Wadla Woreda Revenue Office

Wadla Woreda Revenue Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Wadla Woreda Revenue Office, Government Organization, Bahir Dar.

15/04/2022
የዋደላ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት "ግብራችን ለህልውናችን" በሚል መሪ ቃል በደምቀ መልኩ የታክስ ንቅናቄ  መድረክ እያካሄደ ይገኛል::ሚያዚያ 7/2014 አ/ም
15/04/2022

የዋደላ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት "ግብራችን ለህልውናችን" በሚል መሪ ቃል በደምቀ መልኩ የታክስ ንቅናቄ መድረክ እያካሄደ ይገኛል::

ሚያዚያ 7/2014 አ/ም

 ደረሰኝ  ምን ማለት ነው?የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 19፣119 እና 130(1)(ለ) እንዲሁም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የ...
01/06/2021


ደረሰኝ ምን ማለት ነው?
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 19፣119 እና 130(1)(ለ) እንዲሁም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 240/2008 አንቀጽ 79 ላይ የተደነገጉ ድንጋጌዎችን ጣምራዊ ንባብ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸው ሕጎች መሠረት በማድረግ የደረሰኝ ትርጉም እና ምንነት፣ የደረሰኞች ዓይነቶች እና ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ ያለባቸው ግብር ከፋዮች እነማን እነደሆኑ እንዲሁም ደረሰኝ መሰጠት ያለበት መቼ እንደሆነ ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡
#ደረሰኝ ማለት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ያለበት ማንኛውም ታክስ ከፋይ ከደንበኞቹ ጋር ለሚያከናውነው ግብይትና ለሚሰበስበው ገንዘብ እውቅና የሚሰጥ ሕጋዊ ሰነድ ለደንበኞቹ ቆርጦ በመስጠት በመንግስት የተጣለበትን ግብር የማስከፈል እና የመክፈል ግዴታው የተወጣ ስለ መሆኑ የሚረጋገጥበት የማረጋገጫ ወረቀት ነው፡፡
የሽያጭ መመዝገቢያ መሣርያዎች ስለመጠቀም ለመደንገግ በሚኒስትሮች ምክርቤት የወጣ ደንብ ቁጥር 139/2007 አንቀጽ 2(3) ላይም ደረሰኝ (Receipt) ማለት የጥሬ ገንዘብ ሽያጭ ሲሆን፣ የዱቤ ሽያጭ ኢንቮይስና ያለክፍያ የሚሰጥ እቃ ወይም የአገልግሎት ማስተላለፍያ ደረሰኝን ይጨምራል በማለት ይደነግጋል፡፡ በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 19(3) መሠረት የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ያለበት ማንኛውም ግብር ከፋይ ደረሰኝ እንዲሰጥ ይገደዳል፡፡
የደረሰኙ አይነት በመመሪያው መሠረት የተወሰነው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ደረሰኝ የመስጠት ግዴታ ያለበት ግብር ከፋይ ካለደረሰኝ ግብይት ካከናወነ እንደየሁኔታው በአንቀጽ 119 ወይም በአንቀጽ 130(1)(ለ) መሠረት በወንጀል ይጠየቃል፡፡
የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ያለበት ማን ነው? የሚል መሰረታዊ ጥያቄ በመሆኑ መልስ የሚሻ ጉዳይ ነው፡፡ የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 79(1) እና (2) ላይ በግልፅ እንደተቀመጠው የንግድ ስራ ገቢ የመክፈል ሃላፊነት ያለባቸው የደረጃ ‘ሀ’ እና ‘ለ’ ግብር ከፋዮች በፋይናንስ ሪፖርት አቀራረብ መሠረት የተዘጋጁ የሂሳብ መዝገቦችን የመያዝ ግዴታ አለባቸው፡፡
የደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮችን በተመለከተ ግን የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት ባወጣው ደንብ በወሰነው መሠረት ጠቅላላ የሽያጭ ገቢያቸውን የሚያሳይ ወይም ሌላ አስፈላጊ መዝገብ ሊይዙ እንደሚችሉ የአዋጁ ድንጋጌ በንኡስ አንቀጽ 3 ላይ ይደነግጋል፡፡
በሌላ አገላለጽ የደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ የሚገደዱበት የህግ አግባብ የለም ማለት ነው፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳ እና በተግባር ላይም በባለሙያዎች መካከል ልዩነት እየፈጠረ የሚገኘው አንድ የደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋይ በፍላጎቱ የሂሳብ መዝገብ መያዝ የጀመረ እና የሽያጭ መመዝገብያ መሳርያ ያስገባ ከመሳርያው በሚወጣ ደረሰኝ ወይም ካለደረሰኝ ከተገበያየ በአስተዳደራዊም ይሁን በወንጀል ይጠየቃል ወይስ አይጠየቅም የሚለው ሲሆን የታክስ አስተዳደር አዋጁም በግልጽ ያስቀጠው ሂሳብ መዝገብ መያዝ እና ደረሰኝ መስጠት ግዴታ የተጣለበትን ግብር ከፋይ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
ሆኖም ግን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 119 እና 130(1)(ለ) በዚሁ አዋጅ ተደንግጎ ከሚገኘው አንቀጽ 19 (3) እና ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 240/2008 አንቀጽ 79(1) - (3) ከተጠቀሱት ድንጋጌዎች ጋር በጣምራ አገናዝበን ካልተረጎምነው በስተቀር ፍትሃዊ፣ ሚዛናዊ እና የህጋዊነትን መርህ መሠረት ያደረገ ውሳኔ መስጠት አንችልም፡፡
እነዚህ ግብር ከፋዮች (የደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች) በፍላጎታቸው እና በራሳቸው ተነሳሽነት የሽያጭ መመዝገብያ መሳርያ አስገብተው ሲያበቁ የሽያጭ መመዝገብያ መሳርያው ላለመጠቀም የሚያስችል ምንም አይነት አስገዳጅ ሁኔታ ሳይገጥማቸው ከሽያጭ መመዝገብያ መሳርያው በሚወጣው ደረሰኝ መሠረት ካልተገበያዩ ወይም ከነአካቴው ካለደረሰኝ ግብይት ከፈጸሙ በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 በአንቀጽ 119 ወይም 130(1)(ለ) መሠረት ሊጠየቁ ይገባል የሚል የታክስ ህግ ድንጋጌ፣ ይዘት፣ መንፈስ እና አላማ የለውም፡፡
በእርግጥ እነዚህ ግብር ከፋዮች በፍላጎታቸው የሂሳብ መዝገብ ከያዙና የሽያጭ መመዝገቢያ መሳርያ ቢጠቀሙ የሚበረታታና በመረጃ ላይ የተመሰረተ የታክስ አሰባሰብ መርህን ስኬታማ የሚያደርግ ከመሆኑ በተጨማሪ ጊዜ እና ጉልበት ቆጣቢ በመሆኑም ጠቀሜታው እጅግ በጣም የላቀ ነው፡፡
ይህን የውዴታ ሃላፊነታቸው ካልተወጡ ግን በአመታዊ የሽያጭ መጠን ላይ የተመሰረተ የግምት መደበኛ የቁርጥ ግብር ወይም በሌላ የቁርጥ ግብር ዘዴዎች ግብር እንዲከፍሉ ከማድረግ ውጪ ደረሰኝ ባለመቁረጣቸው ምክንያት ብቻ በወንጀል ሃላፊነት እንዲጠየቁ የሚያደርግ ግልጽ የሆነ የህግ መሠረት የለም፡፡ምክንያቱም የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 240/2008 አንቀጽ 79(3) እና የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 241/2008 አንቀጽ 19፣119 እና 130(1)(ለ) የደረጃ ‘ሐ’ ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ ሆነ ደረሰኝ እንዲሰጡ ሊገደዱ እንደማይችሉ ነው፡፡

28/05/2021

09/04/2021

Invite Friends to Like Your Page
More people might see your posts in News Feed if your friends like your Page and share posts. Invites will be sent from Assefa Biset.

