South Ethiopia Region Finance Bureau

South Ethiopia Region Finance Bureau ይህ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ትክክለኛ የፌስቡክ ገጽ ነው!
(2)

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለ1447ኛው ዓ.ሂ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ‼️በዓሉ "የሰላም፣የደስታ፣ የፍቅር፣ የእርስበርስ መረዳዳት፣ የመደጋ...
27/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፣
እንኳን ለ1447ኛው ዓ.ሂ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ‼️

በዓሉ "የሰላም፣የደስታ፣ የፍቅር፣ የእርስበርስ መረዳዳት፣ የመደጋገፍ፣ ደግነት የሚበዛበት፣የአላህ በረከት የሚትረፈረፍበት በዓል ይሁንላችሁ"።

በዚህ ታላቅ በዓል ሕዝበ ሙስሊሙ ካለው ለሌለው በማካፈል የወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ የእርስበርስ መተሳሰብና የመደጋገፍ እሴቶችን አብዝቶ በተግባር የሚያሳይበት የፍቅርና የርህራሄ በዓል እንዲሆን የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ይመኛል!
ኢድ_ሙባረክ!

"ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል"- አቶ ተፈሪ አባተግንቦት 16/2018 ዓ.ምበምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡ...
24/05/2026

"ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል"- አቶ ተፈሪ አባተ

ግንቦት 16/2018 ዓ.ም

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ በተገኙበት በጎፋ ዞን ዑባ ደብረፀሐይ ወረዳ በልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።

አቶ ተፈሪ አባተ በዚህ ወቅት፥ ብልፅግና ፓርቲ ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት ለህዝቡ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል ብለዋል።

ለረጅም ጊዜያት ሕዝቡ ለሚያነሷቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስና በልማት ስራዎች ሂደት የሚታዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ብልፅግና ፓርቲ ለህዝቡ መሠረታዊ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየሰራ ይገኛል ያሉት አቶ ተፈሪ ፣ ህዝቡ ከፓርቲው ጎን በመቆም ሁለንተናዊ ድጋፉን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል።

የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በአፈፃፀም ሂደት የሚታዩ ጉድለቶችን በውይይት በመፍታት ህዝቡን ማዳመጥ ተገቢ መሆኑንም አስረድተዋል።

የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት እና የመሠረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጭርና የረጅም ጊዜ ዕቅዶች ተዘጋጅተው ሥራ ላይ እየዋሉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ቦሻ ቦምቤ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በማጠናከር ለዘመናት የቆዩ ውስብስብ ችግሮችንና የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በመጨረሻም የክልሉ እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በወረዳው ደጋ ቀበሌያትን ከወረዳው ማዕከል ጋር የሚያገናኘውን የመንገድ መሠረተ ልማት ስራ ጎብኝተዋል።

በወረዳው እየተከናወኑ ያሉ የመንገድ ስራ በአካባቢው የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

23/05/2026

ውጤታማ የውሃ ፕሮጀክቶችና የፋይናንስ አፈጻጸም ስኬቶቻችን!!

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሕዝብ ጥያቄ ምላሽና ውጤታማ የበጀት አፈጻጸምን ያረጋገጡ የንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ስኬት መመዝገቡ ተገለጸ።ሶዶ፣ ​ግንቦት 14 _2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክ...
22/05/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሕዝብ ጥያቄ ምላሽና ውጤታማ የበጀት አፈጻጸምን ያረጋገጡ የንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ስኬት መመዝገቡ ተገለጸ።

ሶዶ፣ ​ግንቦት 14 _2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የህዝቡን መሰረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በሰጠው ከፍተኛ ትኩረት፣ በክልሉ ስር በሚገኙ ሁሉም ዞኖች ሲገነቡ የቆዩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ መሆናቸው ተመላክቷል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ባመቻቸው ቀልጣፋ የበጀት ድጋፍና ቁጥጥር እንዲሁም የክልሉ ውሃ ቢሮ ባደረገው ቀጥተኛ የቴክኒክ ክትትልና አፈጻጸም የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብና ጥራት የመጨረስ አዲስ የስራ ባህል በተግባር ተረጋግጧል።

ይህም የመንግስትን የፕሮጀክት የመፈጸም አቅም ማደግ በግልፅ የሚያሳይ ስኬት ሆኖ ተመዝግቧል።

​ይህ ሰፊ የልማት ንቅናቄ የህዝቡን የዓመታት የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ፍላጎት በዘላቂነት ከመመለሱም በላይ፣ በክልሉ የሚስተዋለውን ፍትሀዊ የልማት ተደራሽነት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው።

