25/11/2025
የምዕራብ በለሳ ወረዳ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ አካሄደ።
=========================
ህዳር 16 / 2018 ዓ.ም
ዕቅድ ትውውቁን አስመልክቶም የፍርድ ቤቱ ፕሬዜዳንት አቶ ሀብተማርያም ወ/ዮሀንስ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉ በኋላ በዕቅድ ባለሙያው በአቶ አማረ ብርሃኑ የ2018 ዓ/ም የተቋሙ ዓመታዊ እቅድ በስላይድ ተደግፎ በዝርዝር ቀርቧል።
በቀረበው ዕቅድ ዙሪያ ላይ የተቋሙ ዳኞች እና ባለሙያዎች የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም በ2017 በጀት ዓመት ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት እንዲሁም የፍርድ ቤቱን ነፃነትና ገለልተኝነት በማረጋገጥ በያዝነው በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ ስራ በመስራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሀብተማርያም አሳስበዋል።
በመጨረሻም በውይይቱ ዙሪያ አስተያየት ከተሰጠ በኋላ የዳቦ ቆረሳና የሻይ ቡና ፕሮግራም በማድረግ ውይይቱ ተጠናቋል።
የምዕ/ወ/ፍርድ ቤት ህዝብ ግንኙነት