ታክስ በግምት የሚወሰንበት ስልትበጥላሁን ጀንበሩየግምት ታክስ ስሌት ማለት ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ ሕግ መሠረት ማቅረብ የሚገባውን የታክስ ማስታወቂያ ያላቀረበ እንደሆነ ወይም በግምት ከ...
26/03/2021

ታክስ በግምት የሚወሰንበት ስልት
በጥላሁን ጀንበሩ
የግምት ታክስ ስሌት ማለት ማንኛውም ታክስ ከፋይ በታክስ ሕግ መሠረት ማቅረብ የሚገባውን የታክስ ማስታወቂያ ያላቀረበ እንደሆነ ወይም በግምት ከመወሰኑ በፊት ካላቀረበ ወይም የሒሳብ መዝገብ ሳያቀርብ ገቢውን ያስታወቀ ወይም ቢሮው በመለወጥ፣ በመቀነስ ወይም በመጨመር የሒሳብ መዝገቡን ያሻሻለ እንደሆነ በማንኛውም ጊዜ የሚያገኘውን ማስረጃ መሠረት በማድረግ
ታክስ ከፋዩ ሊከፍለው የሚገባውን የታክስ መጠን የሚገልጽ ስሌት ነው፡፡
 => የእለት ገቢን በመገመት /Estimated Assessment/፡- የግብር ከፋዮችን
የንግድ እንቅስቃሴ መሠረት ያደረገ በገቢ ጥናት (የክትትል) ባለሙያዎች የህሊና ዳኝነት ላይ ተመስርቶ የቀን ገቢ ይገመታል፡፡ ይህም የቀን ገቢ ግምት ወደ አማካኝ ዓመታዊ ሽያጭ መቀየር ለዚህ በተዘጋጀው የንግድ ዘርፍ የትርፍ
መቶ መተመኛ ምጣኔ /Profitability rate/ ተለይቶ ባለው የገቢ ማስከፈያ ተመን መሠረት ታክሱ ይጠየቃል፡፡
 => በመረጃ መሠረት የሚወሰን፡- የግብር ከፋዩ መዝገብ ከሂሳብ አያያዝ ስርዓትና ከግብር ሕጉ አኳያ ተመርምሮ ተቀባይነት ሳያገኝ ሲቀር ወይም ከሶስተኛ ወገን በሚገኝ የግዥ ወይም የሽያጭ መረጃ ላይ በመመሥረት ታክሱ
ይወሰናል፡፡
 => በቁርጥ የሚወሰን ግብር /Presumptive Taxation/:- ግብር ከፋዮች
መዝገብ ሳይዙ ሲቀሩ ወይም መዝገቡ ተመርምሮ ውድቅ ሲሆን ወይም መዝገብ
የመያዝ የሕግ ግዴታ የሌለባቸው የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ግብር ወይም ስለ ግብር ከፋዩ በቀን ገቢ ግምት ወይም ከሶስተኛ ወገን መረጃ ማግኘት ሳይቻል ሲቀር ታክሱ በቁርጥ /Presumptive/ ይወስናል፡፡

ለግንዛቤዎበጥላሁን ጀንበሩከታክስ ከፋይ ግዴታዎች ውስጥ፡- በግብር ከፋይነት የመመዝገብ ግዴታ፣ በባለሥልጣኑ የተፈቀደ ደረሰኝ የማሳተምና የመጠቀም ግዴታ፣ የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ደ...
17/03/2021