እያንዳንዱ ዞንና ማህበረሰብ ከልማቱ እኩል ተጠቃሚ እንዲሆን የተደረው ጥረት፣ በክልሉ አስተማማኝና ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል እንዲሰፍን የበኩሉን አስተዋፅኦ አበርክቷል።

​ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው በጀትና በተቀመጠ የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለህዝብ አገልግሎት መብቃታቸው፣ የፋይናንስ ዲሲፕሊንንና የበጀት አጠቃቀም ውጤታማነት ደረጃን ከፍ ያደረገ ነው።

በቀጣይም የሚመደብ በጀት የህዝብና የመንግስት ሀብት ለታለመለት የልማት ግብ ብቻ እንዲውል የሚደረገውን ቁጥጥርና ድጋፍ ይበልጥ አጠናክሮ ለመቀጠል ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ ስኬት መሆኑ ተገልጿል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት  3 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ጋር ስምምነት መደረጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 5...
16/05/2026

ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ጋር ስምምነት መደረጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ

ግንቦት 08/2018 ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል 536 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ መፅደቃቸውም ተገልጿል

የፌደራል፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈጻሚዎች የጋራ ምክክር መድረክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በምክክር መድረኩ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ክላስተር አስተባባሪ የክልሉ ፋይናንስ በኃላፊና አቶ ተፈሪ አባተ እንደገለፁት በክልሉ 536 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በኢንቨስትመንት ቦርድ መፅደቃቸውን ገልፀዋል።

መንግስት የውጭ ጫናና የኑሮ ውድነት ፈተናዎችን በመቋቋም የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማረጋገጥ ከግል ኢንቨስተሮች ጋር በመቀናጀት በግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ አገልግሎትና ማዕድን ዘርፎች እየሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

ኢንቨስትመንት የውስጥ ገቢን ለማሳደግ፣ የስራ ዕድል ለመፍጠር እና የእውቀት ሽግግርን ለማሳለጥ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት አቶ ተፈሪ፣ ኮሚሽኑ የክልሉን እምቅ አቅም በማስተዋወቅ ረገድ የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 3 ነጥብ 52 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ ቀጥተኛ ኢንቨስተሮች መሳብ መቻሉን ገልጸዋል።

በ2026 በተካሄደው “ኢንቨስት ኢትዮጵያ” ፎረም 13 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር ያስመዘገቡ ኢንቨስተሮች ጋር ስምምነት መደረጉን ገልፀው ይህም ኢትዮጵያ አስተማማኝና ተወዳዳሪ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን በተግባር ያሳየ መሆኑን አመላክተዋል።

በደቡብ፣ አፋርና ሱማሌ ክልሎች 7 ነጥብ 47 ቢሊዮን ዶላር በመደብ 8.4 ጊጋ ዋት የሚያመነጩ ግዙፍ የንፋስና ጸሀይ ኃይል ፕሮጀክት እንደሚገነባ ገልፀዋል።

ስኬቱ የክልልና የፌድራል ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመስራት ያመጡት በመሆኑ ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አበክረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ አጸደ አይዛ እንደገለጹት፣ ክልሉ እንደ አዲስ ከተመሰረተ ወዲህ 536 የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸው በክልሉ በአጠቃላይ 82 ነጥብ 21 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ 1826 ፕሮጀክቶች ይገኛሉ ብለዋል።

እንደ ኮሚሽነሯ ገለፃ፣ እነዚህ ፕሮጀክቶች የክልሉን ገቢ ከማሳደግ ባሻገር ለብዙ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ኮሚሽኑ ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር በማጣጣም በርካታ ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ማከናወኑን የገለጹት ወ/ሮ አጸደ፣ በዘርፉ ያጋጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

የክልሉን የኢንቨስትመንት ፖቴንሻል በማስተዋወቅና አዲስ ኢንቨስትመንት ለመሳብ አቅም የሚገነባ ሀገራዊ የምክክር መድረክ በክልሉእንዲካሄድ ላደረገው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ወ/ሮ ምስጋና አቀርበዋል።

ከተሞችን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለጸግንቦት 08/2018 ዓ.ም ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ውብ የማድረግ ሀገራዊ ራዕይ እ...
16/05/2026

ከተሞችን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ገለጸ

ግንቦት 08/2018 ዓ.ም

ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹና ውብ የማድረግ ሀገራዊ ራዕይ እውን ለማድረግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ቢሮው አስታውቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት
ቢሮ የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት በጥልቀት ተገምግሟል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ፥ በክልል ተቋማት የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ላይ የ"በጀት ሰሚ" ፕሮግራም መድረክ እያካሄደ መሆኑ ይታወቃል።

