ANRS Occupational Competence Assessment and Certification Authority

ANRS Occupational Competence Assessment and Certification Authority Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ANRS Occupational Competence Assessment and Certification Authority, Government Organization, Ethiopia, Bahir Dar, Bahir Dar.

ተልዕኮ፡-
በመደበኛ፣ መደበኛ ባልሆኑ የሥልጠና ፕሮግራሞች እና በኢ-መደበኛ መንገድ በዝቅተኛና መካከለኛ ደረጃ ሙያው የሚጠይቀውን ዕውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ላካበቱ ባለሙያዎች በአገር አቀፍ የሙያ ደረጃዎች ላይ የተመሠረተ የሙያ ብቃት ምዘና እና ብቁ ለሆኑት የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት በመስጠት ብቃቱ የተረጋገጠ ባለሙያ ለገበያው እንዲቀርብ በማድረግ የኢንዱስትሪውን ምርትና ምርታማነት ማሳደግ፣

ራዕይ፡-

በ2022 ብቃቱ የተረጋገጠና በገበያ ተወዳዳሪ የሆነ ባለሙያ በኢንዱስትሪው ተገንብቶ ማየት፣

እሴቶች፡-

· ቅንነት፣

· ታማኝነት፣

· በቡድን የመስራት ባህል፣

· አዳዲስ እውቀቶችንና ክህሎቶችን መማር፣

· ኪራይ ሰብሳቢነትን መታገል፣

· ጥራትና ተወዳዳሪነት፣

· በሥነምግባር መረሆዎች መመራት፣

· በብቃት ማመን፣

በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከ3 መቶ በላይ ለሚሆኑ  ለአዲስ እና ለነባር ምዘና ማዕከላት   እውቅናና  ፈቃድ እድሳት  መሰጠቱ ተገለጸ========================ባህርዳር፣ ነ...
20/08/2026

በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከ3 መቶ በላይ ለሚሆኑ ለአዲስ እና ለነባር ምዘና ማዕከላት እውቅናና ፈቃድ እድሳት መሰጠቱ ተገለጸ
========================
ባህርዳር፣ ነሃሴ 15 2018 ዓ.ም (የሙ/ብ/ም/ማ/ባ) በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከ3 መቶ በላይ ለሚሆኑ አዲስ የምዘና ማዕከላት ፍቃድ እና ለነባር ምዘና ማዕከላት አዉቅና አድሳት መሰጠቱን የአብክመ የ ሙያ ብቃትና ምዘናና ማረጋገጫ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡

የባለስልጣኑ የሙያ ደረጃ ምደባ፣ ጥናትና አውቅና አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ባያሌው መነሻ እንደገለጹት አምስቱን ካላስተር ማዕከላትን ጨምሮ ለ150 የምዘና ማዕከላት አዲስ አውቅና ለመስጠት ታቅዶ ከመካከለኛና ከፍተኛ እንዱስትሪዎች 25 እና ከጥቃቅንና አንስተኛ ኢንተርፕራይዞች 131 በድምሩ ለ156 ኢንዲስትሪዎች አዲስ የምዘና ፍቃድ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል ፡፡

ለ36 ነባር ምዘና ማዕከላት በ70 ሙያወች ተጨማሪ የምዘና ማዕከላት ፈቀድ መሰጠቱንም ተናግረዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ለ243 ለነባር ምዘና ማዕከላት እዉቅና ለማደስ ታቅዶ አስከ በጀት ዓመቱ ማጠቃልያ ድረስ በተደረገዉ እንቅስቃሴ የቅዱን 170 /70 በመቶ ባቻ ማከናዎን እንደተቻለም አቶ ባያሌዉ ተናግረዋል፡፡

የነባር ምዘና ማዕከላት እዉቅና ማደስ አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆን በክልላችን በአንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ችግር ምክንያት በየደረጃዉ የሚገኙ ባለድርሻ አካለት እና ባለሙያወች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሶ ለመስራት አለመቻል መሆኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ እውቅና ያገኙ ምዘና ማዕከላትም አንዳንድ ሙያዎች ላይ ለምዘና የሚወጣው ወጭ ተመዛኞች ከሚከፍሉት የምዘና ክፍያ አዋጭ አይደለም በሚሉና በሌሎች ተያያዥ ችግሮች ወደ ምዘናው አለመግባት በበጀት አመቱ ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ አቶ ባያለው ተናግረዋል፡፡

የሙያ ብቃት ምዘና መስጫ ማዕከላትና መዛኞችን እና ተያያዥነት ያለቸውን ጉዳዮች በውጤታመነት ለማከናወን በአንድ ተቋም ብቻ ሊሳካ ስለማይችል የአጋር አካላት ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይ በጀት ዓመት ሁሉም አካል የበኩሉን ሚና ሊወጣ ይገባል ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