ለግንዛቤዎ
በጥላሁን ጀንበሩ
ከታክስ ከፋይ ግዴታዎች ውስጥ፡-
 በግብር ከፋይነት የመመዝገብ ግዴታ፣
 በባለሥልጣኑ የተፈቀደ ደረሰኝ የማሳተምና የመጠቀም ግዴታ፣
 የሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ደረጃ ሀ እና ለ፣
 ለተጨማሪ እሴት ታክስ የመመዝገብ ግዴታ ዓመታዊ ሽያጩ ከ 1 ሚሊዮን
ብር በላይ፣
 ግብይትን በደረሰኝ ብቻ የማከናወን ግዴታ፣
 በህግ በተመለከተው ጊዜ ገቢውን ወይም ሽያጩን አሳውቆ ትክክለኛ ታክሱን
የመክፈል ግዴታ፣
 ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብርን ቀንሶ የማስቀረትና ለባለስልጣኑ ገቢ ማድረግ
ግዴታ፣
 ህጋዊና ትክክለኛ ደረሰኞችንና ሰነዶችን ብቻ የመጠቀም ግዴታ፣
 በታክስ ደረሰኝና ሌሎች የግብይት ሰነዶች ላይ የገዥውን ወይም
የአገልግሎት ተቀባዩን የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የመፃፍ ግዴታ፣
አስተዳደራዊ ቅጣቶች
 በታክስ ከፋይነት ያልተመዘገበ እንደሆነ የግብሩን 25% መቀጮ ይቀጣል፡፡
 የሚከፈል ግብር ከሌለ በየወሩ 1,000 ብር ይቀጣል፡፡
 ከግብር ከፋይነት እንዲሰረዝ ያልጠየቀ በየወሩ 1,000 ብር መቀጫ
ይከፍላል፡፡
 የሒሳብ መዝገብ ያልያዘ እንደሆነ የግብሩን 20% መቀጮ ይከፍላል፡፡
 የሚከፈል ታክስ እንኳን ባይኖር ለገቢ ግብር በዓመት 20,000 ብር ለሌሎች
ታክሶች በየወሩ 2,000 ብር ይቀጣል፡፡
 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በደረሰኝ ላይ አለመጻፍ ቁጥሩ ባልተጻፈበት
በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብር 3,000 ያስቀጣል፡፡
 የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tax Identification Number/TIN) ለሌላ
ሰው የሰጠ ብር 10,000 ይቀጣል፣
 የሌላ ሰው TIN የተጠቀመ ብር 10,000 ይቀጣል፣
 የግብር ማስታወቂያ ማዘግየት 5% ያስቀጣል (25% እስኪሞላ ድረስ)
 ግብር/ታክስ ሳይከፈል ማዘግየት ለአንድ ወር 5% ከዚያ በላይ ለሆነው ጊዜ
ተጨማሪ 2% መቀጫ ያስከፍላል፡፡
 ከተከፋይ ሂሳብ ላይ ግብር ያልቀነሰ ወይም ቀንሶ ገቢ ያላደረገ
ያልተቀነሰውን ወይም ገቢ ያልተደረገውን ግብር 10% ይቀጣል፡፡
 እንዲሁም ሥራ አስኪያጁና የሂሳብ ሹሙ እና ግብሩን ተቀናሽ ያላደረጉ
ሠራተኞች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 ይቀጣሉ፡፡
 ለተጨማሪ እሴት ታክስ አለመመዝገብ በየወሩ 2,000 ብር ያስቀጣል፡፡
 ባልተመዘገበበት ጊዜ ላከናወነው ግብይት ሊከፈል የሚገባውን ታክስ 100%
ይቀጣል፡፡
 ታክስን ለማሳነስ ወይም ተመላሽ እንዲጨምር ለማድረግ ትክክለኛ ያልሆነ
ደረሰኝ የሰጠ ሰው ብር 50,000 ይቀጣል፡፡
 ደረሰኛ መስጠት ሲገባው ያልሰጠ ባልሰጠው በእያንዳንዱ ደረሰኝ ብር
50,000 ይቀጣል፡፡
 ታክስ አሳንሶ ማሳወቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን 10% ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን
30% ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን 40% መቀጮ ያስከትላል፡፡
 ታክስ ላለመክፈል የሚደረጉ ጥረቶች ያልተከፈለውን ታክስ እጥፍ መቀጫ