በመድረኩ የቢሮው የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት የተገመገመ ሲሆን፣ በቀጣዩ ዓመት እንዲተገበሩ የታቀዱ የፊዚካል እና የፋይናንሺያል ሥራዎች መሪ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ምክክር ተደርጎበታል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ምክትልና የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምህረቱ አሰፋ፥ የበጀት ሰሚ ፕሮግራም በዋናነት የመንግስት ሀብት በቁጠባ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት ስሜት ለታለመለት የልማት ግብ መዋሉን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።

በክልሉ የከተሞችን ዕድገት ለማፋጠን የተጀመሩ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋል ያሉት አቶ ምህረቱ፥ በየደረጃው የሚታይ ውጤት ለማስመዝገብ በቅንጅት መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመድረኩ በዘርፉ ባለፈው በጀት ዓመት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማስቀጠልና የታዩ ውስንነቶችን በማረም፣ በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን የልማት ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ታሳቢ ያደረገ ውጤታማ ስራ እንዲያከናውኑ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመድረኩ የክልሉ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴን ጨምሮ የቢሮው ማኔጅመንት አካላት ተገኝተዋል።

ብልፅግና ፓርቲ የህዝቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል:- አቶ ተፈሪ አባተግንቦት 07/2018 ዓ.ምበጎፋ ዞን በኦይዳ ወረዳ ከተለያዩ የህብረተሰብ...
15/05/2026

ብልፅግና ፓርቲ የህዝቡን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል:- አቶ ተፈሪ አባተ

ግንቦት 07/2018 ዓ.ም

በጎፋ ዞን በኦይዳ ወረዳ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በልማትና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በብልፅግና ፓርቲ መሪነት የተከናወኑ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ዙሪያ እና በቀጣይ በሚሰሩ ስራዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ከፍተኛ የክልል እና የዞን አመራሮች በተገኙበት መድረኩ የተካሄደው።

በምክትል ር/መስተዳድር ማዕረግ የወላይታ ሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ በመድረኩ እንደተናገሩት፥ ብልፅግና ፓርቲ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ ይገኛል ብለዋል።

ብልፅግና ፓርቲ ትናንት ላይ ስንከባለሉ የቆዩ የመሠረተ ልማት ጥያቄዎችን በህዝብ እና በመንግስት ትብብር በመስራት ረገድ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ፓርቲ መሆኑን አቶ ተፈሪ ጠቁመዋል።

በመደመር መንግስት አማካኝነት ባለፉት ዓመታት ከፍተኛ ልማት መሠራቱን አንስተው አሁንም ቢሆን ህዝብ የሚያነሳቸው ትክክለኛ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ኃላፊነትና ተጠያቂነት ባለው መንገድ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ ፍትሐዊና ተዓማኒነት ያለው፣ በህዝቡ ዘንድ ቅቡልነት ባለው መንገድ እና በአሸናፊነት እንዲጠናቀቅ በየደረጃው ያለው አመራርና አባል በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበትም ተናግረዋል።

በለውጥ መንግስት እሳቤዎች መሪነት ባለፉት ዓመታት የተገኙ ድሎችን ተከታታይነት ባለው መንገድ በህዝብ ግንኙነት ስራዎች ማስተዋወቅና ለህዝብ ግልፅነት መፍጠር እንደሚያስፈልግ የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዳግማዊ አየለ (ኢንጂነር) ገልጸዋል።

የህብረተሰቡን መሰረታዊ ጥያቄ በማዳመጥና ከልብ ተረድቶ አጥጋቢ ምላሽ መስጠት እንዲሁም በፍጥነት የማይመለሱ ጊዜ የሚሹ ጉዳዮችን ከህዝብ ጋር ተነጋግሮ ተግባቦት መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልፀዋል።

ከዚህ አንፃር በዞን ብሎም በወይዳ ወረዳ ትናንት ላይ ከህዝቡ የተነሱ ጥያቄዎችን በማዳመጥ እና ምላሽ ለመስጠት መንግስት በወሰደው ቁርጠኛ አቋም ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

የኦይዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታዘቤ ጋትሶ በበኩላቸው፥ በበጀት ዓመቱ መሠረታዊ የሚባሉ የወረዳውን ጥያቄዎች የዞኑ አስተዳደር እና የክልሉ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ምላሽ እንዲያገኝ አስችሏል ብለዋል።

በመድረኩ የተሳተፉ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው በብልፅግና ፓርቲ ከህዝቡ ጋር በመነጋገር የዘመናት ጥያቄ የሆኑ ጉዳዮችን እየፈታ እንደማገኝ ገልፀዋል።

አክለውም በቀጣይም በሚሰሩ ተግባራት ዙሪያ ህዝቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች መሠረት በማድረግ ደረጃ በደረጃ እንደሚፈታ ሙሉ እምነት አሳድረዋል።