20/08/2026

የግጭትን አዙሪት የሚሽር የሠላም ቀንዲል …ምክክር

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እነሆ ጨለማ ተገፍቷል፤ ጉሙ ተበትኗል። የተሻለች፣ የተረጋጋችና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማውረስ፣ በዚህ ትውልድ እጅ የፀና የተስፋ ቀንዲል ተለኩሷል፤ ስሙም ምክክር ነው።

ከግጭት የተላቀቀች እና ሠላሟን ያፀናች ኢትዮጵያን የሚያወርስ ድንቅ መድረክ መካሄድ ከጀመረ እነሆ አንድ ወር አልፎታታል።

የኢትዮጵያ ልጆች ለዘላቂ ሠላም፣ ልማት እና ዲሞክራሲ መረጋገጥ በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠዋል።

የአሁኑ ትውልድ “ሀገሬ የግጭት ትውስታ የምታስወርስ ሳትሆን፣ ሰላምን፣ ዴሞክራሲን፣ ፍትሕን፣ መተማመንን፣ ልማትን እና ብልጽግናን ለነገ ልጆቿ ማውርስ አለባት” ብሎ ታሪካዊው ውሳኔውን በምክክሩ እያስተላለፈው ነው።

የኢትዮጵያ ልጆች በመከባበር እና በመደማመጥ በቁርጠኝነት የሚያደርጉት ውይይት ነገን ፍሬያማ እንደሚያደርግ ትልቅ ተስፋን ተጥሎበታል።

በውይይቱ ምክንያት ዘላቂ ሰላም ሲሰፍን በግጭት አዙሪት የሚባክነው ጊዜ እና ገንዘብ ወደ ማህበራዊ ልማት እንዲሁም ምጣኔ ሀብታዊ እድገት ይውላል።

በዚህም ሀገሪቱ ወደ ዕድገት እና ብልፅግና ፈጥና ትደርሳለች።

ለዚህም ነው ምክክሩ የኢትዮጵያን ከፍታ እና ብልፅግናዋን ለሚሹ ሁሉ ትልቅ ተስፋን በማሰነቅ ዕድገቷን ለማይሹ የሀዘን ካባን ያለበሳቸው።

ባዕዳ እና ባንዳ ግንባር ፈጥረው የኢትዮጵያን ከፍታ አምርረው ቢቃወሙት ክፉ ምኞታቸው ከሽፎ፣ እነሆ ኢትዮጵያ ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና ጎዳና የሚያደርሳትን ጉዞዋን ቀጥላለች።

የሀገራዊ ምክክር ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ሥላሴ እንደተናገሩት÷ በየትም ዓለም የሚደረጉ ሀገራዊ ምክክሮች መቶ በመቶ በሁሉ ጉዳይ ላይ ይስማማሉ አይባልም።

ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያ እያካሄደችው ያለው ምክክር በአብዛኛው ጉዳዮች ስምምነት ላይ የተደረሰበትና ለንግግርና ውይይት በር የከፈተ ነው ብለዋል። ይህም ለነገ ፅኑ መሰረት የሚጥል ነው፡፡

ይህ ጉዞ መዳረሻው ዘላቂ ሰላም፣ ጠንካራ ማኀበራዊ መስተጋብር እና ሀገራዊ መግባባት ነው። ችግሮች መፍትሄያቸው በምክክር ብቻ መሆኑን በማመን ልዩነቶችን ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ ማምጣታቸው የሀገርን ተስፋ አለምልሞታል።

ሀገራዊ ምክክሩ የትውልድን መፃኢ ዕድል የሚወስን ነው። ለዘመናት የተጠራቀመ አለመግባባቶችን እና ግጭትን የኢትዮጵያዊያን አንድነትና አብሮነት የሚያፀና ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።

በሠራዊት ሸሎ

20/08/2026
20/08/2026
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማረጋገጥ ስራ ከፊታችን ያለ ዐቢይ ተግባር በመሆኑ፣ ይህንን በመገንዘብ ሁሌም ዝግጁ መሆን ይጠበቅብናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
20/08/2026

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማረጋገጥ ስራ ከፊታችን ያለ ዐቢይ ተግባር በመሆኑ፣ ይህንን በመገንዘብ ሁሌም ዝግጁ መሆን ይጠበቅብናል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

የ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ደብተር ድጋፍ ያደረገው ተቋም የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" በሚል  መሪ ሀሳብ የትምህርት ቁሳቁስ የማሠባሠቢያ  መርሐ ግብር ...
19/08/2026