ያስቀጣል፡፡
የኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት አለመከተል
 ታክሱን በኤሌክትሮኒስ ሥርዓት አሳውቆ እንዲከፍል የተጠየቀ ግብር ከፋይ
በዚሁ መሠረት ያልፈጸመ እንደሆነ ብር 5ዐ,ዐዐዐ ይቀጣል፡፡
በታክስ ወኪል ላይ የሚጣል መቀጫ
 የታክስ ወኪል ለደንበኛው የምስክር ወረቀት ወይም መግለጫ ከልሰጠ
ወይም እነዚህን መረጃዎች በህግ ለተወሰነው ጊዜ ይዞ ያልቆየ እንደሆነ፣
 ሥራ ማቆሙን ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ብር 1ዐ,ዐዐዐ ይቀጣል፡፡
ከሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ
 የሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያ የመጠቀም ግዴታ ያለበት ማንኛውም ግብር
ከፋይ፤
 እውቅና ያልተሰጠውን መሣሪያ ተጠቅሞ ከተገኘ ለእያንዳንዱ መሣሪያ
5ዐ,ዐዐዐ ብር፣
 በሸያጭ መመዝገቢያ መሣሪያ ከታተመ ደረሰኝ ውጪ ሌላ ደረሰኝ
ከተጠቀመ ብር 5ዐ,ዐዐዐ፣
 በመሣሪያው ላይ ጉዳት ያደረሰ ወይም የፊሲካል ማስታወሻው እንዲቀየር
ያደረገ ወይም ይህን ለማድረግ ሙከራ ያደረገ ብር 1ዐዐ,ዐዐዐ፣
 በመሣሪያው ላይ ፍተሻ (ኦዲት) እንዳይደረግ የተከላከለ ወይም የቴክኒክ
ምርመራ በየዓመቱ ያላደረገ ብር 25,ዐዐዐ፣
 ከአገልግሎት ማዕከል ጋር ውል ካልፈጸመ ወይም መሣሪያውን ከተርሚናል
ጋር ሳያያይዝ ከተጠቀመ ወይም የመሣሪያው ምርመራ መዝገብ ከመሣሪያው
ጐን እንዲቀመጥ ካላደረገ ወይም በተመላሽ መዝገብ ሳይመዘገብ የተመላሽ
ደረሰኝ ከሰጠ ብር 25ዐዐዐ፣
 መሣሪያው አገልግሎት መስጠት ሲያቋርጥ (ሲሰረቅ ወይም ሲጐዳ)
በሦስት ቀናት ውስጥ ወይም ሲበላሽ በአራት ሰዓት ውስጥ ለአገልግሎት
ማዕከሉና ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ብር 1ዐ,ዐዐዐ፣
 መሣሪያው ያለበትን ትክክለኛ አድራሻ ለባለሥልጣኑ ያላሳወቀ እንደሆነ ብር
5ዐ,ዐዐዐ፣
 የአድራሻ ወይም የስም ለውጥ ሲያደርግ ወይም የንግድ ሥራውን ሲያቋርጥ
ከሦስት ቀናት አስቀድሞ ለአገልግሎት ማዕከሉና ለባለሥለጣኑ ያላሳወቀ
እንደሆነ ብር 25,ዐዐዐ፣
 መሣሪያው ባለበት የንግድ ሥራ ቦታ በህጉ የተዘረዘሩ አስፈላጊ መረጃዎችና
ማስታወቂያዎች ካልተቀመጡ ብር 1ዐ,ዐዐዐ፣
 የሽያጭ ነቁጣ ሶፍት ዌር ዕውቅና ባልተሰጠው ሰው አስቀይሮ ወይም
እንዲሻሻል አድርጐ ከተገኘ ብር 3ዐ,ዐዐዐ ይቀጣል፡፡
 የማይሰራ፣ የተበላሸ (የተጐዳ) መሣሪያ ለአገልግሎት ማዕከላት በሦስት
ቀናት ውስጥ አቅርቦ ማስቀየር (መተካት) አለመቻሉን ለባለሥልጣኑ አስቀድሞ
ካላሳወቀ ብር 5ዐ,ዐዐዐ፣
 ስለተዋዋለባቸው አገልግሎት ማዕከላት መረጃ ካልያዘ ወይም
ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ ብር 5ዐ,ዐዐዐ፣
 የሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያዎች አገልግሎት ማዕከል፣
 የፊሲካል ማስታወሻ በተተካ በሁለት ቀናት ውስጥ ለባለሥልጣኑ ካላሳወቀ
ብር 25,ዐዐዐ፣
 ውል የገባባቸውን መሣሪያዎች በዓመት አንድ ጊዜ የቴክኒክ ምርመራ
ካላደረገ ብር 25,ዐዐዐ፣
 ዕውቅና ያልተሰጠውንና በባለሥልጣኑ ያልተመዘገበ ሠራተኛ ለሥራ
አሰማርቶ ከተገኝ ብር 5ዐ,ዐዐዐ ይቀጣል፡፡
ስለ ታክስ እውቀት ያለው ትውልድ እንዲኖር እንትጋ

