West Bellessa Woreda Court

West Bellessa Woreda Court Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from West Bellessa Woreda Court, Public & Government Service, Bahir Dar.

የምዕራብ በለሳ ወረዳ  ፍርድ ቤት  የ2018  በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ አካሄደ።=========================ህዳር 16 / 2018 ዓ.ምዕቅድ ትውውቁን አስመልክቶም የፍርድ ቤቱ ...
25/11/2025

የምዕራብ በለሳ ወረዳ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ አካሄደ።
=========================
ህዳር 16 / 2018 ዓ.ም
ዕቅድ ትውውቁን አስመልክቶም የፍርድ ቤቱ ፕሬዜዳንት አቶ ሀብተማርያም ወ/ዮሀንስ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉ በኋላ በዕቅድ ባለሙያው በአቶ አማረ ብርሃኑ የ2018 ዓ/ም የተቋሙ ዓመታዊ እቅድ በስላይድ ተደግፎ በዝርዝር ቀርቧል።
በቀረበው ዕቅድ ዙሪያ ላይ የተቋሙ ዳኞች እና ባለሙያዎች የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም በ2017 በጀት ዓመት ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት እንዲሁም የፍርድ ቤቱን ነፃነትና ገለልተኝነት በማረጋገጥ በያዝነው በ2018 በጀት ዓመት የተሻለ ስራ በመስራት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሀብተማርያም አሳስበዋል።
በመጨረሻም በውይይቱ ዙሪያ አስተያየት ከተሰጠ በኋላ የዳቦ ቆረሳና የሻይ ቡና ፕሮግራም በማድረግ ውይይቱ ተጠናቋል።
የምዕ/ወ/ፍርድ ቤት ህዝብ ግንኙነት

ፍየል ሠርቆ የወሠደው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ፡፡ ከሳሽ፡-ዐ/ህግተከሳሽ፡-አቶ ጌታሁን ጋሻው ዕድሜ 22 አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ መንቲ ቀበሌ ሲሆን ተከሳሹ  የማይገባውን ብልፅግና ለማግኜት...
21/11/2025

ፍየል ሠርቆ የወሠደው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ፡፡
ከሳሽ፡-ዐ/ህግ
ተከሳሽ፡-አቶ ጌታሁን ጋሻው ዕድሜ 22 አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ መንቲ ቀበሌ ሲሆን ተከሳሹ የማይገባውን ብልፅግና ለማግኜት በማሰብ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ/ም በምዕ/በ/ወ አርባያ ከተማ ቀጠና 03 ልዩ ቦታው በተለምዶ ጭቃ ሠፈር እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ በግምት ከሌሊቱ 7:30 አካባቢ ሲሆን ንብረትነቱ የአቶ ደርብ ሽፈራው አንድ ቀይ ፍየል ከግል ተበዳይ ቤት ሰርቆ በመውሰድ ፍየሉን ያረደ በመሆኑ በፈፀመው የስርቆት ወንጀል ተከሷል፡፡ተከሳሽም ፍርድ ቤት ቀርቦ ክስ ከተነበበለት በኋላ የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ወንጀሉን የፈፀመ መሆኑን አምኖ ቃሉን የሰጠ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ሌላ ተጨማሪ ማስረጃ ሳያስፈልገው ግለሰቡ የፈፀመው ወንጀል ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጧል፡፡በመሆኑም ግለሰቡ በተከሰሰበት የወንጀል ድንጋጌ አንቀፅ 665/1/ መሠረት ህዳር 5/2018 ዓ/ም በዋለው የወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ነው በማለት ተከሳሹን ያርማል ሌላውን ያስጠነቅቃል ብሎ ያሰበውን የ1 ዓመት ከ2ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ የምዕራብ በለሳ ፍርድ ቤት ውሳኔውን አስተላልፏል፡፡⚖️⚖️⚖️

በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።   ከሳሽ፡-ዐ/ህግተከሳሽ፡-ሰለሞን (አድኖ) ማስሬ ወርቅየ  አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ አርባያ ከተማ ሲሆን ተከሳሹ በ1996 ዓ/ም ተደ...
20/11/2025

በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።
ከሳሽ፡-ዐ/ህግ
ተከሳሽ፡-ሰለሞን (አድኖ) ማስሬ ወርቅየ አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ አርባያ ከተማ ሲሆን ተከሳሹ በ1996 ዓ/ም ተደንግጎ የወጣውን የኢ.ፌ.ድ.ሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 669/3/ለ/ ላይ የተመለከተውን ህግ በመተላለፍ የማይገባውን ብልጽግና ለማግኜት በማሰብ ካልተያዘ ግብረ አበሩ ጋር በመሆን ንሐሴ 25/2017 ዓ/ም በአርባያ ከተማ ቀጠና 05 ልዩ ቦታው በተለምዶ ሀይስኩል እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ በግምት ከሌሊቱ 7 ሠዓት ላይ ሲሆን ንብረትነቱ የአቶ ጌታሰው እያየው አስፋውን የሸቀጣ ሸቀጥ ሱቅ በመስበር ጠቅላላ ግምቱ 105550/አንድ መቶ አምስት ሽ አምስት መቶ አምሳ/ብር የሚሆን ከግል ተበዳይ የወሰደ ሲሆን የግል ተበዳይም ጉዳዩን ለፀጥታ አካላት በማሳወቅ የፀጥታ አካላትም ጠቆማው እንደደረሳቸው ግለሰቡን ተከታትለው በመያዝ ተከራይቶ ከሚኖርበት መኖሪያ ቤቱ ድረስ በመሄድ ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ከግል ተበዳይ የወሰደውን ንብረት እንደያዘ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር የዋለ በመሆኑ በፈጸመው ከባድ የስርቆት ወንጀል ክስ ተመስርቶበታል፡፡
ተከሳሽ ፍርድ ቤት ቀርቦ ክስ ከተነበበለት በኋላ የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ድርጊቱን አልፈፀምኩም በማለት ክዶ የተከራከረ በመሆኑ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ፍርድ ቤትም በዐ/ህግ በኩል የቀረበለትን የሰውና የሠነድ ማስረጃ በአግባቡ ከረመረ በኋላ ተከሳሹ ጥፋተኛ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ተከሳሽም 3 የቅጣት ማቅለያ ተይዞለት ህዳር 03/2018 ዓ/ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያርማል ሌላውን ያስጠነቅቃል ብሎ ያሰበውን የ5ዓመት ከ5 ወር ፀኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።⚖️⚖️⚖️

20/11/2025
19/11/2025
በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።   ከሳሽ፡-ዐ/ህግተከሳሽ፡-ሰለሞን (አድኖ) ማስሬ ወርቅየ  አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ አርባያ ከተማ ሲሆን ተከሳሹ በ1996 ዓ/ም ተደ...
19/11/2025

በስርቆት ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።
ከሳሽ፡-ዐ/ህግ
ተከሳሽ፡-ሰለሞን (አድኖ) ማስሬ ወርቅየ አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ አርባያ ከተማ ሲሆን ተከሳሹ በ1996 ዓ/ም ተደንግጎ የወጣውን የኢ.ፌ.ድ.ሪ ወንጀል ህግ አንቀፅ 669/3/ለ/ ላይ የተመለከተውን ህግ በመተላለፍ የማይገባውን ብልጽግና ለማግኜት በማሰብ ካልተያዘ ግብረ አበሩ ጋር በመሆን ንሐሴ 25/2017 ዓ/ም በአርባያ ከተማ ቀጠና 05 ልዩ ቦታው በተለምዶ ሀይስኩል እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ በግምት ከሌሊቱ 7 ሠዓት ላይ ሲሆን ንብረትነቱ የአቶ ጌታሰው እያየው አስፋውን የሸቀጣ ሸቀጥ ሱቅ በመስበር ጠቅላላ ግምቱ 105550/አንድ መቶ አምስት ሽ አምስት መቶ አምሳ/ብር የሚሆን ከግል ተበዳይ የወሰደ ሲሆን የግል ተበዳይም ጉዳዩን ለፀጥታ አካላት በማሳወቅ የፀጥታ አካላትም ጠቆማው እንደደረሳቸው ግለሰቡን ተከታትለው በመያዝ ተከራይቶ ከሚኖርበት መኖሪያ ቤቱ ድረስ በመሄድ ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ከግል ተበዳይ የወሰደውን ንብረት እንደያዘ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር የዋለ በመሆኑ በፈጸመው ከባድ የስርቆት ወንጀል ክስ ተመስርቶበታል፡፡
ተከሳሽ ፍርድ ቤት ቀርቦ ክስ ከተነበበለት በኋላ የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ድርጊቱን አልፈፀምኩም በማለት ክዶ የተከራከረ በመሆኑ የምዕራብ በለሳ ወረዳ ፍርድ ቤትም በዐ/ህግ በኩል የቀረበለትን የሰውና የሠነድ ማስረጃ በአግባቡ ከረመረ በኋላ ተከሳሹ ጥፋተኛ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ተከሳሽም 3 የቅጣት ማቅለያ ተይዞለት ህዳር 03/2018 ዓ/ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያርማል ሌላውን ያስጠነቅቃል ብሎ ያሰበውን የ5ዓመት ከ5 ወር ፀኑ እስራት እንዲቀጣ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

15/11/2025

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when West Bellessa Woreda Court posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share