የ5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ደብተር ድጋፍ ያደረገው ተቋም
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ "አንድ ደርዘን ደብተር ለአንድ ተማሪ" በሚል መሪ ሀሳብ የትምህርት ቁሳቁስ የማሠባሠቢያ መርሐ ግብር እያካሄደ ነው።
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ኀላፊ መኳንንት አደመ በኢኮኖሚ ዝቅተኛ የኾኑ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይኾኑ እና የሕጻናትን ችግር ለመፍታት የሁሉም የባለድርሻ አካላት ድጋፍ የሚያስፈልግ በመኾኑ መርሐ ግብሩ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።
በክልሉ ዩኒፎርም ሳይለብሱ፣ ደብተር እና እስክርቢቶ ሳይዙ ብሎም ወደ ትምህርት ቤት ለመሄድ አፍረው ከጓደኞቻቸው ተለይተው የሚመለሱ ልጆች በርካታ ናቸው ብለዋል።
ዩኒፎርም እና ደብተር መግዛት የማይችሉ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ፈተና ኾኖባቸዋል። ይህ መርሐግብርም ችግር ያለባቸውን ልጆች ችግራቸውን የሚፈታ ነው ብለዋል።
ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት ገበታ ለማስገባት የመጀመሪያው የሚያስፈልገው የትምህርት ቁሳቁስ ነው። ይህም አንዱ የትምህርትን ጥራት ለማረጋገጥ የመጀመሪያው የትምህርት ቁሳቁስ ማሟላት ነው።
በወቅታዊ ችግሩ ምክንያት በርካታ ሕጻናት ከትምህርት ገበታ ውጭ እና በኢኮኖሚ እጥረት ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ የሚቸገር ማኅበረሰብ ብዙ መኾኑን ነው የተናገሩት።
የክልሉ ማኅበረሰብ ባለሀብቶች፣ ነጋዴዎች፣ መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች፣ መንግሥታዊ ተቋማት፣ ባንኮች፣ ግለሰቦች እና ሌሎችም ይህንን በጎ አድራጎት ተግባር በመደገፍ የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
መርሐግብሩ በክልል ብቻ የሚቆም ሳይኾን እስከ ቀበሌ ድርስ ተደራሽ ይደረጋል ያሉት ምክትል ቢሮ ኀላፊው ይህም በ2019 የትምህርት ዘመን ወደ ትምህርት ቤት ለሚመለሱ 7 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይኾኑ ሁሉም ለድጋፉ እጁን እንዲዘረጋ አሳስበዋል። "ልጆቻችን እኛ እያለን ከትምህርት ገበታ ውጭ መኾን የለባቸውም" ማለት እንደሚገባም ነው የገለጹት።
የዓባይ ህትመት እና ወረቀት ፖኬጂንግ ፋብሪካ ምክትል ሥራ አሥኪያጅ ነጋ ይሁኔ ታዳጊዎች በትምህርት ቁሳቁስ እጥረት ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይኾኑ በየ ዓመቱ 5 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመት 60 ሺህ ደብተር ድጋፍ ማድረጉንም ገልጸዋል።
ድጋፉ የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመገንባት እንደሚያግዝም ነው የገለጹት። ድጋፋቸው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
የአማራ ክልል የመምህራን ማኅበር ምክትል ኘሬዝዳንት እናውጋው ደርሰህ ማኅበሩ 24 ደርዘን ደብተር በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል። በተዘጋጀው መርሐግብር ብቻም ሳይኾን ሁልጊዜም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እያደርጉ መኾኑንም አንስተዋል። ድጋፉ የሕጻናትን ሥነ ልቦና ይገነባል፤ የሕሊና እርካታ የሚሰጥ በጎ ተግባርም ነው ብለዋል።
መርሐግብሩ ከነሐሴ 13/2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥልም ተገልጿል። See

19/08/2026

ከ80 በመቶ በላይ ያመጡ ተማሪዎችን በአዳሪ ትምህርት ቤቶች የመመዝገብ ስራ ተጀመረ
+++++++++++

በ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከ80 በመቶና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎችን በአዳሪ ትምህርት ቤቶች ለመቀበል ምዝገባ መጀመሩን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የአዳሪ ትምህርት ቤቶች የተማሪ ምዝገባን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የሚኒስትሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ክንድዬ ገብረሕይወት (ፕ/ር)፤ በ8ኛ ክፍል ከ80 በመቶና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎችን በማወዳደር ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን፤ ከገጠራማ እና ከአርብቶ አደር አካባቢዎች ለሚመጡ ተማሪዎች ልዩ ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ምዝገባው በሚኒስቴሩ በይነ-መረብ በኩል ያለምንም ክፍያ እንደሚከናወን ጠቁመው፤ ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ውጤታቸውን በፒዲኤፍ (PDF) ስካን በማድረግና የፈተና መለያ (ID) ቁጥራቸውን በመጠቀም ባሉበት ሆነው በመመዝገብ ወደ አዲስ አበባ ሳይመጡ ባሉበት ክልል ሆነው በበይነ-መረብ ፈተናውን ይወስዳሉ ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአምስት አካባቢዎች (ጂጂጋ፣ ጋምቤላ፣ ቦንጋ፣ ቡኢ እና ወሊሶ) አገልግሎት እየሰጡ ካሉት አራት አዳዲስ ትምህርት ቤቶች ማለትም በባህር ዳር፣ አርባ ምንጭ፣ ድሬደዋና አሶሳ መቀበል እንደሚጀምሩ ጠቁመዋል፡፡