ከግብር ለመሸሽ የሚደረግ ዕቅድበአቶ ጥላሁን ጀንበሩ (የግብር ትምህርት ባለሙያ)ከግብር ኃላፊነት ለማምለጥ ወይም ሊከፈል ከሚገባው ያነሰ ግብር ለመክፈልከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ህጋዊ በሚመስሉ ...
14/03/2021

ከግብር ለመሸሽ የሚደረግ ዕቅድ
በአቶ ጥላሁን ጀንበሩ (የግብር ትምህርት ባለሙያ)
ከግብር ኃላፊነት ለማምለጥ ወይም ሊከፈል ከሚገባው ያነሰ ግብር ለመክፈል
ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ህጋዊ በሚመስሉ አሠራሮችና ግንኙነቶች በመታገዝ
አስቀድሞ በታሰበና በተጠና መልኩ “ግብር ያለመክፈል ዕቅድ” በመዘርጋት
ተግባራዊ ማድረግ ማለት ነው።
ማቀድ አንድን ተግባር ለመፈፀም ከማሰብም በላይ በመሆኑ ዕቅዱ በመንግስት
የኢኮኖሚ ጥቅም ላይ ለሚፈፀሙ ሴራዎች መነሻ ነው ማለት ይቻላል።
ይህንና ተመሳሳይ ሴራዎችን ለማክሸፍ የሚያስችሉ ድንጋጌዎች በገቢ ግብር
አዋጅ ውስጥ ተካቶ በአሁኑ ወቅት የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴው
እያደገና እየሰፋ የመጣበት ሁኔታ በመኖሩ ግብር ላለመክፈል የሚዘረጉ ዕቅዶችና
ስልቶች እጅግ እየረቀቁና እየተወሳሰቡ የሚመጡ መሆናቸውን ከግምት ውስጥ
በማስገባት አንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ግብር ከፋዮች ከግብር ለመሸሽ
የሚያስችል ዕቅድ በማዘጋጀትና በመተግበር የግብር ጥቅም ያገኙ እንደሆነ
ባለስልጣኑ፤
 ይህ የተደረገበት ብቸኛ ወይም ዋነኛ ዓላማ የግብር ጥቅም ለማግኘት
መሆኑን በማረጋገጥ፣
 ዕቅዱ ወይም ስምምነቱ እንዳልተደረገ ወይም እንዳልተተገበረ በመቁጠርና
አግባብነት ያላቸውን ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት ግብር የመክፈል
ግዴታ ያለበትን ሰው ወይም ከዕቅዱ ጋር ግንኙነት ያለውን ሌላ ሰው ግብር
ሊወሰን ይችላል።
 ለግብር ከፋዩ የግብር ውሳኔ ማስታወቂያም ይሰጣል።
 የግብር ጥቅም የሚለው ቃል ሊከፈል የሚገባን ግብር ማስቀረትን ወይም
መቀነስን፣ ግብር የመክፈል ኃላፊነትን ማዘግየትን ከግብር በመሸሽ የሚገኝን
