልጠና በመደገፍ እና በማብቃት ጉድለት ያለበትን በማረም የህዝብን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት መሰረት ባደረገ መልኩ እንዲመራ የሚያስችል የፓርቲ ስርዓት ለመ...
05/08/2026

የክልሉን አመራር በአሰራር በመመልመል፣ በስልጠና በመደገፍ እና በማብቃት ጉድለት ያለበትን በማረም የህዝብን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት መሰረት ባደረገ መልኩ እንዲመራ የሚያስችል የፓርቲ ስርዓት ለመፍጠር በትኩረት እየተመራ ይገኛል።

የአንድ ክልል ወይም ሀገር ሁለንተናዊ እድገትና ብልፅግና የሚረጋገጠው የሕዝቡን አመኔታ ባተረፈ፣ በተጠያቂነት መርህ በሚመራና ለውጥ አምጪ በሆነ የአመራር ስርዓት ሲደገፍ ብቻ ነው። የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ይህንን እውነት በመረዳት፣ የአመራሩን አቅም የመገንባት፣ አሰራርን የማዘመንና የተጠያቂነት አሰራርን የመትከል ሥራዎችን በትኩረት እየመራ ይገኛል።

ባለፉት ዓመታት አመራሩን በግልጽ መስፈርት፣ ብቃትንና ህዝባዊ ወገንተኝነትን መሠረት ባደረገ አሰራር የመመልመልና የመመደብ ሥርዓት በመዘርጋት የአመራሩን የአፈጻጸም አቅምና የውሳኔ አሰጣጥ ለማሳደግ ስልጠናዎችን በመስጠት አመራሩን የማብቃት ሥራ በስፋት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ከአገልግሎት አሰጣጥና ከብልሹ አሰራሮች ጋር ተያይዘው የሚነሱ የሕዝብ ቅሬታዎችን በግምገማ በመለየት፣ ክፍተቶችን የማረምና በተጠያቂነት መርህ የመምራት አሰራር ተዘርግቷል በቀጣይነትም ተጠናክሮ ይቀጥላል።

ፓርቲያችን ብልፅግና ሕዝብን በንቅናቄ በመመራትና ከመንግሥት ጎን በባለቤትነት በማሰለፍ በበጀት ዓመቱ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ማሳካት የተቻለበት ነበር።ይህንን ስኬት አ...
05/08/2026

ፓርቲያችን ብልፅግና ሕዝብን በንቅናቄ በመመራትና ከመንግሥት ጎን በባለቤትነት በማሰለፍ በበጀት ዓመቱ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን ማሳካት የተቻለበት ነበር።

ይህንን ስኬት አጠናክሮ ለማስቀጠልና የቀጣይ መንገዶችን ለመቅረጽ፣ የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የ2018 በጀት ዓመት ክልላዊ የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ትውውቅ የውይይት መድረክ ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል።

ሕዝብና መንግሥት በተቀናጀ አቅም ሲንቀሳቀሱ የልማት አቅም እንደሚፈጥሩ በሲዳማ ክልል በተግባር የተረጋገጠበት ዓመት ነበር።

በሕዝብ ተሳትፎ የኢኮኖሚና የመሰረተ ልማት ማጎልበት የተቻለበት ፣የግብርና ምርታማነትና የሌማት ቱሩፋት የንቅናቄ ሥራ በምግብ ራስን ለመቻልና በገበያ ላይ የተረጋጋ ምርት ለማቅረብ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጨባጭ ውጤት አምጥተዋል።

ሕዝብን ያማከለ የውይይትና የምክክር መድረኮችን በመዘርጋት የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን ለማረም ሰፊ ሥራ ተሠርቷል። አደረጃጀቶችን በማጠናከር ወደ ልማትና የአገልግሎት ማሻሻያ ማዕከልነት በመቀየር የአመራሩንና የሕዝቡን ቅንጅት ማጠናከር ተችሏል።

ያለፈው በጀት ዓመት ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው፣ የታዩ ክፍተቶችን በውይይትና በግምገማ በማረም በ2019 በጀት ዓመት የሕዝባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሪ ዕቅዶችን ተግባራዊ ማድረግ የትኩረት ማዕከል ይሆናል።

Address

Awassa
0000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prosperity Party Hawassa City Branch Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share