በመድረኩ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች፣ የወይዳ ልዩ ምርጫ ክልልና የፓርላማ ዕጩዎች፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ከተለያዩ ማህበራዊ መሠረት የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ተገመገመ ግንቦት 07/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ምክትልና የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ...
15/05/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ተገመገመ

ግንቦት 07/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ምክትልና የመንግስት ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ምህረቱ አሰፋ በተገኙበት የክልሉ ጤና ቢሮ የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት በጥልቀት ተገምግሟል።

በክልል ተቋማት የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ላይ የ"በጀት ሰሚ" ፕሮግራም መድረክ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።

በመድረኩ የቢሮው የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት የተገመገመ ሲሆን፣ በቀጣዩ ዓመት እንዲተገበሩ የታቀዱ የፊዚካል እና የፋይናንሺያል ሥራዎች መሪ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ምክክር ተደርጎበታል።

​ይህ የበጀት ሰሚ ፕሮግራም በዋናነት የመንግስት ሀብት በቁጠባ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት ስሜት ለታለመለት የልማት ግብ መዋሉን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በመድረኩ እንደ ክልል በጤናው ዘርፍ ባለፈው በጀት ዓመት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማስቀጠልና የታዩ ውስንነቶችን በማረም፣ በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን የልማት ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ታሳቢ ያደረገ ውጤታማ ስራ እንዲያከናውኑ አቅጣጫ ተቀምጧል።

የቢሮው የበጀት ሰሚ ኮሚቴዎችም የቢሮውን የፋይናንሽያል ዕቅድ ከታቀዱት ፊዚካል ስራዎች ጋር የተመጣጠነ መሆኑን በማረጋገጥ፣ በጀት ለውጤታማ ተግባራት ብቻ እንዲውል ጥብቅ ቁጥጥርና ድጋፍ እንደሚደረግ አስገንዝበዋል።

"በክልሉ በውሃና ኢነርጂ ዘርፎች የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል"- አቶ ተፈሪ አባተግንቦት 06/2018 ዓ.ምበምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡ...
14/05/2026

"በክልሉ በውሃና ኢነርጂ ዘርፎች የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል"- አቶ ተፈሪ አባተ

ግንቦት 06/2018 ዓ.ም

በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ በተገኙበት የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ተገምግሟል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ፥ በክልል ተቋማት የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ላይ እያካሄደ ያለው የ"በጀት ሰሚ" ፕሮግራም መድረክ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በመድረኩም የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የበጀት አፈጻጸም ሪፖርት የተገመገመ ሲሆን፣ በቀጣዩ በጀት ዓመት እንዲተገበሩ የታቀዱ የፊዚካል እና የፋይናንሺያል ሥራዎች መሪ ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ምክክር ተደርጎበታል።

መድረኩን የመሩት በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የሶዶ ክላስተር አስተባባሪና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈሪ አባተ፥ ቢሮው ክልሉ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ሁለት ዓመታት የክልሉን ሕዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ላለው እንቅስቃሴ አመስግነዋል።

የተቋሙ ራዕይ እውን እንዲሆንና ተልዕኮው እንዲሳካ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

በክልሉ በውሃና ኢነርጂ ዘርፎች የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ያሉት አቶ ተፈሪ፥ የሚመደበውን ውስን የመንግስት ሃብት ለታለመለት ዓላማ በማዋል የሕዝብን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የመንግስት ሀብት በቁጠባ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት ስሜት ለታለመለት የልማት ግብ ማዋል እንደሚገባ ተገለጸ ግንቦት 06/2018 ዓ.ምየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ፥ በክልል ተቋማት የ...
14/05/2026

የመንግስት ሀብት በቁጠባ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት ስሜት ለታለመለት የልማት ግብ ማዋል እንደሚገባ ተገለጸ

ግንቦት 06/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ፥ በክልል ተቋማት የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት ላይ እያካሄደ ባለው የ"በጀት ሰሚ" መድረክ፣ ከአምስት ተቋማት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በዚህም የክልሉ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን፤ የክልሉ ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን፤ የጂንካ፣ የዲላ እንዲሁም የቦዲቲ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የ2019 ዓ.ም የበጀት ዕቅድ ዝግጅት በጥልቀት ተገምግሟል።

የበጀት ሰሚ ፕሮግራም በዋናነት የመንግስት ሀብት በቁጠባ፣ በግልጽነትና በተጠያቂነት ስሜት ለታለመለት የልማት ግብ መዋሉን ለማረጋገጥ ያለመ ነው።

Address

3F7P+ 533
Awassa
104

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Region Finance Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share