ማንኛውንም ጥቅም ይጨምራል።
 ግብር ለመሸሽ ከሚደረጉ ዕቅዶች ዓይነተኛ ምሳሌ የሚሆነው “tax
planning” ነው።
 ከግብር መሸሽ (tax avoidance) ግብር ከመሰወር (tax evasion)
የሚለይ ሲሆን ከግብር መሸሽ (tax avoidance) የህግ ከፍተቶችንና የፖሊሲ
ቀዳዳዎችን በመጠቀም ህጉ ተፈጻሚ እንዳይሆንባቸው ሁኔታዎችን ከማመቻቸት
ጋር የተያያዘ ሆኖ ጥፋቱ በአስተዳደር የሚያስቀጣ ነው።
 ግብር መሰወር (tax evasion) ግብር ላለመክፈል በማሰብ ሆነ ብሎ ህግን
በመጣስና ህጋዊ ግዴታን ባለመወጣት መከፈል የሚገባን ግብር በከፊል ወይም
በሙሉ አለመክፈል ወይም አነስተኛ ግብር ለመክፈል ገቢንና መረጃን መደበቅን
ያጠቃልላል።
ከግብር መሸሽ ማህበራዊ ግዴታን አለመወጣት ማለት ነው
አንድ ታክስ ከፋይ በስግብግብነት እና በራስ ወዳድነት ለህግ ተጠያቂነት
ተጋላጭ ያደርገዋል፣ ዝናውን ያበላሸዋል እንዲሁም የህዝቡን አመኔታ
ያሳጣዋል።
ከግብር መሸሽ የታክስ ስርዓቱን እጅግ ታማኝነትን የሚሸረሽር ሥነ- ምግባር
የጎደለው ተግባር በመሆኑ በጋራ ልንከላከለው ይገባል።
በሌላ በኩል የግብር ማጭበርበር የግብር ክፍያውን በማታለል፣ በተንኮል
ማጥበብ ወይም በመደበቅ ለመቀነስ የሚደረግ ሙከራ ነው።
ግብርን ማጭበርበር ማለት ገቢን ወይም መረጃን ከታክስ ባለሥልጣናት
መደበቅ ማለት ሲሆን ድርጊቱም ሕገ-ወጥ ነው ከግብር መሸሽ ማለት ግብር
የሚከፈልበት ገቢን በሕጋዊነት መቀነስ ማለት ሲሆን ምክንያቶች ውስጥ፡-
 የግብር ስርዓት አወቃቀር፣
 በተለያዩ የመንግስት ደረጃዎች መካከል የሥርዓት አልበኝነት መኖር፣
 የሥልጣን ክፍፍል በተለይም በፌዴራል እና በክልሎች መካከል፣
 የህዝብ ብዛት፣
 ዝቅተኛ የትምህርት ደረጃ፣
 የታክስ ሕጉ ቀላልነት እና ትክክለኛነት እጥረት፣
 የዋጋ ግሽበት፣
ብዙውን ጊዜ በግብር ስወራ ወይም በግብር መሸሽ እቅዶች ውስጥ የመሳተፍ
ዕድላቸው ከፍተኛ ገቢ ያላቸው ናቸው ተብሎ ይታመናል።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wadla Woreda Revenue Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share