በሁሉም ክልሎች የተገነቡ 13 የፌደራል አዳሪ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት ሲጀምሩ፣ እያንዳንዱ አዳሪ ትምህርት ቤት እስከ 1,000 ተማሪዎችን በመቀበል በየዓመቱ 13 ሺህ አዳዲስ ተማሪዎችን የማስተናገድ አቅም ይኖራቸዋል ሲሉ ተናግረዋል።

ለትምህርት ቤቶቹ የሚያስፈልጉ ዳይሬክተሮችና መምህራንም በፌደራል ደረጃ በልዩ ሁኔታ ተመርጠው እየተቀጠሩ ይገኛሉ ሲሉ ገልጸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፕሮግራሙ ከፍተኛ አገራዊ ሀብት እየፈሰሰበት የሚገኝ በመሆኑ፣ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ብቁ ተማሪዎች የዚህ እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ፕሮግራሞች ጥራት ማሻሻል መሪ ስራ አስፈፃሚ ዮሐንስ ኦጋሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች በተግባር የተደገፈ ትምህርት በመስጠት በፈጣራ የጎለበተ ዜጋ እያፈሩ ነው፡፡

"አዳሪ ትምህርት ቤት ላይ የሚማሩ ልጆች መጀመሪያውንም በጣም ጎበዝ፣ ፈጣን የመማር ችሎታና ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ልጆች የሚማሩ በመሆኑ በቀጣይ እነዚህ ልጆች የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው" ብለዋል፡፡

ባለፈው ዓመት በአምስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች በእያንዳንዱ 250 ተማሪዎች፣ በአጠቃላይ 1,250 ተማሪዎች የ9ኛ ክፍል ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።

MIE

#አዳሪትምህረትቤቶች #ምዝገባመጀመር #ትምህርት

19/08/2026

የሀገራዊ ምክክር ም/ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ሥላሴ የሀገራዊ ምክክሩን አሁናዊ ሁኔታ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

👉 ከስምንቱ ቡድን የተወጣጡ አጠናቃሪ ተሳታፊዎች ስራቸውን ሲሰሩ ቆይተዋል።

👉 ይሄ ስራ የስምንቱንም ቡድን አጀንዳ አጠናቅሮ ለማቅረብ ጥንቃቄ የሚፈልግ ስራ እንደመሆኑ ጊዜ ፈጅቷል።

👉 አጠናቃሪዎቹ እስከ ትናንት ምሽት ድረስ ባደረጉት ርብርብ የስምንቱንም ቡድኖች ምክረ ሐሳብ ያካተተ አንድ ወጥ ሰነድ ማዘጋጀት ችለዋል።

👉 ይህ ሂደት እያንዳንዱ ቡድን በሚቀርበው ሰነድ ላይ የመጨረሻ ግብዓቱን ማስገባት፣ አስተያየቱን መስጠት እንዲችል የተዘጋጀ ሂደት ነው።

👉 በተዘጋጀው አንድ ወጥ ሰነድ ላይ ውይይት ለማድረግ በዛሬው ዕለት ለየቡድኖቹ የማቅረብ ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡

👉 ዛሬ ስምንቱ ቡድኖች የስምንቱንም ቡድኖች ምክረ ሃሳቦች በመስማት ግብዓት ይሰጣሉ።

👉 ማምሻቸውን እነዚህ 120ዎቹ አጠናቃሪ ቡድኖች የመጨረሻዎቹን ግብዓቶች በማካተት የመጨረሻውን ሰነድ አጠናቅቀው ያዘጋጃሉ።

👉 በዚህ መሰረት በነገው ዕለት ይሄ የተጠናቀረው የመጨረሻው ሰነድ ለአራት ሺህ ተሳታፊ ይቀርባል።

👉 መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የተዛቡ መረጃዎችን በመስማት እንዳይወዛገብ ትክክለኛ የሆኑ ሚዲያዎችን እና የኮሚሽኑን መግለጫዎች እንዲከታተሉ አሳስበዋል።

በዮናስ ጌትነት

Address

Ethiopia, Bahir Dar
Bahir Dar
6000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Occupational Competence Assessment and Certification Authority posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ANRS Occupational Competence Assessment and Certification Authority:

Shortcuts

Share